cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Event Addis/ሁነት አዲስ

ለአስተያየት : @Tmanaye https://eventaddis.com (Website)

Show more
Advertising posts
6 558
Subscribers
+2724 hours
+1477 days
+73230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የአባቶች ቀን ልዩ ውድድር ዘንድሮ በኢትዮጵያ ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ አባቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ልጆች ለአባታቸው ያላቸውን ክብርና ምስጋና በምን መልኩ እንደሚገልፁ የሚያሳይ አጭር ቪዲዮ በመቅረጽ የሚካሄድ ነው። ምስሎቹ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በሚያገኙት የእይታና የላይክ መጠን ተመርጠው 1ኛ - ለሚወጣ የምስክር ወረቀት፣ ጋቢና ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ፡፡ 2ኛ - ለሚወጣ ጋቢና ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ፡፡ እንዲሁም 3ኛ ለሚወጣ ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ ላይ የሚታደሙ ይታደማሉ። ተወዳዳሪዎች ቪዲዮዎቻቸውን ከታች በሚገኘው በኢትዮጵያ አባቶች ቀን በጎ አድራጎት ድርጅት ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ መልዕክት መላኪያ ላይ ያስቀመጡ። https://www.facebook.com/profile.php?id=100064190287928&mibextid=ZbWKwL ፕሮግራሙ ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በዮድ አቢሲያ የባህል አዳራሽ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይከናወናል።
Show all...
የአባቶች ቀን ልዩ ውድድር ዘንድሮ በኢትዮጵያ ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ አባቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ልጆች ለአባታቸው ያላቸውን ክብርና ምስጋና በምን መልኩ እንደሚገልፁ የሚያሳይ አጭር ቪዲዮ በመቅረጽ የሚካሄድ ነው። ምስሎቹ እስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በሚያገኙት የእይታና የላይክ መጠን ተመርጠው 1ኛ - ለሚወጣ የምስክር ወረቀት፣ ጋቢና ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ፡፡ 2ኛ - ለሚወጣ ጋቢና ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ፡፡ እንዲሁም 3ኛ ለሚወጣ ከውዱ አባብዬ ጋር በዮድ አቢሲኒያ ልዩ የምሳ ግብዣ ላይ የሚታደሙ ይታደማሉ። ተወዳዳሪዎች ቪዲዮዎቻቸውን ከታች በሚገኘው በኢትዮጵያ አባቶች ቀን በጎ አድራጎት ድርጅት ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ መልዕክት መላኪያ ላይ ያስቀመጡ። https://www.facebook.com/profile.php?id=100064190287928&mibextid=ZbWKwL ፕሮግራሙ ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በዮድ አቢሲያ የባህል አዳራሽ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይከናወናል።
Show all...
ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ በቅርቡ ለአድማጮች ያደረሰው "ቢሊሌ" ሙዚቃ ላይ የተጠቀሰችው "ቢሊሌ" ማናት ? መህቡባ/ቢሊሌ በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው ጉማ እ.ኤ.አ. በ1820 ስትወለድ ቤተሰቦቿ "ቢሊሌ" የሚል ስም አውጥተውላት ነበር። ትርጉሙም "ቆንጆ" "የምታምር" እንደማለት ነው። መህቡባ ማለት ደግሞ በአረብኛ "ተወዳጇ" ማለት ነው። መህቡባ እድሜዋ 15 ዓመት ሲሞላት እ.ኤ.አ. በ1835/36 በተነሳ የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት አባቷንና ስድስት ወንድሞቿን  አጣች። በ1837 በለጋነት እድሜዋ በእሳት ቃጠሎ ከወደመው የትውልድ መንደሯ በባሪያ ፈንጋዮች ተፈንግላ ከእህቷ ጋር ተቆራኝታ ወደ ጎንደር ከተወሰደች በኋላ ለሽያጭ ልትቀርብ በሱዳን ካርቱም አድርጋ ወደ ካይሮ አቀናች። በ1837 የጀርመኑ ልዑል ኸርማን ፉርስት ቮን ፐክለር-ሙስካው ወደ ሰሜን አፍሪካ ጉዞ አድርጎ ነበር። በካይሮ ቆይታው የቱሪስቶች ተወዳጅ ስፍራ ወደሆነው የካይሮ የባሪያ ገበያ ቦታ ይሄዳል። በእዛም በባርነት ለሽያጭ በቀረበች አንዲት ጉብል የኦሮሞ ልጅ ውበት ይማረካል። ወዲያው ተደራድሮ ከገዛት በኋላ አገልጋዬ ናት በማለት ዋሽቶ ከእራሱ ጋር አብራው እንድትጓዝ አደረገ። ልዑሉ በመህቡባ ፍቅር ተንበረከከ። ልዑሉና መህቡባ ወደ ፍልስጥኤም፣ ሶርያ እና ኢስታንቡል አብረው ተጉዘዋል። ልዑሉ ተፈጥሮ ለመህቡባ በለገሰቻት ሞገስና የአውሮፓውያንን ባህል ለመልመድ በምታሳየው ፍላጎት ተደምሞ ነበር። እሷም ባልጠበቀችው አዲስና ያልታሰበ ሁኔታ ደስተኛ ሆና ነበር። አውሮፓ እንደደረሱ ለተወሰነ ጊዜ በቡዳፔስት ቆይታ አድርገው ነበር። በእዛም መህቡባ የቅዱስ ጥምቀት ስነስርዓት እከናውናለች። ልዑሉም መህቡባን ለተወሰነ ጊዜ በቪየና ወደሚገኝ ጥሩ ትምህርት ቤት አስገብቷት የትምህርት ቤቱን መነኩሴዎች አውሮፓዊ አኗኗርን እንዲያስተምሯት ነገራቸው። እሷም ተፈጥሮ በሰጠቻት ፀጋና ንቃት በትምህርቷ በመጎበዝ ሁሉንም አስደስታለች። የገባችበት ሁሉ አካባቢውን በፈገግታዋ ታደምቅ ነበር። ለቋንቋ የተሰጠች ስለነበረች ጣሊያንኛ በቶሎ ለመደች። አብረዋት ሊሆኑ የሚወዷትና በተፈጥሮ ገርና ደግ ነበረች። ማህበረሰቡም የልዑሉንና የልዕልቷን ግንኙነት በቅንነት ተቀብሎ የመህቡባ አስደናቂ ውበት ያደንቅ ጀመረ። የቪየና ጣእም ሆነች፣ ጋዜጦችም ስለሷ አድንቀው ይፅፉ ነበር። የወሬ ሁሉ ማድመቂያም ሆነች። ወደ ንጉሱ ዙፋን በተወሰደች ጊዜም ይሁንታንና ግርማ ሞገስን አገኘች። ሁሉም ሰው ወደዳት። ይሁን እንጂ መህቡባ ምግቡንና ቀዝቃዛውን የአውሮፓ አየር መልመድ አቃታት። በጊዜ ሂደትም በሳንባ ምች ተይዛ በፅኑ ታመመች። ልዑሉ  መህቡባን ለሚንከባከበው ሃኪም ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግላትና ስለ እርሷም እንዲያሳውቀው አዝዞት ለሥራ ወደ በርሊን ተጓዘ። ከሁለት ቀናት ቆይታ በኋላ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 27 ቀን 1840 የመህቡባ አገልጋይ የመህቡባን መኝታ ክፍል መጋረጃ ስትገልጥ መህቡባን ሞታ አገኘቻት። ብቻዋን ሞታ ተገኘች። በትልቁ አልጋ ላይ እንደ ትንሽ ምስል ትታይ ነበር። በአቅራቢያው በሚገኝ መካነ መቃብርም ተቀበረች። በመቃብሯም ላይ "መህቡባ" ብቻ የሚል ፅሁፍ ያለው ምልክት ተደረገላት። መካነ መቃብሯን በየአመቱ ሺህዎች ይጎበኙታል። ልዑሉ ስለ መህቡባ ሞት ለጓደኛው በፃፈው ደብዳቤ "ሰው መውደድ እችላለሁ ብዬ ከማስበው በላይ ወድጃት ነበር። ሞቷም ጥልቅ ስቃይ ውስጥ ከትቶኛል። እርሷ ለእኔ ሁሉ ነገሬ ነበረች" በማለት መሪር ሃዘኑን ገልጿል። #Event_Adddis
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
"የአዲስ አበባ ሰፈር ፣ እድር ፣ እና ግቢ" ውይይት በዶ/ር አንተነህ ተስፋዬ የተዘጋጀው "ሰፈር፣ እድር እና ግቢ" የተሰኘው መጽሀፍ  የኢትዮጵያን የከተማ ኑሮ፣ ስፍራ የማበጀት እና የንድፍን ንድፈ ሀሳብ  የሚያሳይ መጽሀፍ ነው። በዚህ በዶ/ር አንተነህ ተስፋዬ መጽሀፍ ሀሳብ ላይ ነገ ሐሙስ ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 እስከ 10፡30 ድረስ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ዋናው ግቢ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ውይይት ይካሄዳል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
ሮፍናን ኑሪ የክብር የእንግዳ የሆነበት አንጋፋው የኪነጥበብ ምሽት ዛሬ ይካሄዳል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የሚዘጋጀው የኪነጥበብ መርሃግብር ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 14 2016 ዓ.ም ይካሄዳል። በዕለቱ ሮፍናን ኑሪ "የአንድ ግጥም፣ የአንድ ወግ" የክብር እንግዳ ሆኖ  ይገኛል። እንዲሁም ግጥሞች፣ ወግ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ተሰናድተው እናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ11: 30 ጀምሮ ይጠብቃችኃል ብለዋል አዘጋጆቹ ። ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...
"መስተዋድድ" የኪነጥበብ ምሽት ዛሬ ይካሄዳል "መስተዋድድ" የኪነጥበብ ዝግጅት ዛሬ ግንቦት 14 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ ሜክሲኮ በሚገኘው ገነት ውስጥ ይካሄዳል። በዕለቱም ገጣሚያኑ ሚካኤል ምናሴ ፣ ሂክማ ፋንቱ ፣ዘውድ አክሊል ከሚሎ ባንድ ጋር በመሆን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። በተጨማሪም ደራሲ ገብረክርስቶስ ደስታ፣ ሔኖክ ስዩም ፣ ሰመረ ባሪያው ፣መሐመድ ካሣ እና ካሣዬ ጨመዳ ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
"አልፅፍም"መጽሐፍ ለንባብ በቃ የአይዳ ታደሰ " አልፅፍም" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ባሳለፍነው ቅዳሜ ለንባብ በቅቷል። የግጥም መጽሐፉ በ200 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን የቀረበ ሲሆን በዓይናለም መጻሕፍት መደብር ውስጥ ይገኛል ተብሏል። አይዳ ታደሰ ከዓመታት በፊት ገጣሚያኑ በረከት በላይነህ ፣ አበባው መላኩ ፣ ቸርነት ወ/ገብርኤል እና ሌሎችም የተሳተፉበት "ቃል እና ቀለም" የተሰኘ ፊልም ለተመልካች ማድረሷ ይታወሳል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የዓለማየሁ ደመቀ "ዮቶር 2" መጽሐፍ ለንባብ በቃ የደራሲ ዓለማየሁ ደመቀ " ዮቶር 2" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ  ግንቦት 12 2016 ዓ.ም ለንባብ በቅቷል። በ207 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ450 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል። የመጽሐፉ መታሰቢያነትም ለአንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ የተሰጠ ሲሆን ደራሲው በመግቢያው "ለታላቁ የኢትዮጵያ ሙዚቃ አድባር ፣እኔንም ሆነ የጥበቡን ቤተሰቦች በሥራዎችህ ውስጥ ላስተማርከን ፣ በግንባርም ለመገብከን ዕውቀት እናመሰግናለን" በማለት ምስጋናውን አቅርቧል። መጽሐፉ ጃፋር መጻሕፍት መደብርን ጨምሮ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል። ከዚህ ቀደም በደራሲ አለማየሁ ደመቀ የተጻፈው "ዮቶር ኮባላይ ካህን" 14ተኛ ዕትም መጽሐፍ በድጋሚ ለአንባቢያን መቅረቡ ይታወሳል። በተጨማሪም አለማየሁ ደመቀ ለበርካታ ድምጻዊያን የግጥም እና ዜማ ስራዎችን ሰርቷል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የመጋቢ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ "37 አልፋ ገ3" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ በሚቀጥለው ሳምንት ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል። መጋቢ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው " [37 አልፋ 73] በሚቀጥለው ሳምንት ለአንባብያን ይቀርባል።" ስለ ይዘቱም "ቀደምት ሊቃውንት የተጠበቡበት ጥበብ እጆ ይደርሳል። ከጽርሐ አርያም እስከ DNA፤ ከኢዮር እስከ አሚኖ አሲድ፤ ከአድማስ እስከ ፔርዮዲክ ቴብል፤ ከመላእክት ስም እስከ ኖኅ መርከብ ሙሉ ዕውቀት ይዟል።" ብለዋል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
Show all...