en
Feedback
UMER SEMEREDIN 🇪🇹

UMER SEMEREDIN 🇪🇹

Open in Telegram

ስህተት ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ አደራ👌 ሼር በማድረግ ይተባበሩን🙏 ━━━━━━━━━━━━━ #ማሳሰብያ:Leave Channel ከማለቶ በፊት ያልተመቾት ነገር ካላ በፍጥነት ያሳውቁን🔥 ━━━━━━ 👇 ━━━━━ For any comment and Cross ▼▼▼▼▼▼▼▼▼▼ 👉 @Lekel_hemdu_rebi

Show more
1 048
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-3430 days
Posts Archive
💚ኸሚስ ምሽቱ የናፈቅነውን፣የከጀልነውን ሁሉ የምናገኝበት ይሁንልን🤲 አብሽሩ🥰 ለኛም ቀን አለን ሁሉም ነገር አሁን እንዳለበት አይቀጥልም፤ያስፈልገናል ያልነው ነገር ሁሉ የሚያስፈልገን ጊዜ ሲደርስ የሰጪዎች ሰጪ የሆነው ጌታችን ይሰጠናል እናንተ ብቻ ከዱዐ አትቦዝኑ ምሽታችንም በሰለዋት ይድመቅ اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد 💚💚💚

. የሰዎችን ልብ ከፍተን የማየት ዕድሉን ብናገኝ እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ ከባድ ህመም አለው። ዝም ማለት አለመታመምን አይገልፅም።

ሕይወት ያንቱ ስም ባይጠራበት ኖሮ…መራር ነበር! ሙሀመድﷺ🤎 اللهم صل وسلم وبارك على نبينا وحبيبنا مُحمد

ሰምቸው በጣም ያስገረመኝን ነገር ላጋራችሁ ሰላት ስንሰግድ መጀመሪያ እንቆማለን አይደል ያ የሚወክለው ا ( አሊፍ) ነው ከዛ ሩኩዕ አለ እሱ ደሞ የሚወክለው حا ( ሃ) ነው ከዛ ሱጁድ ስንወርድ م ( ሚም) ይወክላል ከሱጁድ ተነስተን ስንቀመጥ د ( ዳል) ይወክላል አንድ ላን ስንገጥማቸው احمد ( አህመድ) የሚል ይሰጠናል አህመድ የማን ስም ነው የሚለውን ለናንተ ትቻለው .

اللهم اغفِر لي ما قَدَّمْتُ وما أخَّرْتُ وما أسْرَرْتُ وما أعلَنتُ وما أنت أعلَمُ به منِّي أنت المُقَدِّمُ وأنت المُؤَخِّرُ و
اللهم اغفِر لي ما قَدَّمْتُ وما أخَّرْتُ وما أسْرَرْتُ وما أعلَنتُ وما أنت أعلَمُ به منِّي أنت المُقَدِّمُ وأنت المُؤَخِّرُ وأنت على كلِّ شىءٍ قدِير أسعد الله صباحكم بكل خير

" ተነሱ ውጡ ከዚህ! እዚያ ፍልስጤማዊያንን ጨፍጭፋችሁ እዚህ ትዝናናላችሁ ውጡ ከዚህ ! እዚያ ጋዛ ላይ እየጨፈጨፋችሁ እዚህ ትበላላችሁ ትጣጣላችሁ? ውጡ ! ፍልስጥኤም ነፃ ሆና ለዘልአለም ትኑር!" ይህ እንግድህ እስራኤላውያን ጎብኝዎች በስፔን የገጠማቸው ነው። ስፔይናዊያን በጣም ተለዩብኝ! ይህ ስፔናዊ የሪዞርት ባለቤትም እየተዝናኑ የነበሩት እስራኤላውያን መሆናቸውን ባወቀ ጊዜ እንደዚህ አባሯቸዋል። በአሁኑ ሰአት አለም ሁሉ የሚፀየፋቸው ሄ ህዝቦች ሆነዋል። ማንም ሊጠጋቸው ቀርቶ ሲያቸው የሚያመው ፀያፎች ሆነዋል። እና በዚህ ከቀጠለ እስራኤላውያን ወደፊት አለም ትጠብባቸዋለች።

እንዲህ ቢሆንስ...? ረሱል ﷺ በህልምህ መተው በጀነት ጎረቤቴ ነህ ቢሉህ ምን ይሰማሀል(ሻል)....?
እንዲህ ቢሆንስ...? ረሱል ﷺ በህልምህ መተው በጀነት ጎረቤቴ ነህ ቢሉህ ምን ይሰማሀል(ሻል)....?

በኒን ሰፈር በምንወልበት ጊዜ እንዲሁ አንድ በዱኑ ጠንካራ "ሱንይ" ነኝ ብሎ የሚያስብ ወጣት አንድን መስጂድ የሚውሉ አዛውንት ውዱእ ሲያደርጉ አገኛቸው ጺማቸውን ተላጭተው ነበርና አባባ ምነው ሱና ለምን ሐይ አያደርጉም ይላቸዋል? በኃላ ጫን ብሎ ስለ ጺም ማሳደግ ይነተርካቸው ጀመር። ምን ብለው መለሱለት መለሰለህ። « አቦ ልጄ ተወኝ እኔ አቅሜን አውቃለሁ ከእርሳቸው ጋር አልለካካም አሉት።» :-D እነዚህ የድሮ አባቶች ከሕይወት፣ ከሸይኾቻቸው የተማሩት ብዙ ነው። ከሰው ጋርም አይሟገቱም እንዲሁ አላዋቂ መስለው አላህ ጋር የቀረቡ ልዩ ሰዎች ናቸው። እርግጥ የእስልምና ልዩ አስኳሉም መምሰል፣ ማስመሰል፣ ጩኸት ሳይኾን መረዳትና መኖር መቻል ነው። አላህ በቁጥር የሚመለክ ሳይኾን በዘውቅ የሚቀርቡት ጌታ ነው። አላህ ዘውቁን ይስጠና ♥

#ሊላሂ_ተአላ... በዐሹራ ቀን አራት ሱና ረከአት የሰገደ ሰው ከፋቲሐ በኋላ በእያንዳንዱ ረከዓ ‹ቁል ሁዋ አሏሁ አሀድ› አስራ አንድ ጊዜ ያነበበ አላህ የሃምሳ አመት ወንጀሉን ይማርለታል። በዐሹራ ቀን የሱና ሻወር ያወሰደ ሰው በዚያ አመት ከሞት ህመም በስተቀር አይታመምም እና ኩልን በአሹራ ቀን አይኑን የተቀባ ሰው በዚያ አመት ህመም አይሰማውም።

ነገ ጁመዓና ቅዳሜ የዐሹራእ ፆም እንዳያመልጣችሁ! #ሼር እያደረግን ሙስሊሞችን እናስታውስ (ሊላሂ ተዓላ)

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን 😭 ዕውቁ ማዲህ ሸኽ ሙሀመድ ሁሴን ወደ አኼራ ሄደዋል። አላህ ይዘንላቸው። ለዘመናት የተቀኙላቸውን ነብይ ሸፈዐ እና ጉርብትና ይወፍቃቸው። ጀነተል ፊርደውስን ይግጠማቸ
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን 😭 ዕውቁ ማዲህ ሸኽ ሙሀመድ ሁሴን ወደ አኼራ ሄደዋል። አላህ ይዘንላቸው። ለዘመናት የተቀኙላቸውን ነብይ ሸፈዐ እና ጉርብትና ይወፍቃቸው። ጀነተል ፊርደውስን ይግጠማቸው።  ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው ሶብርን እመኛለሁ። إنا لله وإنا إليه راجعون አላህ ይዘንላቸው  ቀብራቸውን የጀነት ጨፌ ያድርግላቸው ያረብ 🤲

🌙🌙የጠዋትና የማታ አዝካር🌙🌙 💯🎙መቶ(100) ጊዜ ያለ🎙💯 👉አስር ባሮችን ነፃ እዳወጣ ይቆጠርለታል 👉መቶ ሀሰናት(አጅር) ይፃፍለታል ። 👉መቶ ወንጀል ይሰረዝለታል ። ሙስሊም ዘግቦታል ። Muslim  4/2071 لاَ إِلَـهَ إِلاَّ اللهُ وَحْدَهُ لاَ شَرِيْكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيْرُ. (100× إذا أصبح) l«ላኢላሀ ኢልለሏህ ወህደሁ ላሸሪከ ለሀ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሃምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር ።» ☞ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም፡፡ አንድ ነው፡፡ አጋር የለውም፡፡ ንግሥና ለርሱ ብቻ ነው፡፡ ምስጋናም ተገቢው ነው፡፡ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፡፡››- ✔ምሽት / ንጋት ላይ መቶ ጊዜ፡፡

ከሁሉም ዐሊዩ ቀደመ ቸኩሎ መደብ ተጋደመ ድመሙ ሶፊዩ ሀይደር ሳይሰስት ሳይግደረደር ወዳጄ አንተን ክፉ አይንካህ አለሁኝ በቦታህ ልተካህ ማለና ፊዳ ልሁን ብሎ ተኛሎት መደብ ተጠቅልሎ

ዐሊይ: ያቺን ለሊት! የመካ ቁረይሾችም ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) በአንድነት ለመግደል በተስማሙበት፣ የእስልምናን ብርሃን ለማጥፋት ባሴሩበት በዚያ ወሳኝ ሌሊት፣ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ከአላህ
ዐሊይ: ያቺን ለሊት! የመካ ቁረይሾችም ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) በአንድነት ለመግደል በተስማሙበት፣ የእስልምናን ብርሃን ለማጥፋት ባሴሩበት በዚያ ወሳኝ ሌሊት፣ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ከአላህ ዘንድ መካን ለቀው ወደ መዲና እንዲሰደዱ ታዘዙ። ይህ ጉዞ የእስልምናን የቀን መቁጠሪያ ብቻ ሳይሆን፣ የፍትሃዊ ማህበረሰብንም መሰረት የሚጥል ታሪካዊ ክስተት ነበር። ነገር ግን ከመውጣታቸው በፊት፣ ጠላትን እንዲያዘናጋላቸው በሳቸው ቦታ ተተክቶ እንዲተኛ የጠላቶችን አይን እንዲያሳስት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) አንድ ታላቅና ከባድ አደራ ለአንድ ሰው ሰጡ። ይህን የከበረ ተልዕኮ እንዲወጣ የተመረጠው ሌላ ማንም አልነበረም —ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የአጎት ልጅ፣ ወንድማቸውና ታማኝ ደጋፊያቸው የሆኑት ዐልይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ (ዐ.ሰ) እንጂ። ዐልይ ይህን ሃላፊነት የተቀበሉት በፍጹም መረጋጋትና በማይናወጥ ፍቅር ነበር። በየትኛውም ቅጽበት ሰይፎች ሊወርዱባቸው እንደሚችሉ እያወቁም፣ በነቢዩ አልጋ ላይ ተኙ። አላመነቱም፤ ፈጽሞም አልፈሩም። ታሪክ በርካታ ጀግና ነፍሳትን ያስታውሳል፤ ነገር ግን ህይወታቸውን ያለ ምንም ማመንታት ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑት ጥቂቶች ናቸው። ለእውነት፣ ለፍቅር እና ለመለኮታዊ ተልዕኮ መከበር እንዲህ ያለ መስዋዕትነት እምብዛም ነው። እናም አሊይ ያቺን ለሌት ሲነቁ እንደ ሰማዕት ሳይሆን፣ እንደ የማይረሳ ታሪክ — ከእንቅልፋቸው ተነሱ።

ኢማም አል ገዛሊ رحمه الله በአንድ ወቅት: " ያ ኢማም! አንድ ሰላቱን የተወ ሰው ላይ የሸሪኣው ፍርድ ምንድነው?" በማለት ተጠየቁ። ኢማሙም የሚገርም መልስን መለሱለት! እንዲህም አሉ: "ፍርዱ ነው ያስጨነቀህ?" አሉት። "አዎ! ያ ኢማም አላህ ጋር ያለው ቅጣት ምን ይሆናል የሚለው አሳስቦኝ ነው።" አላቸው! ... እንግዲያውስ አሉ ኢማሙ! "እንግዲያውስ አንተ ሰላቱን የተወውን ሰው እጁን ይዘህ ወደ መስጂድ መውሰድህ ነው ፍርዱ። ተጣሪ እንጂ ፈራጅ አትሁን!" አሉት! ይባላል አላህ ከተጣሪዎች ያድርገን 🤲🏼 የተዋበ ጁምዓ😘 ሱረቱል ከሀፍ ዱዓ ሰለዋት اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد 💚صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين

በዛሬው እለት አዲስ ጨረቃ በመታየቱ በሒጅሪ የዘመን ቀመር የዓመቱ መጀመርያ የሆነው ሙሐረም ወር መግባቱ መረጋገጡን ኢንሳይድ ሐረመይን ዘግቧል።
በዛሬው እለት አዲስ ጨረቃ በመታየቱ በሒጅሪ የዘመን ቀመር የዓመቱ መጀመርያ የሆነው ሙሐረም ወር መግባቱ መረጋገጡን ኢንሳይድ ሐረመይን ዘግቧል።

ከፍ ለማለት ዝቅ ማለትን ልመድ!!ሁሌም ራስህን አስተናንስ ያኔ ደረጃህ ከሰዎች ብቻ ሳይሆን ከጀሊሉ ዘንድም ከፍ ያለ ይሆናል!!

اللهم نستودعك قطر وأهلها والمقيمين على أرضها وسائر بلاد المسلمين ኳታር ያላችሁ አላህ ይጠብቃችሁ🤲❤️

ዛሬ መካከለኛው ምስራቅ ላይ ትልቅ የጦርነት ድግስ አለ። የአረብ ሀገራቴ አየር ክልላቸውን ሙሉ ዘግተዋል። የቱርክ አየር መንገዶች ወደ ኢማራት ኳታር እና መሰል ሀገራት የሚያደርጉትን በረራ ሰርዘዋል።
ዛሬ መካከለኛው ምስራቅ ላይ ትልቅ የጦርነት ድግስ አለ። የአረብ ሀገራቴ አየር ክልላቸውን ሙሉ ዘግተዋል። የቱርክ አየር መንገዶች ወደ ኢማራት ኳታር እና መሰል ሀገራት የሚያደርጉትን በረራ ሰርዘዋል። GPS በመካከለኛው ምስራቅ ጠፍቷል። የአሜሪካና እንግሊዝ የጦር ጄቶች በቀጠናው እየተርመሰመሱ ነው። የኢራን ሚሳኤሎች የአሜሪካን የጦር ሰፈሮች አነጣጥረው እንደተሰደሩ እየተነገረ ነው። ዛሬ ጦርነቱ አንድ ወደፊት እንዳይባባስ የሚያሰጋበት ቀን ነው።

ነገ ሰኞ ነው የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ