en
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Open in Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Show more
3 585
Subscribers
-124 hours
-57 days
+5330 days
Posts Archive
🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱 Red brick:- This is the classic brick color that you see Quality with affordable price 🧱ጥራ
🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱 Red brick:- This is the classic brick color that you see Quality with affordable price 🧱ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ ጡቦችን እናመርታለን። 🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣ 🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣ 🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣ 🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣ 🧱  ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣ 🧱 ለx-ray ክፍሎች፣ 🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣ 🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣ 🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣ 🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣ 🧱 ለአበባ መትከያ 🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣ 🧱 ለፒዛ ኦቭን፣ 🧱 ለምድጃ፣ 🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ፣    NEW POINT BRICK FACTORY *We produced best quality clay bricks for various construction purposes. 🧱 For building construction, 🧱 For bank vaults, 🧱 Fence for the yard, 🧱 For road edges, 🧱 For Hotels,Restaurants,and Cafes decoration, 🧱 For x-ray rooms, 🧱 For manuals, 🧱 For kitchen, 🧱 For shower tray 🧱 To cover PBC drains, 🧱 For garden, 🧱 Furnace For steel factory, 🧱 For pizza oven, 🧱 For waste incinerator, 🧱 For more information join our telegram channel 🧱Order now 📲0912854327,0902378888 🧱"Quality is our first priority 🧱Thank you 谢谢

የግሩፑ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ግንባታ የድምድማት ፕሮግራም ተካሄደ ♦️የኤርፖርቱን ከተማ ቻይናዎች ሳይገነቡት አይቀርም ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ላለፉት ሁለት አመታት በቻይናው China Civil Enginee
+2
የግሩፑ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ግንባታ የድምድማት ፕሮግራም ተካሄደ ♦️የኤርፖርቱን ከተማ ቻይናዎች ሳይገነቡት አይቀርም ▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ላለፉት ሁለት አመታት በቻይናው China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) እየተገነባ ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ የዋናው ሕንፃ የመጨረሻ ከፍታ 45 ሜትር ላይ መድረሱን የቻይና ሚዲያዎች እየዘገቡት ነው።
የግንባታው ፕሮጀክት ከ33,560 ካሬ ሜትር በላይ በሆነ የመሬት ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ በጠቅላላው ስድስት የተለያዩ ሕንፃዎችን ያካተተ ነው። ግንባታው ሙሉ በሙሉ በነሐሴ 2026 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ሰኞ ዕለት በተካሄደው የሕንፃው ድምድማት ፕሮግራም ላይ የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) በቢሾፍቱ የሚገነባው ግዙፍ ኤርፖርት እንዲገነባ ግብዣ ማቅረባቸውን ዤኑዋ ዘግቧል። ▭▭▭ ኢንፍራኮን ሚዲያን ፎሎው እና ሼር ያድርጉ! የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ t.me/infraconmedia

+2
ERA Quality Manual Vol.3 በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ERA) ድህረገጽ ከሚገኙ የጥራት ማንዋል (Quality Manual) መካከል የግዥ ሂደቶች የሚመሩባቸው ስታንዳርድ  ሰነዶች ክፍል አንዱ ሲሆን በጣም ጠቃሚ ናቸው። ለሌሎች የመንግስት ተቋማትና የግል ድርጅቶችም እንደ መነሻ የሚጠቅሙ ጠቃሚ ሰንዶች በመሆናቸው ☝️👇 አጋራናችሁ፤ በተለይ ለግንባታ እና የማማከር አገልግሎት ጨረታዎች Standard Forms, Reports, Checklists, Memos and Letters ተካተውበታል። 📢 Join: @procinsightet 📬 Contact: @Procinsight_bot 👵 Discussion: @procinsightet2

China porcelain ceramic 60x60cm 80x80cm 60x120cm 20x1m 30x60 30x30 available 0911798889
+9
China porcelain ceramic 60x60cm 80x80cm 60x120cm 20x1m 30x60 30x30 available 0911798889

Elegant & Durable PVC Doors ✨ Upgrade your home with stylish PVC doors featuring modern glass designs. Strong, beautiful, and
Elegant & Durable PVC Doors ✨ Upgrade your home with stylish PVC doors featuring modern glass designs. Strong, beautiful, and long-lasting! 📍አድራሻ : ጋዜቦ አደባባይ፣ ከ ሙሌሙል ዳቦ ቤት አጠገብ ለበለጠ መረጃ በዚህ ሰልክ ይደውሉ 📞 0930099145 | 0930099146" ቤትዎን በዘመናዊ እና ቆንጆ የPVC በሮች ያዘምኑ። ጠንካራ፣ ውብ፣ እና የረጅም ጊዜ የሚቆዩ!

የ ስራ ቅጥር ማስታወቂያ | Vacancy ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ በ 11 መስኮች ክፍት የ ስራ ቅጥር ቦታ አውጥቷል 1. የ ህንፃ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ - Bsc with civil e
የ ስራ ቅጥር ማስታወቂያ | Vacancy ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ በ 11 መስኮች ክፍት የ ስራ ቅጥር ቦታ አውጥቷል 1. የ ህንፃ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ - Bsc with civil engineering 20+ year experience 2. ንብረት አስተዳደር 3. ተቆጣጣሪ መሀንዲስ(inspector) - 10+ years experience with Bsc with civil engineering 4. ኳንቲቲ ሰርቬየር- 6+ years experience 5. ጀነራል ፎርማን - 12+ years experience 6. Office engineer- 6+ years experiences በ ሁሉም መስክ ለማመልከት የ ስራ ልምድ (CV) copy ይዛችሁ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ዋና ፅህፈት ቤት አስረክቡ 📍 አድራሻ :- ፍላሚንጎ መስቀል አደባባይ ወደማርዮት ሆቴል መሄጃ ላይ 📞 ስልክ +2511513289 📞 ስልክ +2511512444 ማሳሰቢያ እድሜ ከ55 አመት በታች ለሆናችሁ ብቻ

#CapitalNews ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ከግዢ ዋጋ በላይ የሚሸጡባቸው ሀገራት ኢትዮጵያ እና ስሪላንካ ብቻ መሆናቸው ተገለጸ የተሽከርካሪዎች ዋጋ በዓለም ዙሪያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሲሄድ፣ በ
#CapitalNews ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ከግዢ ዋጋ በላይ የሚሸጡባቸው ሀገራት ኢትዮጵያ እና ስሪላንካ ብቻ መሆናቸው ተገለጸ የተሽከርካሪዎች ዋጋ በዓለም ዙሪያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሲሄድ፣ በኢትዮጵያ እና ስሪላንካ ግን በተቃራኒው ያገለገሉ መኪናዎች ከገዙበት ዋጋ በላይ ይሸጣሉ። እንደ መረጃዎች ከሆነ ሁለቱ ሀገራት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ለዓመታት ከተጠቀሙባቸው በኋላም እንኳ ከገዙበት ዋጋ በላይ የሚሸጡባቸው ብቸኛ ሀገራት ናቸው። የግሎባል ፌዴሬሽን ኦፍ ስሪላንካ ቢዝነስ ካውንስልስ ዋና ጸሐፊ ሳጂቭ ክሻትሪያ ራጃፑትራ እንደተናገሩት ፣ ይህ ሁኔታ ሰዎች በመጨረሻ ጥቅም ላይ የማይውሉ ተሽከርካሪዎችን ለመግዛት ብዙ ገንዘብ እንዲያወጡ እንደሚያደርግ እና በመጨረሻም ብረት ክምር ብቻ እንደሚሆን ገልጸዋል። ይህን ችግር ለመፍታት ስሪላንካ ያረጁ ተሽከርካሪዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ውጭ በመላክ፣ ከሽያጩ የሚያገኘውን ትርፍ ደግሞ የአዲስ ተሽከርካሪዎችን የማስመጣት ግብር ለመቀነስ ልትጠቀምበት እንደምትችል ጠቁመዋል። በአሁኑ ጊዜ ስሪላንካ ተሽከርካሪዎች ላይ እስከ 300 በመቶ ግብር ትጥላለች፣ በአገር ውስጥ ደግሞ ያገለገሉ መኪናዎች ዋጋ ከመጀመሪያው የግዢ ዋጋ እስከ ሦስት እጥፍ ከፍ ሊል እንደሚችል ተጠቁሟል።

▪️የጨረታ ሰነድ ሽያጭ ዛሬ ይጠናቀቃል 👉 የመንግስት ንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ ሰነድ መሽጫ ዛሬ 12/12/17 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ስአት ተጠናቆ ነገ 13/12/17 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰአት ጀ
▪️የጨረታ ሰነድ ሽያጭ ዛሬ ይጠናቀቃል 👉 የመንግስት ንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ ሰነድ መሽጫ ዛሬ 12/12/17 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ስአት ተጠናቆ ነገ 13/12/17 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰአት ጀምሮ ይከፈታል፡፡ 👉 በመሆኑም በጨረታው መክፈቻ ተጫራቹ ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው መሳተፍ የሚችል መሆኑን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ያሳውቃል፡፡

Repost from Emanvictordoors
0912288223 ኢማን ቪክተር_በር 🏠ከውጭ የምናስገባቸው በሮቻችን የብረት በሮች ሲሆኑ በተለያየ አይነት ከለር እና አስታይል የተሰሩ ናቸው። 🏠 በጣም ዘመናዊና ለየት ያሉ ናቸው 🏠የምንጠቀመው
+5
0912288223 ኢማን ቪክተር_በር 🏠ከውጭ የምናስገባቸው በሮቻችን የብረት በሮች ሲሆኑ በተለያየ አይነት ከለር እና አስታይል የተሰሩ ናቸው። 🏠 በጣም ዘመናዊና ለየት ያሉ ናቸው 🏠የምንጠቀመው የቀለም ቅብ (Oven Painting System) ሲሆን ውበታቸውንና ጥንካሬያቸውን ይገልፀዋል 🏠ከስድስት እስከ ዘጠኝ ተወርዋሪ ቁልፎች(ማስተር ኪስ)አሉት 🏠ድምጽ የማያሳልፍ(Sound Proof)እንዲሁም እርጥበት የማያበላሸው(Water Proof) ነው 🏠አሳትን የመቆቆም አቅሙ ከፍተኛ ነው(High Fire Resistance) 🏠የሚታጠብ እና የሚወልወል 🏠የብረት በር ግን የእንጨት መልክ ያለው ይደውሉ ☎️ 0912288223 Victor Door 🔒👉ስሪቱ የብረት ሲሆን እጅግ ጠንካራና ባህሪው (Character) ግን የእንጨት ነው ማለትም በእጅ ሲነካ ወይም ሲመታ የሚያሰማው ድምፅም ሆነ አጠቃላይ ገፅታቸው የእንጨትን ባህሪ የያዘ ነው። 🔑👉ድምፅ የማያሳልፋ(Sound-proof) እንዲሁም የትኛውም አይነት እርጥበት የማያበላሻቸው(Water-proof) ናቸው። 🔑👉ከዉስጥ ወደ ውጪ የሚያሳይ ካሜራና የመጥሪያ ደውል  የተገጠመላቸው ናቸው። 🔑 ከ9-12 ተወርዋሪ ቁልፎች ያሉት 👉ውበታቸውን የሚያጎላ ራሱን የቻለ ሞስትራ(ጌጦች) አሏቸው። 👉ተቀጣጣይ ነገሮችን ወይም እሳትን የመቋቋም አቅም(Fire-resistance) አላቸው። ከ 2 ሰዓት በላይ 200c⁰-250c እሳትን መቋቋም የሚችል ☎️ ለበለጠ መረጃ: Eman #contact us 091228822https://t.me/Emanvictordoors

ኮንስትራክሽኑ በአዲስ አተያይ እየመጣ ነው ለግንባታ ግብዓቶች ግዥ በአመት 1.2 ቢሊዮን ዶላር ይወጣል ♦️♦️♦️ የኢትዮጵያ መንግስት ባስቀመጠው አዲስ አቅጣጫ መሰረት በመጪው ጊዜ፡- ጥራት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው መለያ መሆን እንዳለበት ሰሞኑን ይፋ በተደረገ ሰነድ ላይ ተጠቁሟል፡፡ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒሰቴር ለሚቀጥሉት 25 አመታት የሚተገበር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሸቲቭ ፕሮግራምን ጋር ተያይዞ አዲስ ይፋ በተደረገው የ25 አመት ፍኖተ ካርታ ውስጥ፣ ግንባታዎች በዕይታ ረገድ ውበትን የተላበሱ፣ ከአገልግሎት አንጻር በጊዜ ተፈትነው የሚያልፉና ትውልድን የሚሻገሩ፣ የአካባቢ ጥበቃ እና ማኀበራዊ ጉዳዮችን የሚያከብሩ፣ ደህንነታቸው የተረጋገጡ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ እና ሁሉንም የኀብረተሰብ ክፍሎች የሚያገለግሉ ሊሆኑ እንደሚገባ ያትታል፡፡
በከተማና መሰረተ ልማት ሚንስቴር "መደመር በኮንስትራክሽን" በሚል ርዕስ ይፋ የተደረገው ሰነድ እንደሚጠቁመው፡- ከዚህ በፊት ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የ30 ዓመት ፍኖተ ካርታ፣ የ10 ዓመት የዘርፍ እቅድ እና የ3 ዓመት የመካከለኛ ዘመን እቅድን ጨምሮ በዘርፉ እንዲሳኩ የሚጠበቁ የተለያዩ ግቦችን ያካተቱ ሰነዶች ተዘጋልተውየነበሩ መሆኑን ገልፆ፣ እነዚህ ሰነዶች ኢንዱስትሪው የደረሰበትን የእድገት ደረጃ፣ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ እና እያጋጠመው የሚገኘውን ተግዳሮቶች በመለየት፣ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማመላከት እንዲሁም ዝርዝር ፕሮግራሞችን እና ፕሮጀክቶችን በማመላከት በኩል የማይተካ ሚና ቢጫወቱም፣ በዘርፉ የተለያየ ሚና እና ድርሻ ያላቸው አካላት ግልጽ የጋራ ግብ ኖሯቸው ይህን የጋራ ግብ ለማሳካት በቅንጅት እና በትብብር ሲሰሩ አይስተዋልም ብሏል።
በፕሮጀክት ትግበራም ሆነ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ጤናማነት፣ ተወዳዳሪነትና እድገት መንግስት የማይተካ ሚና እንዳለው አበክሮ የገለጸው ሰነዱ፡- በፌደራል፣ በክልል፣ በዞን፣ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ በተዋረድ የሚገኙ የአስተዳደርና የመንግስት አስፈጻሚ አካላት በኩል ከፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች አፈጻጸም አኳያ የጎንዮሽ እና የተዋረድ አለመናበብ፣ አለመቀናጀት እና አለመተባበር በግልጽ የማይታይ ሆኖም ከፍተኛ ጉዳት እና ኪሳራ እያደረሰ የሚገኝ ጉዳይ ነው። በተለይም በፌደራል ደረጃ የሚያዙ የመሰረተ ልማት እና ሌሎች የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶችን በሁሉም ደረጃ ያሉ የመንግስት አካላት ፕሮጀክቶቹን እንደ ሀገራዊ ፕሮጀክት በመውሰድ የሚያሳዩት ትብብር እና ድጋፍ በአብዛኛው ዝቅተኛ ነው በማለት አስቀምጦታል።
በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የእጥረት አስተሳሰብ ጉልህ ሳንካ መሆኑን የገለጸው "መደመር በኮንስትራክሽን" ሰነድ፣ ኢትዮጵያ ትልቅም፣ ብዙ ፀጋዎች ያሏትም ሀገር ብትሆንም፣ ያለመታደል ሆኖ፣ አስተሳሰባችን እያለን እንደሌለን፣ እየቻልን እንደማንችል ነው በማለት ያትታል።
የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የዚህ የእጥረት አስተሳሰብ ቀጥተኛ ተጎጂ ነው የሚለው ሰነዱ፣ በተለይም ለተለያዩ ግንባታዎችም ሆነ የመሰረተልማት ዝርጋታዎች መሬት እና የተፈጥሮ የግንባታ ግብአቶች (ድንጋይ፣ አሸዋ፣ እንጨት፣ የተመረጠ አፈር፣ ወዘተ.) ማግኘት አዳጋች መሆኑ ብቻ ሳይሆን በዚሁ ምክንያት የሚከፈለው ክፍያ እጅግ የተጋነነ መሆኑ ተፈጥሯዊ ያልሆነ እና የእጥረት አስተሳሰብ የፈጠረው ነው። ይህ ጉዳይ በፖሊሲ እና በህግ ተደግፎ በሚሰራ ሥራ መስመር እንዲይዝ ካልተደረገ እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የመሰረተ ልማት እና ሌሎች ግንባታዎች ጉድለት ባለበት ሀገር የህዝቡንም ሆነ የሀገር የመልማት ፍላጎት ማሟላት ፈታኝ ነው።
ሌላው የኢንደስትሪው ሳንካ ተብሎ የተገለጸው፡- "ግድ ማጣት እና አላካኪነት" ነው ያለው መረጃው በዚንዱስትሪው ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣ ሲሆን፣ የተለያዩ አካላት መሆን ያለበት ነገር ሳይሆን ሲቀር፣ ወይም መሆን የሌለበት ነገር ሲሆን በ"ምን አገባኝነት እና በምኔ ይነካል" ስሜት ችላ ሲሉት ይስተዋላል በማለት ተችቷል። 
ይህ ጉዳይ በተለይ በፌደራል ደረጃ በሚሰሩ የመሰረተልማት ፕሮጀክቶች አካባቢ ጎልቶ የሚታይ እና ፕሮጀክቶች በአብዛኛው በቀላሉ ሊፈቱ በሚችሉ ምክንያቶች አፈጻጸማቸው ሲጓተት እና ሀገር ላይ ትልቅ ኪሳራ ሲያደርሱ እያዩ እምብዛም ግድ የማይሰጣቸው፤ ችግሮችን ተቀናጅቶ በጋራ ከመፍታት ይልቅ ማላከክ የሚቀናቸው የወረዳ፣ የከተማ፣ የክልል እና የፌደራል አካላት በርካታ ናቸው፡፡ የዚህ ችግር ምንጭ ኃላፊነትን በሥራ መደብ እና በተቋም አጥር ውስጥ ብቻ ገድቦ መያዝ፣ የሀገራዊ ስሜት መሸርሸር እና ከልክ ያለፈ ግድየለሽነት በማለት ሰነዱ ላይ ሰፍሯል፡፡
የሀገር ውስጥ የግንባታ ግብአቶችን በተገቢው መንገድ ካለመጠቀም ጋር በተያያዘ በሰነዱ ላይ እንደሰፈረው፣ ሀገራችን ብዙ የተፈጥሮ ሀብቶች ቢኖሯትም፣ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በአብዛኛው ከውጭ ሀገር በሚገቡ ግብዓቶች እና በውጭ ሀገር የሚመረቱ የግንባታ እቃዎች ላይ ጥገኛ ነው። በተለይም እንደ ብረት፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች፣ ቀለም፣ ግራናይት፣ ሴራሚክ እና ሌሎች የግንባታ ማጠናቀቂያ እቃዎችን በስፋት ከውጭ ለማምጣት በየዓመቱ እስከ 1.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ይደረጋል፡፡
ይህ ጥገኛነት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ክምችት የሚጎዳ ከመሆኑ ባሻገር የአገር ውስጥ አምራቾችን አቅምና ተወዳዳሪነት እና ሰፊ የሥራ ዕድል የመፍጠር እድልን በማዳከም ኢኮኖሚውን በዘላቂነት ይጎዳል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሀገራችን ውስጥ በብዛት የሚገኙ የግንባታ ማቴሪያሎችን (ቀርከሃ/ባምቡ፣ እንጨት እና እንደ ጣውላ ያሉ የእንጨት ውጤቶች፣ ድንጋይ፣ አፈር፣ የተለያዩ ተረፈ ምርቶች፣ ወ.ዘ.ተ.) በማውጣት ለቤቶች እና የተለያዩ መሠረተ ልማት ስራዎች በአግባቡ እና በስፋት መጠቀም የሚቻል ቢሆንም በዚህ ረገድ በተግባር የሚታየው እውነታ ውስን እንዲሁም በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ፣ በቀላል ማሽነሪዎች እና በውጤታማ የግንባታ ስልቶች የታገዘ አይደለም። በሀገር በቀል የግንባታ እውቀት እና ዘዴዎች ላይ የተወሰኑ በቀላል ማሸነሪዎች የታገዙ ሥራዎችን በማከል፣ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን ሥራ ፈጣሪዎች በማበረታታት እና የገበያ ትስስር በመፍጠር በየአካባቢው ያሉ ጸጋዎችን ወደ ሀብት መቀየር እንዲሁም በተጨባጭ መሬት ላይ ያሉ የህብረተሰብ ችግሮችን ማቃለል፣ የተሻለ የኑሮ ሁኔታ መፍጠር ይቻላል ቀማለት ሰነዱ አብራርቷል።

🔺ታምራት ፕሌት እና ጄቦልት አቅራቢ🏗 📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን ✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና ማጠፊያ ማሽኖች አሉን 🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን
🔺ታምራት ፕሌት እና ጄቦልት አቅራቢ🏗 📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን ✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና  ማጠፊያ ማሽኖች አሉን 🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን 📐ማንኛዉንም የሞደፊክ ስራዎችን እንሰራለን 📍ኢትዮጵያ ዉስጥ የትም እንልክሎታለን! ➕➕➕➕➕➕➕➕➕ 📍አድራሻችን፦ ቁ.1 አዉቶብስ ተራ(መሳለሚያ)                     ቁ.2 መርካቶ                     ቁ.3 ተክለሀይማኖት 📞0904040477 📞0911016833

🚚ሲኖትራክ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ስለተሰጠው ክልከላ ማብራሪያ ይመለከታል

የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበ #Ethiopia | በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የሆነውን የግብር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት፣
የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበ #Ethiopia | በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የሆነውን የግብር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት፣ የሀገሪቱ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔን ከ15% ወደ 17.5% እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ መቅረቡ ታወቀ። ይህንን የግብር ምጣኔ ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የግብር ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ሊያሳድግ እንደሚችል ተነግሯል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና የፊስካል ጥናት ተቋም (IFS) በጋራ ባዘጋጁት አዲስ ጥናት፣ የኢትዮጵያ የ15% የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ከብዙ የምስራቅ አፍሪካ እና የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት ምጣኔዎች ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ ነው። ለምሳሌ፣ የኬንያ የ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔ 16% ሲሆን፣ የሩዋንዳና የዩጋንዳ ደግሞ 18% ነው። የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት አማካይ ምጣኔም 17.5% መሆኑን አመልክቷል ሲል ካፒታል ጋዜጣ አሰነብቧል። ሌላ ትኩሳት 🥺😔🤯🤥

የሲኖትራክ ተሽከርካሪ የጥራት ጉድለት ሳይሻሻል ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል - የጉምሩክ ኮሚሽን ********* የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ያለበትን የጥራት እና የቴክኒክ ችግር እስኪያሻሽል ድረስ
የሲኖትራክ ተሽከርካሪ የጥራት ጉድለት ሳይሻሻል ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል - የጉምሩክ ኮሚሽን ********* የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ያለበትን የጥራት እና የቴክኒክ ችግር እስኪያሻሽል ድረስ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል። የጥራት ጉድለቱ በየጊዜው የሰው ሕይወት ብሎም ንብረት እንዲጠፋ ምክንያት በመሆኑ፤ አምራች ድርጅቱ ማሻሻያ እስከሚያደርግ ድረስ ተሸከርካሪው ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መከልከሉን ነው የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ዘሪሁን አሰፋ ለኢቢሲ ዶትስትሪም የተናገሩት። ክልከላው ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉንም ገልፀዋል። በዚህም ከተጠቀሰው ዕለት ጀምሮ ምንም ዓይነት የማስገቢያ ፈቃድ እንዳልተሰጠ አረጋግጠዋል። Source: EBC

👉🏢በአዲስ አበባ ብቻ 141 ሰዎች በሕንፃ ግንባታ ሥራ ላይ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ 🚧 ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በተሰራ ጥናት መሠረት በሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ 141
👉🏢በአዲስ አበባ ብቻ 141 ሰዎች በሕንፃ ግንባታ ሥራ ላይ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ 🚧 ከ2015 እስከ 2017 በጀት ዓመት በተሰራ ጥናት መሠረት በሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ 141 ሰዎች በሕንጻ  የግንባታ ሥራ ላይ በደረሰ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉን የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ለአሐዱ አስታውቋል። 👉 ሕይወታቸውን ያጡ ዜጎች በሁሉም የእድሜ ክልልና ፆታ የሚገኙ መሆናቸውን የገለጹት የባለስልጣን መስሪያቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አበበ እሸቱ ናቸው። ▪️በተደረገው ጥናት መሠረት የሞታቸው መንስኤ ተብለው የተለዩት፤ የመጀመሪያው ጥንቃቄ ባልተሞላበት መንገድ የደህንነት ቀበቶ፣ ጫማ እና ኮፍያ የመሳሰሉትን ሳያደርጉ ሲሰሩ የነበሩ ሠራተኞች ከከፍታ ላይ መውደቃቸው ስለመሆኑ ተናግረዋል። ከዚህ ሌላም በግንባታው ቦታ ላይ በሚያጋጥም የኤሌክትሪክ አደጋ ሲሆን፤ የተላጠ ኤሌክትሪክ በሚይዙበት ወቅት ወይም መብራት ሳያጠፉ በሚሰሩበት ጊዜ የሚከሰት እንደሆነ ተናግረዋል። ▪️በተጨማሪም ከላይ ብሎኬት ወይም ድንጋይ በመውደቁ ከሥር ያለውን ባለሙያ ሔይወት ያጠፋበት ሁኔታ ስለመኖሩ ም/ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል። ▪️ሕይወታቸውን ካጡ ዜጎች መካከል አብዛኞቹ የሕንፃ ግንባታ ሠራተኞች መሆናቸውን አንስተው፤ አንዳንዶች ግን ህንፃውን ለመጎብኘት ወይም ለመግዛት የሚሄዱ ሰዎች ላይ ጭምር አደጋው መከሰቱን ገልጸዋል። ም/ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እነዚህ አደጋዎችም በቀላሉ ጥንቃቄ ቢደረግ ኖሮ መከላከል እና የሞት አደጋን ማስቀረት የሚቻልበት ሁኔታ እንደነበረ አስረድተዋለ። 🏢በመሆኑም የሕንፃ ግንባታ ደህንነትን በተመለከተ በሰፊው እየተሰራ በሚገኝበት በዚህ ወቅት፤ ከበፊቱ የሞት አደጋ እየቀነሰ ስለመምጣቱ ተናግረዋል።

ብርሃን ባንክ ሰንጋተራ ጎማ ተራ አካባቢ ተሰማ አባ ቀናው መንገድ ላይ ለሚያስገነባው የሽግግር ዋና መስሪያ ቤት የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር Yema Architecture ያቀረበው ዲዛይን አሸናፊ ሆ
+4
ብርሃን ባንክ ሰንጋተራ ጎማ ተራ አካባቢ ተሰማ አባ ቀናው መንገድ ላይ ለሚያስገነባው የሽግግር ዋና መስሪያ ቤት የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር Yema Architecture ያቀረበው ዲዛይን አሸናፊ ሆኗል።
በውድድሩ ሁለተኛ Jdaw Consults ሦስተኛ Addis Mebratu አራተኛ Geretta ሲሆን፤ አምስተኛ Biybone consultings ናቸው።
አሸናፊው Yema Architecture ባለፈው ማክሰኞ በብርሃን ዋና መሥሪያ ቤት ስምምነት ሊያደርግ ችሏል። Yema Architecture የተቋቋመው እኤአ በመስከረም 2007 ዓ.ም በአዲስአበባ ውስጥ ሲሆን፣ ትኩረት አድርጎ የሚሠራው በአረሰክቴክቸር፣ በኢንጂነሪንግ፣ በኢንቴሪየር ዲዛይን እና በፕሮጀክት ማኔጅመንት ዙሪያ ነው። t.me/infraconmedia