UMER SEMEREDIN 🇪🇹
Open in Telegram
ስህተት ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ አደራ👌 ሼር በማድረግ ይተባበሩን🙏 ━━━━━━━━━━━━━ #ማሳሰብያ:Leave Channel ከማለቶ በፊት ያልተመቾት ነገር ካላ በፍጥነት ያሳውቁን🔥 ━━━━━━ 👇 ━━━━━ For any comment and Cross ▼▼▼▼▼▼▼▼▼▼ 👉 @Lekel_hemdu_rebi
Show more1 048
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-3430 days
Posts Archive
1 048
✅ማክበር ማለት ማስታወስ፣ ለቀኑ እውቅና መስጠት፣ በሰው ልጅ ትውስታ ደጋግሞ እንዲታተም ማድረግ፣ ውለታቸውን ማስታወስ፣ የመምጣታቸው ብስራት በደስታ መቀበል፣ አጋጣሚውን የበለጠ እሳቸውን ለመተዋወቅና ዓለምን ለማስተዋወቅ መጠቀም፣ የመሀባቸው ምዕራፎች ውስጥ አንዱን መሞጠል፣ እንዳላወቋቸው ቦታ እንዳልሰጧቸው ከሳቸው ሌላ ጉዳይ እንዳላቸው ገፍላና ውለታ ከሀዲዎች ይህን ታላቅ ክስተት በገፍላ በቸልታ አለመርሳት፣ በሰለዋት በሲራቸው በናፍቆታቸው መጠመድ፣ የውልደታቸውን ገፆች አንድ በአንድ በሸውቅ ማስታወስ ቤተሰቦቻቸውን ሀገራቸውን ደግሞ ከማንበብ አለመጥገብ ነው።
.....ውልደታቸው ዓለም ላይ የፈጠረውን ብርሀን ዳግም እንዲታደስና እንዲያድሰን መፍቀድና ማስተዋል ነው።
ﷺ ﷺ ﷺ
ረቢ
1 048
ولو أني أعيش وياه
وذوق الصحبة والمعشر..
ويبدا يومي من أصحى
قباله، افتح العينين،
ووجهه أول اللي تشوفه
عيني يبتسم ليا
ويسألني عن الليلة..
لأن يدري، كنت تعبان..
حاسس باللي كان بيا..
ويمسحلي على صدري..
ويدعو خالق الأكوان..
وحس بيده حنية..
أشوف التمر ويقللي
كل التمرات، آكلها
سبع تمرات من يده
يقوم ويحلب العنزة
وأتناول لبن منها
يدللني على الراحات
محمد طيب المعشر..
#لو_ألقاه
1 048
#ባሕርይ_መች_ይበላሻል?
ዙኑን አልሚስሪይ (ቁዲሰ ሲረሁ) እንዲህ ይላሉ፦ በባሕርይ ላይ የሚከተሉት ስድስት ነገሮች ሲቀላቀሉ ብልሹነት ይፈጠራል።
አንደኛ፦ ሰዎች በአኺራ ሥራዋቻቸው ላይ በውስጣቸው ደካማ ኒያ ሲገኝባቸው።
ሁለተኛ፦ አካላቸው በብርቱ ስሜታዊ ፍላጎት ተረትቶ ሲያዝ(ሲሸነፉ)።
ሦስት፦ የነገሮችን እውነታ (ፍጻሜን) ከመረዳት ጋር ያለ ረጅም ምኞት ውስጥ ሲጠመዱ፤
አራት፦ ከፈጣሪያቸው ፍቅር የበለጠ በፍጡራን የመወደድ ተጽዕኖዎች ውስጥ ሲወድቁ፤
አምስት፦ የገዛ ዝንባሌያቸውን በመከተል የመልእክተኛውን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ፈለግ ወደ ኀላ ሲተዉ።
ስድስት፦ የቀደሙትን አበዎች (ሰለፎች) ኢምንት ክፍተቶች ለነፍሳቸው ጥፋት እንደማስረጃ በመጠቀም በርካታ መልካም ተግባራቸውን ሲቀብሩ።
***
በዐሪፎቹ ወግ መቀማመጥ በእነርሱ መንፈሳዊ ልምምዶች መጃሊሶችን ማብዛት አንድም ከአድካሚዋ ሕይወት ማገገሚያ ስልት ነው። ሌላ ጎንዮሽ ፋይዳው ደግሞ የነፍስን እንከን ማወቂያ ስልት ነው። ዘላለማዊ ስለኾኑት አኺራዊ ጉዳዮች ደጋግመን ካልተዋወስን ደጋግሞ ወደ ውስጣችን በሚገቡት ሐሳቦች እንጠመዳለን። መጃሊሶች፣ የዒልም፣የዚክር፣የሰለዋት ሐለቃዎች ኹሉ ለዚህ ቀውሳችን ሕክምና ነው።
ምሽቱ ኸሚስ ነው ♥
በሰለዋት ለሊቱን እናሳምረው ♥
አላህ ያስረዳን ♥
1 048
🤍ኢማሙ ነወዊ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ይህንን ብለዋል:
”واعلم أن أحوال رسول الله ﷺ وسيره وما أكرمه الله تعالى به وما أفاضه على العالمين من آثاره ﷺ غير محصورة ولا يمكن استقصاؤها“
(🤍የነብያችን ﷺ ሁኔታዎች እና ታሪካቸው ፥ አሏህ በሳቸው ላይ የዋለው ፀጋ ፥ በተሰጣቸው ልግስና ( አለሙን በሙሉ ያጣቀሙበት የማይዘለቅ ስጦታቸው) ፥ በርሳቸው ﷺ ፋናዎች (በአለም ሁሉ) ያሳደሩት (ተፅኖ ) በሙሉ ተቆጥረው የማያልቁ እና የማይዘለቁ ናቸው።
ምንጭ :-ተሕዚቡል አስማኢ ወሉጋ📚
🌷اللَّهُمَّ صَلِّ عَلىٰ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ ، عَدَدَ مَافِي عِلْمِ اللهِ ، صَلاةً دَائِمَةً بِدَوَامِ مُلْكِ اللهِ🌷
1 048
ያሰቡሁ ያቁዱሱ ያረበል መላዒከቲ ወሩህ❤️
ያሰቡሁ ያቁዱሱ ያረበል መላዒከቲ ወሩህ❤️
ያሰቡሁ ያቁዱሱ ያረበል መላዒከቲ ወሩህ❤️
1 048
مَا وَدَّعَكَ رَبُّكَ وَمَا قَلَىٰ
ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም 93:3 አላህ ይጠላኛል ረስቶኛል አትበሉ ይህን ቃል አስቡ ቀጥሎም ምን አለን
ولسوف يعَطِيكَ رَبُّكَ فَتَرَضَى
ጌታህም ወዷ ፊት(ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል።
ትደሰታለህም 93:5 ይህን ተብለን ሳለማዘን ተስፋ መቁረጥ የለም ዉዶቼ
1 048
እንኳን ለ 1500ኛዉ ለታላቁ ነብዩ ሙሀመድ መዉሊድ በሰላም አደረሳቹ እያልን በአንዋር መስጅድ የፊታችን ጁመዐ የመዉሊድ መቀበያ ሰለዋት ይቀራል 🥹
የሠይዳችንን (ﷺ) ተግባራትና ስነምግባራት ለማግኘት አይቻልም በጥብቅ አትኩሮት ቢሆን እንጂ፤ በአትኩሮት ላይ መድረስ አይቻልም እርሳቸውን አጋንኖ በማፍቀር እንጂ፤ ፍቅራቸው ላይ ሊደረስ አይቻልም በርሳቸው ላይ በብዛት ሶለዋት በማውረድ ቢሆን እንጂ!"
የሰፈር ወር የረቢዑ ዋዜማ ከሁለት ቀናቶች በፊት አሀዱ ብሏል። ለሰው ልጆች እንደ አዲስ ውልደት ሊቆጠር የሚችል ሁለንተናዊ ለውጥ ያመጡት ታላቁ ሰው (ﷺ) ወደዚህች ዓለም የዘለቁበት ዋዜማዊ ወር ነዉ። እኛ ሀበሾች በአሳዳጊያችን በኡሙ አይመን ተወክለን ያን ታላቅ ሁነት የታደምን ከመሆኑ አኳያ ልዩ ትርጉም ይሰጠናል። የራህመት ንፋስ የጀመረበት ወር ነዉ።
ይህ የሰፈር ወር የዒዶቹ ዒድ ረቢዕ ከመድረሱ ከወር በፊት ታላቁ አንዋር መስጅድ እንደከዚህ ቀደሙ የኑሩን መወለድ አስቀድሞ ዜና ያበስራል። ዛፍ ቅጠሉ ይወዛወዛል ሽታው ከአምበር የሚበልጠው ሠው ሥም ሲጠራ ሉባንጃው በትልቅ ማጨሻ ይንቧለቃል። ጊቢው በሶለዋትና በሙሐባ ይታጠናል። ልክ ጀበሉል ኡሑድ ነቢ ሲቆሙበት እንደተነቃነቀው የአንዋር ሚንበሩም ሚህራቡም አውጋሩም አውታሩም ሶለሏህ ዓላ ሙሐመድ እያለ ይዋልላል።
عليك الصلاة والسلام.
ሁላቹሁም ተጋብዛቹሀል
የታላቁ አንዋር መስጂድ ወጣት ጀመዓ
1 048
የኡመት ሙሐመድ ጉዳይ ትካዜና ቁጭት ይፈጥራል። ዐለም ላይ ስላሉ ሙስሊሞች ማሰብ ይከብዳል። በመካከለኛው ምስራቅ፣ በገዛ፣ በየመን፣በሶሪያ የተረጋጋ ነገር የለም። በአንጻራዊ መረጋጋትና አማን ላይ ያለችውም ሐገራችን ከባድ ዱዓ ትፈልጋለች። በየዕለቱ ስለጦርነት እየሰማን ማደር ምቾት ይነሳል። ስለ ኹሉም ወደ አላህ እየተዋደቁ እርሱኑ እየተማጸኑ መለመን ይበጃል። ዱዓ አትራፊ ልብን ያስገኛል። ዱዓ ወደርሱ ያለን ባርነት ያጸናል። በሰደቃው፣ በለይሉ፣ በመውሊዱ እየተሰባሰቡ ችክ ብሎ ለሐገር፣ ለወገን፣ ለዓለም ኡማ ደጋግሞ መጸለይ የሚገባን ወቅት ነው።
ጘፍላውን አላህ ያንሳልን ♥
ወደርሱ መመላለስን፣ በእርሱ መወከልን ይረዝቀና ♥
አልላሁመ ኢንሱር ኡመተ ሙሐመድ!
አልላሁመ ፈሪጅ ኡመተ ሙሐመድ!
አልለሁመ አስሊሕ ኡመተ ሙሐመድ!
1 048
ሰሞኑን የግብፅ ወጣቶች የሚያደርጉት ቢያጡ የተለያዩ ነገራቶቾን በሀይላንድ እያሸጉ መዳረሻቸው የፍሊስጢን ምድር ይሆን ዘንድ ወደ ባህር ሲጥሉ ነበር ። በጀሊሉ ፍቃድ ኢሄው ለጋዛውያን ደርሶቸው የምስጋና መልዕክት እየላኩ ነው ።
وأخير دعوانا أن الحمد لله رب العالمين 🤲😭❤️
1 048
1 birr ይቅርታ በመጠየቁ ሪፖርት እንዳደረግበት የለጠፍኩትን ፖስት አንስቼዋለሁ።
ይቅርታ ማድረግም ይቅርታ መጠየቅም ትልቅነት ነው።
ከዚህ ድርጊቱ በብዙ እንደተማረም ተስፋ አደርጋለሁ።
አንድ ብር "ንግግሬ ሙስሊሙን ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያን ያስከፋ ስለነበረ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ብሏል።
1 048
'ይቅርታ አልጠይቅም ከፈለጋችሁ አካውንቴን አዘጉት....' እያለ ሲወራጣጠር የነበረው አንድ ብር ከቲክቶክ አካውንቱ ይልቅ አጉል መወጣጠሩን መተው መርጦ ይቅርታ ጠይቋል። እንደ ፊኛ ያለአቅሙ እንዳልተነፋፋ ቀናት እንኳን ሳይቆይ ተንፍሶና በርዶለት ነው የተመለሰው !
በእኛው ርብርብ በሪፖርት የተነሳ መፖሰት ስላልቻለ ስቶሪው ላይ የይቅርታ ቪዲዮዎን አስቀምጧል !
ከስህተቱ በደንብ እንደ ተማረ ለማሳየት ደግሞ ከእኛ አልፎ እንደዛ ያበሻቀጣቸውን እኚያ የፍልስጤም እናት ላይቭ ላይ አስገብቶ ይቅርታ ቢጠይቃቸው ከአሁን በተሻለ ጉዳዩ የሚያምር መቋጫ ያገኛል ❤🙌
ሚድያ ላይ 'ይቅርታ መጠየቅ የለበትም...' እያላችሁ ስታስተባብሉ የነበራችሁ ሰዎች የይቅርታውን ቪዲዮ ስታዩ እናንተም ምን ያህል ወርዳቹ እንደነበር በደንብ ግልፅ ይሆንላችኋል !
