ጥበብ ፍልስፍና
Open in Telegram
ተፈጥሮን በጥልቀት ተመልከት ያን ጊዜ ሁሉንም ነገሮች በተሻለ ትረዳለህ ፫፮፱ ፤ ሰዉም ትሆናለህ!!
Show more2 774
Subscribers
+124 hours
+207 days
+8430 days
Posts Archive
2 774
አንድ ሰው አንድን ሰው ለምን ይወዳል?
አንድ ብላቴና አንዲትን ኮረዳ የሚወዳት ለምንድን ነው? ስለሌሎቹ አላውቅም:: እኔ ግን ወሰንን የወደድኳት በብርሃን ተከባ ስላየሁዋት ነበር:: ሰዎች ሊያምኑኝ አይችሉም:: ግን በብርሃን ተከባ ስላየሁዋት ነው::
ለመስቀል ለመስቀል የከተማችን ሕዝብ በጠቅላላ ተሰብስቦ ዳመራ የሚያቀጣጥልበት ጉብታ ከከተማው ወጣ ብሎ አለው:: እስላሙ የሙስጠፋ አባት እንኳን ከነ ቤተሰባቸው ለወሬ ብለው ይመጣሉ:: ሲመሽ አንድና ሁለት ሰዓት ገደማ ሕዝቡ ዳቦቱን ይዞ ከየቤቱ ሲወጣ የንፋስ መውጪያ ከተማ ከሰማይ የወረደ የኮኮብ ስብርባሪ ትመስል ነበር፡፡ እውነቴን ነው ያን ዕለት ማታ ከሰማይ የወረደች ትመስል ነበር:: አሳዳጅ ጥላ ሞቷ ሁሉ ስለሚጋረድ እንኳን ንፋስ መውጪያ ተወለድኩ ያሰኛል:: የዳመራው እርጥብ እንጨት በእሳት ተበልቶ ሳያልቅ፣ ሰዎች ሁሉ ፊታቸው በፈገግታ እንደ ተከፋፈተ፣ አባት የልጁን እጅ ይዞ ወደ ዳመራው ቦታ እየመራው በየጓዳቸው በእንጉርጉሮ ባሽ እየመረቀ…ፈራ ተባ የሚለው ጨለማ ከተማዋ ሰማይ ላይ እንደረጋ…የችቦዎቹ ብርሃን እንዳፈጠጠ…ንፋስ መውጪያ እንዲያ እንዳማረባት ብትኖር እወድ ነበር።
የዚህ የደመራ ማንደጃ ኮረብታ ዙሪያው ሙልጮ ነው የመላጣ ሰው ጭንቅላት ይመስል ነበር:: ደመራውን ቀን በብርሃን በተለይ ከመሃል የሚቆመውን ቃወት አዛውንቶች ይገነቡትና ማታ ችቦ ይዘን መጥተን እንለኩሰዋለን…….ከፊሉ የደመራው ግድግዳ ላይ የሚነድ ችቦ እንደ ጦር ወርውሮ ይሰካል…ከፊሉ እንደመፋቂያ ወስዶ ይሸጉጣል…ከፈሉ እቃ እንደሚጥል አድርጐ ይወረውራል…ታዲያ ሁሉ ፊት ላይ ደስታ አያለሁ:: የሚገርመኝ ነገር የዕውነት ሳቅ አይ ነበር…ሁሉ ከየቤታቸው እየተኮረኮሩ የመጡ ይመስላል፡፡
ታዲያ ደመራው በየቤታችን በችቦ ተሸክመን ባመጣነው እሳት ይለኩስና ይቀጣጠላል፡፡ ሲቀጣጠል ሰዎች ዙሪያውን ከበው ይዘፍናሉ…'ኢዮሀ አበባዬ!' 'ሎጋው ሽቦዬ!' ይላሉ:: ሌላ ሌላ ሁሉ ዐይነት ዘፈንም ይዘፍናሉ፡፡ ብዙ ጊዜም ደመራው ከሚነድበት ምን አልባት ሁለት ኪሎሜትር የምትርቀውን የአድባር ዛፍ(7) ነክቶ የመመለስ ሩጫ ውድድር ይደረጋል:: የመጀመሪያው ሦስቱ አሸናፊዎች ያማረ ጠላ በቀንድ (ቀንድ?) ዋንጫ ይሰጣቸዋል:: ጉራቸው መከራ ነበር:: በዚህ ሁሉ መሃል መጠጥ ይቀዳል። ድፎ ዳቦ ይቆረሳል... የተከመረው የሚቃጠል እንጨት በእሳቱ እየተናደ፣ ቁመቱ እያጠረ፣ ፍምና አመድ እየሆነ የዘፋኙና የጨፋሪው ድምዕ እንደ ቅራሪ መቅጠን ሲጀምር ሰዎች ወደ፡የቤታቸው ይበታተናሉ:: ልጆች ግን 'ብዙ አታምሹ ተብሎ እንመከርና ወደ ሁዋላ እንቀራለን (እኔን ማለቴ አይደለም)…እንደ እናት ወተት የሚሞቅ እሳት ዙሪያ እንደ ገበጣ ጠጠር ተደርድረን::
ወሰን የለሽን ያየሁዋት ይሄን ጊዜ ነበር:: ሰዎች ወደ የቤታቸው ለመሔድ መበተን ሲጀምሩ ወደ እሳቱ ተጠግታ ተቀመጠች:: ብን ያለች ነጭ ኩታ ለብሳለች። አንዳንዴ ወንዝ የማያቸውን ትናንሽ እግረ-ቀጫጭን ወፎች ትመስል ነበር፡፡ ቅጥነትዋ ደሞ የሆነች ዝሃ:: እንግዲህ እሳቱ አጠገብ መጥታ ስትቀመጥ የእሳቱ ወጋገን የሚያበራበት ፊቷ በእኔ በኩል ይሆናል፡፡ ታዲያ ያምራል። የእውነቴን ነው ያምራል:: ለምን እንደሆነ አላውቅም ያምራል:: ተጨማሪ ጐንዋ ቆመው የነበሩ ሰዎች ገለል ገለል ብለው ከእሳቱ ራቅ ብለው ወሬ ጀመሩ:: ከሁዋላዋ የአገር ልብስ የለበሱ ሴቶች የኖራ ግድግዳ መስለው ቆመው ነበር:: የወሰን ፊት ፀጥ ያለ ነበር:: ሠላም ያለበት ይመስላል፡፡ አልፎ አልፎ ምክንያቱን ባላውቅም በትንሹ ፈገግ ትላለች:: አፌን ከፍቼ አያታለሁ:: ከበስተሁዋላዋ የቆመው ከነጠላና ከጋቢ የተሰራው የሰው ግድግዳ ሲፈርስ ተአምር ተፈጠረ፡፡ ያ የኖራ አገር ባሕል ልብስ ግድግዳ ሰማይ ላይ የምትፎልል ድፍን ጨረቃ ከልሎ ኖሮአል:: ታዲያ ጠቆር ያለው የወሰን ጭንቅላት ድፍንዋ ጨረቃ መሐል ላይ የተቀመጠ መሰለ፡፡ አቅጣጫው:: ጨረቃዋ ቢጫ ናት:: የጨረቃዋ ማድያት የለም:: ታዲያ ወሰን በስዕል ላይ የማያትን ትንሽ ማሪያም መሰለችኝ:: አፌን በለጠጥኩ:: ትንፋሽ አጠረኝ:: የደመራውን እሳት ትቼ እሷ ላይ ዐይኖቼን እንደመዥገር አጣበቅሁ:: ወሰን በቀስታ ብትነቃነቅም ጭንቅላቷ ከጨረቃዋ ክብ አልወጣም:: ብዙ ሳይቆይ እስኪበቃኝ ሳላያት ያ የኖራ፣ የአገር ልብስ ግድግዳ ቀድሞ እነበረበት ተመለሰ፡፡ እንደ አጋጣሚ ዞር ብላ አየችኝ:: ያውም ያን የተረገመ አፌን እንደከፈትኩ፡፡ እጅ ከፍንጅ:: አልሮጥ ነገር:: እሳት ውስጥ ዘልዬ አልገባ ነገር:: ታዲያ ከዛን ቀን ጀምሮ ያቺ ምስልዋ አንጀቴ ውስጥ ገብታ ከሌሎች ሰዎች ያልተለየች መሆንዋን ብረዳም ምክንያቱን ልገልጠው በማልችልበት ሁኔታ ልዩ አድርጋ አሳቀለችኝ:: አንድ አንድ ሴቶች አንደበታቸው ብቻ ያምራል፤ አንዳንድ ልጃገረዶች ፊቶቻቸው ብቻ ያምራሉ፣ አንዳንድ ሴቶች ቂጣቸው ብቻ ያምራል፣ አንዳንድ ልጃገረዶች አለባበሳቸው ብቻ ያምራል…በብርሃን የሚከበቡ ግን ከወሰን ሌላ ያሉ አልመሰለኝም::📖 ግራጫ ቃጭሎች
2 774
እማ ዘንድ ይደር?!
ቴዎድሮስ ገብሬ በ'በይነ-ዲሲፕሊናዊ የሥነ ጽሁፋዊ ንባብ፣ ሚካኤል ሽፈራው በ'ማስጠንቀቂያው ደውል፣ ሀብታሙ አለባቸው በ'ታላቁ ተቃርኖ፤ ስለ 'Myth' ወይንም ትርክት አፈጣጠር፣ አስተዳደግና በአገረ መንግስት እና የብሄር ግንባታ ላይ ያለውን አውንታዊ ተፅዕኖና የአንድ ማህበረሰብን ስብዕና እንዴት እንደሚቀርፅ አትተዋል። እማ ዘንድ ይደር እነዚህን የጥናት መስኮች የሚነካ ሙዚቃ ነው። ሀብታሙ አለባቸው እንደሚሉት 'ኢትዮጵያ አሁንም አሁንም state formation ወይም ሀገረ- መንግስት ግንባታ ላይ ነች እንጂ Nation build አድርጋ አልጨረሰችም።' ይህም ማለት ህዝቧን ለአንድ አላማ አስተባብሮ የሚያኖር የወል ማንነት ወይም Collective Consciousness እስካሁን አልፈጠረችም። ይሄ ሙዚቃ ይህንን ይደግፋል.. ቁጭት የወለደው መጠይቅ ያነሳል፣ በትዝታ ቅኝት ይቃትታል። ሙዚቃው በጭብጥ ረገድ ታሪክ ጠቃሽ፣ Folklore (ሀገረሰባዊ)'ና rhetoric ነው። በዚህ ሙዚቃ የወል ማንነት (National myth) ሊመሰርት ነው የፈለገው። ለ' Great Britain- King Arthur ለ'Japan- Emperor Jimu እንደሆነ ሁሉ እዚህ ላይ ንግስት ማክዳን¹ መርጧታል።
ብሄር ግንባታ ላይ ያተኮረ በአዲስ ማንነት የተዋቀረ ሌላ አገር የመስራት ተልዕኮ። ለዚህም አንድ ጀግ'ና ያስፈልጋል። ምን የሚያደርግ?
"ማ ዘንግ ይዞ ገብቶ ገዳም ቢያገናኘው ፍቅርን ካ'ዳም ማ ፆም ይዞ ቆጥሮ ጠጠር ባሳከለው ፍቅርን ሀገር"ራቁቱን ለሆነ ገላ የምንጥለት ነው!
"ስለት አለብኝ ከርቤ እና እጣን ለመተያየት እንዲያበቃን፡፡ የጠቢቡ ሰው የሊቁን ቅኔ ህልሜ አይፈታም ሳላይሽ ባይኔ፡፡ እማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ፡፡ ማዘብ ኖሮ ለኔ ገላ ደግሞ አያለሁ ካንቺ ሌላ፡፡"¹በቅዱስ በመፅሃፉ የተጠቀሰች ብቸኛ በራሷ የነገሰች ሴት። እውቀትን ፍለጋ ባህር የተሻገረች እና የሁለት ሺ አመታት ስርወ' መንግስት መመስረት ምክንያት የሆነች ንግስት።
2 774
የስነ-ጥበብ ውሳኔዎች (Objectivity) ወይስ (Subjectivity) ናቸው ?
ይህ ክርክር በስነ-ውበት ፍልስፍና (Aesthetics) ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሲሆን፣ የ ሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ "#ሞናሊዛ" (#Mona_Lisa) ለዚህ ውይይት ተመራጭ ማሳያ ናት። የጥበቡን "ተጨባጭነት" ስንመለከት፣ በስራው ላይ የሚታዩትን ግዙፍ እውነታዎች ማለትም የቀለሙን አጠቃቀም፣ የብሩሽ አያያዝ ዘዴን (Sfumato) እና የጥላና ብርሃን ውህደትን እናጠናለን። ከዚህ አንጻር እንደ ኢማኑኤል ካንት (#Immanuel_Kant) ያሉ ፈላስፋዎች "የውበት ፍርድ" (Judgment of Taste) በከፊል ሁለንተናዊ ሊሆን እንደሚችል ይከራከራሉ። ካንት #Critique_of_Judgment በሚለው መጽሐፉ ላይ እንደሚረዳው፣ አንድን ነገር "ቆንጆ ነው" ስንል ሌሎችም በዚያ እንዲስማሙ የመጠበቅ ዝንባሌ አለን፤ ይህም ውበት በራሱ በሥራው ውስጥ የሚገኝ ተጨባጭ ባህሪ እንዳለው ያሳያል። የሞናሊዛ ፈገግታ በሂሳባዊ ስሌትና በሰውነት ጥናት (Anatomy) ላይ ተመስርቶ መሳሉ፣ ጥበቡ ከግል ስሜት ባለፈ ሳይንሳዊ እና ተጨባጭ እውነትን የተላበሰ መሆኑን ያረጋግጣል። በሌላ በኩል፣ የስነ-ጥበብ "ግላዊነት" ወይም ሳብጀክቲቪቲ የጥበብ ስራው በተመልካቹ ህሊና ውስጥ የሚፈጥረውን ትርጉም ይመለከታል። የሞናሊዛ ምስጢራዊ ፈገግታ ለአንዱ የደስታ፣ ለሌላው ደግሞ የሐዘን ወይም የፌዝ ምልክት ሆኖ ሊታይ ይችላል። ይህንን ሃሳብ የዴቪድ ሂዩም (#David_Hume) "Of the Standard of Taste" በሚለው ድርሰቱ ላይ ካሰፈረው እይታ ጋር ማገናኘት ይቻላል። ሂዩም ውበት ያለው በነገሩ ላይ ሳይሆን በተመልካቹ አእምሮ ውስጥ ነው ይላል። እንደ እርሱ አባባል፣ እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ የስሜት ህዋሳት እና የህይወት ተሞክሮ ስላለው፣ ጥበቡን የሚረዳበት መንገድ ይለያያል። ሞናሊዛን ስንመለከት የምናየው የራሳችንን ስሜትና ትውስታ ጭምር በመሆኑ፣ ጥበቡ ቋሚ ትርጉም የሌለው እና እንደ ተመልካቹ የሚቀያየር "ግላዊ" እውነት ይሆናል።
በመጨረሻም
ዘመናዊው የሄርሜኔቲክስ (#Hermeneutics) ፍልስፍና በሁለቱ ጽንፎች መካከል ያለውን መስተጋብር ያጎላል። እንደ ሃንስ-ጆርጅ ጋዳመር (#Hans-Georg_Gadamer) ያሉ ፈላስፋዎች እንደሚሉት፣ ጥበብ በተጨባጭ የታሪክ እውነታ እና በተመልካቹ ወቅታዊ ግንዛቤ መካከል የሚደረግ "ውይይት" ነው። ሞናሊዛ በታሪክ ውስጥ ያለፈችበት ጉዞ እና የሊዮናርዶ ጥበብ (ተጨባጭ) ከተመልካቹ የግል ስሜት (ግላዊ) ጋር ሲዋሃድ ነው የጥበብ እውነተኛ ትርጉም የሚፈጠረው። ስለዚህ፣ የሞናሊዛ ታላቅነት የሚመነጨው በሁለቱ መርሆች መካከል ካለው ሚዛን ነው፤ ስራው በራሱ ጥበባዊ ህግጋትን የጠበቀ ተጨባጭ አካል ሲሆን፣ በተመልካቹ ህሊና ውስጥ ደግሞ ማለቂያ የሌለው የግል ትርጓሜን የሚፈቅድ ህያው ምስል ነው።ፍልስፍናዊ ጥያቄዎች 1 ውበት ያለው በሊዮናርዶ ብሩሽ አያያዝ እና በቀለማቱ ውህደት (Objectivity) ውስጥ ነው ወይስ በተመልካቹ አይንና ስሜት (Subjectivity) ውስጥ? 2 የሞናሊዛ ፈገግታ በፊቷ ላይ ያለ እውነተኛ እንቅስቃሴ ነው ወይስ የእኛ አእምሮ ያልተሟሉ ጥላዎችን ለመሙላት የሚፈጥረው የራሱ ትርክት? 3 አንድ የጥበብ ስራ ለዘመናት "ቆንጆ" ተብሎ የሚታሰበው በራሱ ባለው ጥበባዊ ጥራት ነው ወይስ ማህበረሰቡ በጋራ ስለተስማማበት (Collective Subjectivity)? 4 ሮላንድ ባርት (Roland Barthes) እንደሚለው፣ የሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ የግል ሃሳብ ለስራው ትርጉም ወሳኝ ነው ወይስ ስራው አንዴ ተስሎ ካለቀ በኋላ የራሱ ህይወት ኖሮት በተመልካቹ ትርጓሜ ብቻ መኖር አለበት?
2 774
"እውነት ከሰው ልጅ ፍላጎት ውጭ ነው በስምምነት አይፈጠርም፡፡ እውነት ከሰው ልጅ ፖለቲካዊ ስልጣንና ሀይል ጋርም ግንኙነት የለውም፤ የኃይል ብዛት እውነትን ማጥፋትም ሆነ መፍጠር አይችልም፡፡ በርግጥ እውነትን የኃይለኞች ፍላጎት አድርገው የሚተረጉሙ አሉ፡፡ የራሳቸውን ፍላጎት ህዝቡ ሁሉ የሚገዛበት እውነት አድርገው ለማቅረብ ቄሱ መፅሐፍ ቅዱስን፣ ሼሁ ቁርዓንን፣ ሀብታም ገንዘቡን፣ ባለስልጣን ደግሞ ህግንና ሚዲያን ይጠቀማሉ፡፡ በዚህም የተነሳ ሀይማኖት፣ ገንዘብ፣ ስልጣንና ሚዲያ እውነትን የመፈብረኪያ ማሽኖች እየሆኑ በዘመናት ሁሉ ታይተዋል፡፡’’
2 774
....... የመጨረሻው ክፍል
የምንኖረው ወደድነውም ጠላነውም የወንዶች ዓለም( man's world ) ውስጥ ነው። አዎ! ወንዶች የገነቡዋት! ይህንን ክፍል በምሳሌዎች እያዋዛሁ ማቅረብ የተሻለ ሆኖ ስላገኘሁት «እንደምሳሌ አንድን እስር ቤት» እንውሰድ። በእስር ቤቱ ከሚገኙ ከአሥሩ ታሳሪዎች ሰባቱ ወንዶች ፣ሶስቱ ደግሞ ሴቶች ናቸው እንበል። ታድያ በእስር ቤቱ ህይወት ውስጥ ኑረትን ታሳቢ የሚያደርገው «ወንዶችን ብቻ» ነው። ሶስቱ ሴቶች በዚህ እስር ቤት ውስጥ ከወንዶቹ በላይ ተጠቃሚም፣ ተጎጂም የሚሆኑበት መንገድ ሰፊ ነው።
ሴቶቹ ወንዶችን ለማግኘት ብዙ አይቸገሩም፣ ዓለሙ የወንዶች ስለሆነ «ፈላጊ ሳይሆኑ ተፈላጊዎች» ናቸው። ይህ «የፈላጊ እና ተፈላጊነት» ሂደት ግን ምግባሩን ላይጠብቅ እና ሊያፈነግጥ የሚችልበት መንገድም አለ። በሰላማዊ መንገድ ተነጋግሮ መፍታትን እሴታቸው ያላደረጉ ሰዎች ጉልበትን በመጠቀም ከሴቶቹ የሚፈልጉትን ለማግኘት ሊፈልጉ እና ሊያደርጉት ይችላል። በተመሳሳይ ሴቶቹን ወደ እራሱ ለመሳብ የሚለምን፣ የሚደልልም ብዙ ነው።
ዓለምን በእዚህ እስር ቤት ልንመስላት እንችላለን። ማንም ተዋጠለትም፤ አልተዋጠለትም አሁን ላይ ባለው የወንዶች ዓለም ውስጥ ሴቶች ህይወት የሚያሳምሩ ቅመሞች ናቸው። የአንድ ሴት እና የአንድ ወንድ በአማካይ ያላቸው ፈላጊ ብዛት ሊነጻጸር አይችልም።
ይሄ ተፈላጊነት «አስገድዶ ደፈራዎችን፣ ጾታዊ ትንኮሳዎችን» ይዞ እንደሚመጣ የታወቀ ነገር ነው። አንድ ፈላጊ ፍላጎቱን በምን መልክ የማሳካት ስትራቴጂ አለው? በጉልበት? በልመና? የሴቶቹን ፍላጎት በመገደብ? በማክበር? በመደለል? በገንዘብ? ...?
ወደ ወንዶቹ ስንመጣ የት ገባህ የት ወጣህ የሚለው ሰው እንኳ ላይኖረው ይችላል። አንድ ወንድ ልጅ የሚፈለገው ባቀረበው ልክ እንጂ በእሱነቱ፣ በጾታው አይደለም። የሚያቀርበው ነገር ከሌለ ትኩረት የሚሰጠውም የለም። ሴቶች በወንዶች ዓለም ውስጥ ሲኖሩ ህይወት ከመክበዷም ባሻገር «ህይወት ቀላል» የመሆን ዕድሏ ሰፊ ነው።
በተለይ ፖስት-ፌምኒስት የሚሏቸው የፌምኒዝም ምሁራን ይሄንን አያጡትም። ሴቶችን ነጻ ለማውጣት በቅድምያ እነርሱ ላይ የተጣለው «የተፈላጊነት ቀንበርን መስበር» ይፈልጋሉ። የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ድጋፍ፣ የትዳር ተቃውሞ፣ ነጠላ እናትነት፣ የወሲብ ንግድን፣ የኦንላይን ወሲብን ወዘተ... በዕቅድ ይዘው ያቀነቅኑበታል። ጥቃቱን ለመቀነስ ተፈላጊነት መቀነስ።
እዚህ ጋር ፌምኒዝም የረጅም አመታት የሴቶች ትግል እንደመሆኑ ፌምኒዝምን «እንደባቡር ፌርማታ» እንውሰደው። ትግላችን እዚህ ድረስ ነበር ብለው ከፌርማታው የወረዱ ትላልቅ የፌምኒዝም አቀንቃኞች (የንቅናቄው መሪዎችን ጨምሮ ) አሉ። የፌምኒዝም አጀማመር መሰረታዊ ጥያቄዎች ቢሆኑም ወደ ሀገራችን ስናወርደው አሁን ላይ የደረሱበትን ፌርማታ መረዳት ያስፈልጋል።
አሁን፣ አሁን (እነሱ ባሉበት ሀገር ላይ) እንደታሰበው የሴቶች ተፈላጊነት እየቀነሰ የመጣ ይመስላል። በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩት የትዳር እድሜ ላይ የሚገኙ አብዛኛው ወንዶች ወደ ትዳር የመግባት ፍላጎት ፈጽሞ የላቸውም። በተቃራኒው በሴቶች ዘንድ «የትዳር አጣን ጥያቄዎች» ሲሰ'ሙ ፈላጊነቱ ወደ ሴቶቹ እየዞረ የመጣ ይመስላል። ትዳር የሚፈልግ ወንድ አናሳ በመሆኑ ትዳር የሚፈልገው ወንድ «ከመምረጥ ወደ መመረጥ፣ ሴቶቹ ሲያደርጉ እንደነበረው መራጮችን ሰብስቦ ወደ መምረጥ» እየሄደ ነው።አሁን የሚታየው ወንዶችን የሚያማልል አለባበስ፣ ጡት ጭመራ/ቅነሳ፣ ዳሌ ጭመራ፣ ለውበት የሚሰሩ ቀዶ ጥገና ህክምናዎች፣ ሜክአፖች፣ አርቴፊሻል ጸጉሮች፣ ለቅጥነት የሚደረጉ የምግብ አድማዎች ወዘተ..ከተፎካካሪዎች መሀል ላቅ ብለው ትኩረትን፣ ፈላጊን የማግኘት ሂደቶች ናቸው። መቶ / ሁለት መቶ ዓመት ወደፊት ብንጨምርበት ሴቶች በተፈላጊነታቸው የሚሰጣቸው እንክብካቤ ይበልጥ ይመናመንና አሁን ወንዶች ወዳሉበት ያለመፈለግ ስሜት፣ ድብርት፣ እራስን የማጥፋት፣ የህይወት ትርጉም ማጣት ሊያመሩ የሚችሉበት እድል ሰፊ ነው። በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩት አሁን ያሉ ትዳር ፈላጊ ወንዶች ከዘበናይ ትዳር ወደ traditional value ትዳር ፍላጎታቸው እየተሳበ ነው። ፍቺ ጨምሯል፣ ወደ ሌላ (ባህላዊ ትዳር የሚከበርባቸው) ሀገራት የትዳር ፍለጋ ጉዞዎች ጨምረዋል ወዘተ...ይሄ ለአቀንቃኞቹም ሆነ በእነሱ ስር ላሉ ሰዎች መልካምም አሉት መጥፎ የተለየ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው። ____________ የኢትዮጵያ ሴቶች ችግር በዋነኛነት በሁለት መክፈል ይቻላል። የከተማ ሴቶች ችግር እና የገጠር ሴቶች ችግር። የሁለቱ ችግሮች መራራቅ ከዚያም ባስ ሲል የሌላ ሀገር ፌምኒስቶች የደረሱበት የፌርማታ ርቀት ትግላቸውን እጅግ አዳጋች ያደርገዋል። የከተማ ሴቶች....
_ የከተማ ሴቶች ችግር ከገጠሮቹ አንጻር የማይታይ እና የተደበቀ ነው። ሴቶች 'prime age' ተብሎ በሚቀመጥበት ሰዓት ትዳር መያዝ፣ ልጅ መውለድ በማህበረሰቡ ይጠበቅባቸዋል። ይሄን ያላሳካች ሴት ከማህበረሰቡ፣ ከቤተሰቦቿ የሚደርስባት ጫና የሚታወቅ ነው። ስለዚህ የማግባት ፍላጎት ባይኖራት እንኳ፣ የማትፈልገው ሰው ቢሆን እንኳ አብራ ለመኖር፣ ካገባችም ባልተሳካ ትዳር ውስጥ የሚደርስባትን ችግሮች ለመቋቋም ትገደዳለች። አቻዋን አጥታ «የመውለጃ ጊዜዬ ሳያልፍ ልጅ መውለድ እፈልጋለሁ ግን ትዳር አልፈልግም፣ ዝግጁ አይደለሁም» ካለችም እንደ ዘመናዊ ሽርሙጥና ተደርጎ ይያዝባታል። ልጇም ዲቃላ ይባላል። ታድያ ከሀብታም ወንዶች፣ ከተሳካላቸው ወንዶች ስር የማይጠፉ፣ ድሃ ወንድ አያውራኝ የሚሉ፣ ማህበረሰቡ በስኬታቸው ለተቀበላቸው ወንዶች እግር ላሽ የሚሆኑ ሴቶች ካለባቸው ማህበራዊ ጫናም ጭምር ነው። ሰነፍ ሊሆኑ የመቻላቸው እድል እንዳለ ሆኖ ሰርተው እንዳይለወጡ prime age ያልፋል፣ ያላቸው አማራጭ የተሳካለት ወንድ አሳዳጅ ነው። _ በየሄዱበት፣ በሚሰሩበት ወሲባዊ ትንኮሳ ይደርስባቸዋል፣ ከላይ በእስርቤቱ ምሳሌ እንዳየነው ሴቶች ተፈላጊዎች ቢሆኑም ፈላጊዎች «ጉልበትን፣ ማስፈራራትን በመጠቀም ፍላጎታቸውን ለማሟላት ወሲባዊ ጥቃት፣ አካላዊ ጥቃት እና አስገድዶ ደፈራ» ሊያደርጉባቸው ይችላል።የገጠር ሴቶች ....
የገጠር ሴቶች ችግር ከከተማዎቹ እጅግ የራቀ ነው። የሴት ልጅ ግርዛት እና ጠለፋ ባልተፋቀበት ሀገር ውስጥ ሌሎች ጥያቄዎች መጠየቅ የሚያደክም ነገር ነው። መሰረታዊ የሴት ንጽህና መጠበቂያ የሌላቸው፣ አስገድዶ መድፈር እንደ ኖርማል ወሲባዊ ድርጊት የሚታይበት፣ አይ ሴት ነች እኮ! የሚባልበት፣ ሴት ሲወለድ የሚታዘንበት፣ ሴት ልጅ ከማድቤት ከወጣች፣ ከሰፈሯ ከራቀች ሳትደፈር የምትመለስበት ሁኔታ የመነመነበት..ሀገር ነው።..........
2 774
የተገናኘን ቀን ነው አልጋ ላይ ራሳችንን ያገኘነው ፤ ወሲባችን ፍቅር አልነበረውም ፤ ሰክረን ነበር ፤ ከአንድ ዙር መፋተግ በኋላ ፤ አንድ ዙር ፍቅር አልባ ወሲብ እንዳለቀ ፊቴን አዞርኩ ሲጋራዬን ለኮስኩ ፤ ፊቷን አዙራ ስልኳን መነካካት ጀመረች ።
ሁለታችንም ጀብረር ብለን ነበር።
ምንም ያላወራው ይመስለኛል ፤ እርግጠኛ ነኝ ከዚህ በኋላ አንገናኝም ፤ በአንድ ቀን የምትጋደም ፣ ከሴተኛ አዳሪ ገንዘብ ባለመቀበል ብቻ የምትበልጥ ወይም የምታንስ ልጅ ማን ቁምነገር ይሰጣታል።
አስክሮ ፣ እትትት ብሎ የሚዳራ አለሌ ሸሌ ወንድ ለቁም ነገር እንደማይሆን እርግጥ ነው።
ተኛን !
ሳንተቃቀፍ ተኛን...
እኩለ ለሊት እንዳለፈ ይመስለኛል ፤ አመመኝ ከተኛሁበት አልጋ ተስፈንጥሬ ከአልጋዬ ብዙ ሳልርቅ ወለሉ ላይ አስመለስኩ ።
ከምቅፅበት ተነስች!
ከጎኔ መጥታ ልቤን ያዘችልኝ ፤ ከሆዴ ጀምሮ አማጥኩኝ ፣ አማጥኩኝ አቅም አነሰኝ እና ጥምልምል አልኩ ፤ መታገል ፣ ማጓራት ብቻ የሚወጣ ግን የለም ፤ ውሃ ጠጣ ብላ ሰጠቺኝ ፤ ትንሽ ጠጣሁ አፍታ ሳይቆይ የጠጣሁትም ውሃ ወጣ ።
ቀና በል ፥ ቀና ይሸትኻል አለቺኝ ፤ ትውከቱ እንዳይሸተኝ ቀና እያደረገችኝ ፤ እሷን ተደግፌ ቀና አልኩ ጨርቅ አምጥታ (ከውስጥ የለብስኩትን ቦዲ ) ውሃ ነክራ አንገቴን ፣ ግንባሬን አራሰችልኝ ፤ ቅዝቅዝ አለኝ ።
ቀስ ብዬ ጠቅልል ብዬ ተኛሁ ፤ ስትንጎዳጎድ እንቅስቃሴዋ ይሰማኛል ፤ አቅሜ ተዳክሞ ስለነበር ለጥ አልኩ ። ጠዋት ስነቃ እና ማታ የሆነውን ሳጤነው ሁኔታዋ እና እንክብካቤዋ አንጀቴን በላው። ትውከቴ ከቦታው የለም ፤ እንዴት አልተፀየፈችውም ፤ ማን ስለሆንኩ አንደዚህ ተንከባከበቺኝ ።
አብረን ቁርስ በላን ። ስለ ማታው ሁኔታ ምንም አላወራንም ፤ አፈርኳት ፤ ውለታዋ ቆጠበኝ ። ከዛ ቀን በኋላ አብረን ነው የምንውለው ።
ተልካሻ ስፍራ በማይረባ ሁኔታ እንዴት እንደዚህ ግጣሜን ላገኝ ቻልኩ?
በሁለት ወር ከአስራምስት ቀን ዳግም ለሁለተኛ ቀን ተዋሰብን ፤ ያኔ ሰውነቴ ተቀብሏት ነበር ፤ ሰውነቷ ተቀብሎኝ ነበር እናም ተዋሃድን ፤ የሚዋደዱ ሰዎች ሲዋሰቡ ወሲቡ ውህደት ነው ፣ የነፍስ ቁርኝት ፤ ተቆራኘን። ውድ ቦታ እና ቅዱስ ቦታ ብቻ ነው ትክክለኛ ሰው የሚገኘው ያለው ማነው?የጀመርነው ህይወት ለሁሉ ሰው አሳማኝ ይሆናል ያለው ማነው ፤ ህይወታችን የሚመዘነው በምናገኘው ደስታ አይደለም ወይ ? ዛሬ አምናታለሁ ! የምትንዘላዘልበትን ምክንያት ደፍኜዋለሁ ፤ ፍቅሬ እንድትታመነኝ ሰርቷታል ። እንደትላንት እንዳልሸረሙጥ ከእሷ ጋ ያለኝ ነገር ይጋርደኛል ።
ሰው መቼ በተገናኘበት ስፍራ ይመዘናል ፤ ያለንበት ስፍራ ሁሌ መቼ ልካችን ሆኖ ያውቃል። አጀማመራችን ሳይሆን አካሄዳችን ነው የማንነታችን ማሳያ!።
2 774
ዘመን ያገነነው ጅብ ቆሟል ከበሬ ኡኡታዬ 🎶 አፌ እንዳታስበላኝ ባለመናገሬ ኡኡታዬ 🎶 እያየህ ስትወጣ ብትጫወት በሳት ኡኡታዬ 🎶 ምን ያረጋል አፌ ካለፈ ብትወቅሳት ኡኡታዬ 🎶 አይቶ በዝምታ በስተመጨረሻ ኡኡታዬ 🎶 ቢጮህ ምን ያረጋል ጅብ ከሄደ ውሻ ኡኡታዬ 🎶
2 774
...የቀጠለ
የተማህሎ (mystic) ዓለም ሰዎች ዘመናዊው ሳይንስ ለመረዳት እየጀመረ ያለውን ይህን እውነት ከብዙ ዘመናት በፊት ተገንዝበውት ነበር... የገሃዱ አማናዊ እውነት ከስሜት ህዋሳት ባሻገር እንደሆነ ደጋግመው አስተምረዋል...
[ ለምሳሌ ]
ፐርሺያዊው የሱፊ እስልምና ማላይ #Rumi ከግጥሞቹ በአንዱ ውስጥ "Close both eyes to see with the other eye." በማለት የሥጋ ዓይንን ዘግቶ [በሦስተኛው ዓይን] ስለማየት ተናግሯል... በሌላ መስመር ደግሞ “The eye goes blind when it only wants to see why.” በማለት አክሏል...
የጥንታዊቷ ቻይና ፈላስፋ #Lao_Tzu በበኩሉ "The Tao that can be told is not the eternal Tao." በማለት ዘላለማዊው እውነት በአንደበት የሚነገር እንዳልሆነ መስክሯል...
ጀርመናዊው የክርስትና ማላይ #Meister_Eckhart "The eye through which we see God is the same eye through which God sees us." በማለት አስተምሯል...
እኒህ ውብ መስመሮች ጥልቁን የመረዳት መንገድ እናነቃ ዘንድ ከዘመናት በፊት የተስተጋቡልን መልዕክቶች ናቸው...
በኔ እምነት...
በዙሪያችን ስላለው ነገር ያለን መረዳት ውስን መሆኑን ማወቅ ለበለጠ ተገንዝቦት ያነቃቃናል... ትህትናን እንድንላበስ፣ ጠያቂ እንድንሆን እንዲሁም ከስሁት እርግጠኝነት እንድንላቀቅ ያደርገናል...
[እልፍ ቤቶች ካሉት ሕንፃ ላይ የአንድ ኩሽና ዕውቀት የጠቅላላ ግንባታውን ምንነት አይገልጽም...]
ክምናውቀው የማናውቀው መብለጡ የማናየውን አማናዊ እውነት ከስሜት ህዋሳቶቻችን በሚሻገር መንገድ እንድንገነዘብ ፍንጭ ይሰጠናል... ለዚህም ጥሞና፣ (meditation)፣ እርጋታ (stillness)፣ አዕምሮ በውስብስብ የሃሳብ ጅረት ሲናውዝ ነጠል ብሎ ማስተዋል፣ ልብና ነፍስያን ማድመጥ ብርቱ መላ ሆነው ይጠቀሳሉ...ጉዳዩ ግን ይህ ብቻ አይደለም... "We touch the skin of what is real, Yet truth escapes the eye’s ideal. A wave, a whisper, not a wall— The cosmos waits, unformed by all." በግልጽ ከሚታወቀው ምልዓተ ዕለም ውስጥ እኛ የምንረዳው ከ 1% በታች ያለውን ብቻ ከሆነ በሕዋው ላይ ያለነው 'እኛ ብቻ ነን' ማለት ድፍረት ነው... ከንቱ ግብዝነትም ይመስላል... ዩኒቨርሱ በትሪሊየን የሚቆጠሩ ጋላክሲዎች፣ ተቆጥረው የማያልቁ ሊኖርባቸው የሚችሉ ፕላኔቶች፣ እንዲሁም የማይታወቁ በርካታ አውታሮች (Dimensions) የያዘ መሆኑ ሲታሰብ ሐይማኖቶች ሰውን የመለኮት ብቸኛ የትኩረት ማዕከል (Center of Attention) አድርገው የሚያስተምሩበት መንገድ ጥያቄ ይፈጥራል... "The universe is a pretty big place. If it's just us, seems like an awful waste of space." እንዲል አስትሮ ፊዚስቱ #Carl_Sagan Mystic-priest-scientist እየተባለ የሚጠራው #Teilhard_de_Chardin በአንድ ወቅት "Universe evolving toward consciousness, not confined to Earth." በማለት ምድር የዩኒቨርሱ ማዕከላዊ ጉዳይ እንዳልሆነች ገልጿል... በሂንዱ ኮዝሞሎጂ ውስጥ "God" የሆነ ሩቅ ቦታ ተቀምጦ የሚመለከት አካል (Entity) ሳይሆን "a consciousness manifesting through everything—from stars to cells, atoms to awareness." ተብሎ የተነገረበት አውድ ይህንኑ የሚያጸና ነው...
[ይህን ጠይቅ: መለኮት አይለኬ (infinite) ነው ካልን ፍቅሩና አነዋወሩስ ገደብ-አልባ መሆን የለበትም?... ታዲያ ለምን ምድር ላይ ብቻ?... ለእኛ 'ያዳላል' እያልከኝ ነው?... ያለ ባሕሪው?...]ለመስመሮቻችን ዋቢ እናብጅ... ፩ ) ኳንተም ፊዚክስ ስለ እውነታ (Reality) የኳንተም ፊዚክስ ታላላቅ ስሞች ምን አሉ?... #Albert_Einstein እውነታ አይጨበጤ መሆኑን ያረጋግጥና ነገር ግን ዘላቂው እርሱ ብቻ እንደሆነ ያወሳል... “Reality is merely an illusion, albeit a very persistent one.” #Werner_Heisenberg በበኩሉ፣ የምናየው የተፈጥሮን ምልዓት ሳይሆን ለአዕምሮችን በሚመች መገድ የተገለጸውን ማሳያ ነው በማለት ይደመድማል... “What we observe is not nature itself, but nature exposed to our method of questioning.” #Richard_Feynman የተፈጥሮ እውነት በጣም እንደረቀቀበት በገለጸበት ንግግሩ ...“I think I can safely say that nobody understands quantum mechanics.” ብሏል.. የዘርፉ ሌላኛው ትልቅ ስም ያለው #Max_Planck ደግሞ: ...“Science cannot solve the ultimate mystery of nature... because in the last analysis, we ourselves are part of the mystery we are trying to solve.” በማለት የፌይማንን እሳቤ ተጋርቷል ስለ ኳንተም ፊዚክስ አውርተን ፈጽሞ የማንዘለው አንድ ስም ደግሞ አለ #Niels_Bohr.. ቦር እንደ አይንስታይን ሁሉ እውነታ በልምምዳችን ውስጥ ከሚታወቀው እውነታ ፈጽሞ የተለየ መሆኑን ሲገልጽ... "Everything we call real is made of things that cannot be regarded as real." በማለት ደምድሟል... ፪) ፍልስፍና
“All our knowledge begins with the senses, proceeds then to the understanding, and ends with reason. There is nothing higher than reason.” #Immanuel_Kantካንት በዚህ ንግግሩ እውቀት ከስሜት ህዋሳት ቢጀምርም እውነታ ከገጽታ ባሻገር የሚሄድ ጉዳይ እንደሆነ አውስቷል... “We can easily forgive a child who is afraid of the dark; the real tragedy of life is when men are afraid of the light.” #Plato] ፕሌቶ allegory of cave በተሰኘ ስራው (The republic - Book VII) ላይ እስረኞቹ የለመዱትን ጥላ ከብርሃኑ በላይ አጥብቀው ሲሹት ያሳየንና የእውነታን ጥላ እንጂ አማናዊውን እውነት እንዳልተገንዘብን ይልቁንም እንደምንሸሸው በተምሳሌት ነግሮናል... “The menu is not the meal.” #Alan_Watts የምስራቃዊውን ዓለም ነጽሮት በጥልቀት በማጥናት የሚታወቀው ፈላስፋው ዋትስ በዚህ ንግግሩ ቃልና ስሜት ተግባቦት ወካዮች እንጂ በራሳቸው እውነታ አለመሆናቸውን አስገንዝቧል... እስካሁን የመጣንበትን መንገድ በአንዲት ውብ ግጥማዊ መስመር እንቋጭ... "The world you see is but a thread, A shimmer spun from what’s unsaid. Behind the form, no edge, no line— Just breath of God, and curve of time."
2 774
ማየት ማወቅ አይደለም...
በመኖር ሃዲድ ላይ ስንፈስ ብዙውን ጊዜ ለእምነት የምንተወው፣ እንደገባን ሁሉ የምንዘለው፣ ነገሬ ብለን የማንፈትሸው ብዙ ገራሚ ነገር ይኖራል...የሰው ልጅ - ማየት፣ መስማት፣ መንካት፣ መቅመስና ማሽተትን እንደ ብቸኛ የዕውቀት ምንጭ ሲገለገል ዘመናትን አስቆጥሯል... በተለይ ደግሞ Reality / 'እውነታን' የሚረዳበት ብሎም የሚተነትንበት መንገድ Objectivity / 'ተጨባጭነት' ወይም 'ተዳሳሽነት' ብቻ መሰረት ያደረገ ስለሆነ ከነዚህ ፭ የስሜት ህዋሳት የተሻለ መንገድ ሳይገባው ዕድሜውን ፈጅቷል... ግን እኒህ የስሜት ህዋሳት እየዋሹን ቢሆንስ?
የአይለኬውን ሕዋ ቁራጭ ብቻ እየተረጎሙልን ቢሆንስ? በህዋሳቶቻችን የምንረዳው የግዝፈቱን ጥላ ወይም ነጸብራቁን ብቻ ቢሆንስ?...[ነገሩን በሳይንስ ትንታኔ ውስጥ እንየው...] እንደ Astrophysics ትንታኔ 68℅ የሚሆነው ምልዓተ ዓለም (universe) ይዞታ Dark energy ነው... 27%ቱ ደግሞ በ Dark matter የተሸፈነ ነው... ይህም በድምር 95℅ ይደርሳል... ቀሪውና ወደ 5% የሚጠጋው ደግሞ ምድርንና ግሳንግሷን በሕዋ ላይ ካሉ መሰሎቿ ጋር የሚሸክፈው ሁነኛ (baryonic) ሊባል የሚችለው የቁስ መጠን ነው... የጉዳዩ አስገራሚነት ግን በዚህ ብቻ አያቆምም... የሰው ልጅ ይህንን 5 መቶኛም ሙሉ ለሙሉ መረዳት አይችልም... ይልቁንም በ ፭ቱ የስሜት ህዋሳት መገንዘብ፣ (perceive ማድረግ) የሚችለው ተዳሳሽ/ ተጨባጭ የሆነው ቁሳዊ ክፍል 0.0001% ያህል ቢሆን ነው... ቀሪዎቹ መኖራቸውን ብቻ ለማወቅ እንኳ በጣም የተራቀቁ መሳሪያዎች ያስፈልጉታል... [ከዚህ ግንዛቤ አንፃር እውነታ ምንድነው?...] ነገሩን በደንብ ለማስረገጥ፣ በ Quantum level ያለውን ሃቅ ተንተርሰን እውነታን የምንመዝንበትን የተጨባጭነት/ ተዳሳሽነት (objectivity) ግንዛቤ ስንፈትሽም እጅግ አጨቃጫቂ ጉዳይ ይገጥመናል... [ለምሳሌ...] አሁን ይህን ጽሑፍ ስታነብ የያዝከው ሞባይል፣ የተቀመጥክበት ወንበር፣ ሰውነትህ ራሱ፣ በዙሪያህ ያለው ቁስና ዓይንህን የሞላው ጉዳይ በሞላ በ Energy - Frequency እና Vibration እሳቤ ውስጥ አስገብተህ ብትመዝነው ዓይንህ እንደዋሸህ ትረዳለህ... ቢያንስ አሉ በምትላቸው ልክ real አይደሉም ወይም የሉም... ጉዳዩ ግን እዚህ ጋ ብቻ አይቆምም... Double-slit በተሰኘው ዝነኛ Experiment ላይ እንደታየው ዕይታህ (Observation) 'እውነታውን' የመጫን (Influence የማድረግ) ባሕሪ አለው... ቅንጣቶች (particles) ዕይታ ሲለያቸው የ Wave-function ጸባያቸውን ገልጠው mind-bending ሃቅ የገለጡ ሲሆን በዕይታ/ በልኬት (measurement) ጊዜ ደግሞ ወደ definite state ተመልሰዋል... [ይህን መረዳት ለእኛ ምናችን ነው?... ለኑረት ምን ያዋጣል?... ለመረዳታችን ምን ይፈይዳል?... ለመንፈሳዊ ዕይታችን ምን አስተዋጽዎ አለው?...] የስሜት ሕዋሶቻችን ስሁት መረዳት ብዙውን ጊዜ በማይጨበጥ ምሉዕነት ይሞላናል... በተሳሳተ መረጃም በዙሪያችን ስላሉ ነገሮች በሙሉ እንደምናውቅ እንዲሰማን ያደርጋሉ... እውነቱ ግን ሌላ ነው... [ለምሳሌ...] በዓይናችን ትርጉም የምንሰጠው የብርሃን spectrum ከአጠቃላዩ Electromagnetic spectrum አንፃር ሲመዘን ከ 0.0035% በታች ነው... ዓይናችን ለቀሪዎቹ ጨረሮች [gamma ray፣ x-rays፣ infrared፣ ultraviolet እና radio waves] ፈጽሞ ባዕድ ነው... ካለመሳሪያ በጭራሽ ሊገነዘባቸው አይችልም... ጆሮአችን መቃኘት የሚችለው በጣም ጠባብ ለሆነ የድግግሞሽ ምጣኔ (frequency band) ነው... በዙሪያችን ግን እጅግ ብዙ ከፍተኛና ዝቅተኛ የድምጽ ዓይነቶች አሉ... አንዳቸውም ግን አይሰሙንም... ጆሮአችን ደግሞ ያልሰማውን ድምጽ 'አለ' አይለንም... የመዳሰስ እውቀት በአካል ንክክኪ የተገደበ ነው... የማሽተትና መቅመስ ግንዛቤ በቅርበትና በነገሩ ኬሚካላዊ ጥንካሬ ላይ የተመሰረተ ነው... ይሁንና እኒህን ገርበብ ያሉ የመረጃ መስኮቶች ሙሉውን ስዕላዊ ገጽታ እንደሚያሳዩን ሁሉ አጥብቀን እናምናቸዋለን...
[ዙሪያህ በ ፭ቱ የስሜት ህዋሳት ብቻ የማትረዳው ብዙ እውነት እንዳለ ብትቀበል ማየት ማወቅ እንዳልሆነ ይገባሃል፤ ታዲያ ይህን መረዳት አኗኗርህን የሚቀይረው አይመስልህም?...] “The world is illusory; Brahman alone is real; Brahman is the world.” ~ Ramana Maharshiይቀጥላል......
2 774
....... የቀጠለ
በዚህ ክፍል የፌምኒዝም እንቅስቃሴ ችግሮች እና ከእርሱ በተቃራኒው የሚነሱ ሀሳቦችን ከላይ ከላይ እንዳስሳለን።
የሶስተኛው ዙር የመብት ጥያቄ በወቅቱ ድህረ-ሴታዊነት እንቅስቃሴ (post feminism) ይሉት ነበር። ሴቶች የሰው መብት ተሰጣቸው፣ ከዚያም ማህበራዊ ተሳትፎ እኩልነታቸውን አረጋገጡ ስለዚህ አሁን የሴቶች እኩልነት ጥያቄ ተፈጽሟል፣ አብቅቷል ከሚል መነሻ ነው።
ርብቃ ዋከር «እኔ ድኅረ-ፌምኒስት አይደለሁም እኔ የሶስተኛው ዙር እንቅስቃሴ አካል ነኝ።» I'm not postfeminism feminist I'm third wave በሚል ነበር የሶስተኛው ዙር መሆኑን ያወጀችው። becoming a third wave የሚል ጽሑፍም አዘጋጅታለች ይህ የትግል እንቅስቃሴ በዋነኛነት የመራብያ አካላትን የተመለከተ ነው። አትድፈሩን! ወሲባዊ ትንኮሳ አይደረግብን! የስነ-ተዋልዶ መብታችን ይከበር! ሰውነቴ ምርጫዬ! ወዘተ የሚሉ ትግሎች ነበሩ።ትግሉን እንዲፋፋም ያደረገው፡ አኒታ ሂል የተሰኘች አቃቢ ህግ ክላረንስ ቶማስ የሚባል የጠቅላይ ፍርድቤት ዳኛ ወሲባዊ ትንኮሳ አድርጎብኛል የሚለው ክስ ነው። ታድያ በወቅቱ ሴቶችም ቢሆኑ ክሱን ሲያጣጥሉት ነበር። ክሱ ውሸት ነው በሚል በአብላጫ ድምጽ በወቅቱ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ብቸኛ ጥቁር የነበረው ዳኛ ነጻ ቢወጣም ትግሉን አቀጣጥሎት አልፏል። የአራተኛው ዙር ጥያቄዎች ከሶስተኛው ብዙም ባይለዩም የማህበራዊ ሚድያን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ብዙ ሴቶችን፣ የሴቶች ጥያቄ የሚያስተጋቡ ወንዶችን አሳታፊ አድርጓል። ከእዛም ውስጥ ጥቃት ደርሶብኛል የሚሉ 30% ወንዶችም ተሳትፈውበታል። ጾታዊ ጥቃት ያደረሱ ሰዎች ተጠያቂ ይሁኑ፣ ጾታዊ ጥቃት ይቁም በሚሉ ሀረጎች ስር ሁለቱ እንቅስቃሴዎች መጠቃለል ይችላሉ። ችግሮቹ :-
1) የፌምኒዝም አራማጆች ከጥንት ጀምሮ ሌሎች መብታቸው ተጓድሏል ብለው ላመኑት ድጋፍ ሲሰጡ ነበር። ታድያ ይህ የሴቶች መብት ላይ ብቻ አለማተኮራቸው፣ አጀንዳቸውን ወደሌላም ማስፋታቸው ሴት ጠል ያልሆኑ ሰዎች፣ እራሳቸው መብታቸው የተጓደለ ሴቶች እንኳ በሙሉ ልብ እንዳይቀበሏቸው አድርጓል።
2) ይህንን ክፍተት በመጠቀም በፌምኒዝም የታርጋ ስም ሌላ አጀንዳ የሚያራግቡ ሰዎች በውስጣቸው በመኖራቸው። ለምሳሌ postmodern feminism, transfeminism, ecofeminism, sex-positive feminism የመሳሰሉት... #sex_positive_feminism ማለት ሴቶች ወሲባዊ ነጻነታቸውን ማግኘት አለባቸው የሚል ትግል ነው። የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ፣ የወሲብ ንግዶች ህጋዊ ይሁኑ የሚሉ ጥያቄዎችን ያካተተ ነው። ሴቶች ወሲባዊ ነጻነታቸውን የሚያገኙት ያሻቸውን ጾታ ማግባት፣ ገላቸውን ላሻቸው ዓላማ ማዋል ሲችሉ ነው የሚል አመለካከት ነው። ይሄንን ምልከታ ታሪክ ሰርተዋል የሚባሉት ፌምኒስቶች ሳይቀር ያፈነገጠ ጥያቄ ነው ሲሉ፣ የሴቶች ጥያቄ ይህ አይደለም የሚሉ ጥያቄዎች ያነሱበታል። ከዚህ ቀደም ባለው ጽሑፍ ውስጥ በጠቀስኩት መጽሐፏ ቤቲ ፍሪዳን ይሄንን ፍራቻ አስቀምጣለች። #Trans_feminism ደግሞ ወደ ሴትነት የተለወጡ ወንዶች ሴቶች ናቸው መብታቸው ይከበር የሚል ትግል ነው። #eco_feminism ደግሞ የመብት ታጋይ እስከሆንን ድረስ አትክልት በል እንሁን የሚል ትግል ነው። እንስሳትን መብት ከመጠበቅ አኳያ ፌምኒዝም የበኩሉን መወጣት አለበት ባይ ናቸው። #post_modern_feminism ከእነ አካቴው የ feminism አቀንቃኞች አይደሉም የውል ጥያቄ ይነሳባቸዋል።
3) ፌምኒስት የሚለውን ቃል ማንም ሰው ለእራሱ መስጠት በመቻሉ፣ እውነተኛው ፌምኒስት ማነው? ፌምኒስት የመሆን ግብ እና አላማ ምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ በቀላል እና ውስብስብ ባልሆኑ ቃላት ሊመለስ ባለመቻሉ።
4) ትግል ቀሚዎች፣ መስራት የማይወዱ ሰነፍ ሴቶች፣ ከማንበብ የራቁ ባለው ክፍተት ተጠቅመው ትኩረት በማግኘት ከሌሎቹ ይልቅ ወደ ማኅብረሰቡ ገነው በመውጣታቸው።ትችቶች/ ተጻራሪ ሀሳቦች ሴት ልጅ ለማድ-ቤት ነው የተፈጠረችው፣ ሴት ልጅ ሰው አይደለችም የሚሉ ተቃውሞዎችን ሀሳብ እዚህ ጋር አላነሳም። ግን አንዳንድ ተቃውሞዎችን ላንሳ :-
ፕሮፌሰር ክርስቲና ሆፍ የተባለች የፍልስፍና መምህር "Who Stole Feminism? How Women Have Betrayed Women" በሚል ባጠናቀረችው መጽሐፏ የፌምኒዝም ትግል እየተቀማ እንዳለ ትገልጻለች። ፌምኒዝምን በመጽሐፏ በሁለት ስትከፍለው #equity_feminism እና #gender_feminism በሚል ነው። እራሷን equity ፌምኒስት ብላ ስትጠራ ጥያቄያቸውም «ሴቶች እኩል መብት ማግኘታቸው፣ ከወንዶች እኩል ዕድሎችን ማግኘታቸው ፣ ጾታ ላይ መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዳይደርስባቸው፣ ማህበራዊ መብታቸው እንዲረጋገጥላቸው» ብቻ ነው ትላለች። ነገር ግን Gender feminist የምትላቸው ከዚህ ሌላ ዓላማ አላቸው ያለቻቸው ታጋዮችን ነው። ኋላ ላይ #victim_feminism ብለው ሀሳቧን የተቀበሏት እነ ሮፊ ስራዋን እጹብ ይሉታል። ጾታዊ ዘረኝነት፣ ከእኩልነት የዘለለ ጥያቄ፣ የተጠቃሁ ስነልቦና፣ ወንድ ጠልነት፣ ከወንዶች በላይ መብት መፈለግ እያሉ victim feminism ብለው በከፈሏቸው ላይ ትችት ያዘንባሉ። ከዚህ በተጨማሪ በእነዚህ ወገኖች የሚሰራጨው አሀዛዊ መረጃም እውነት እንዳልሆነ ይሞግታሉ።
ከፌምኒዝም እኩል «የወንድ ልጅ መብት» እንቅስቃሴ ተቀባይነት ባያገኝም በርካታ አቀንቃኞች አሉት። የወንድ ልጅ የሞት መጠን ከሴቶች ይበልጣል፣ መንገድ ላይ የሚኖሩ የጎዳና ተዳዳሪዎች አብዛኛቹ ወንዶች ናቸው፣ ሴት እና ወንድ እኩል ወንጀል ቢፈጽሙ ከ20 እጥፍ በወንዶቹ ላይ ይፈረዳል፣ በወንዶች ላይ የሚደረግ አስገድዶ መድፈር እንደሴቶቹ ትኩረት አይሰጠውም፣ ሴቶች በሀሰት ጾታዊ ጥቃት አደረሰብኝ እያሉ የወንዶችን ህይወት እያመሳቀሉ ስለሆነ ያለ በቂ ማስረጃ ማመን(መክሰስ) ወንዶችን መበደል ነው፣ ሴቶች ከወንዶች በተለየ በመንግስት በርካታ ጥቅማ ጥቅሞች ያገኛሉ፣ ወንድ ልጅ ለማህበራዊ አገልግሎት በግዳጅ ሲመለመል ሴቶች አይመለመሉም፣ ወንድ ልጅ በስጋ ያልወለደውን ልጅ እንዲያሳድግ ሴቶች እየፈረዱበት ስለሆነ የዘረመል ምርመራ በግዳጅ እንደልደት ሰርተፊኬት ይሰጥ፣ ወንድ ልጅ የሚያገኘው በሴቷ መልካም ፍቃድ ብቻ እንጂ ልጅ የማግኘት መብት አልተሰጠውም፣ ልጅ የመውለድ ፍላጎት የሴት ብቻ ነው ወንዱ ቅድሚያ ሴቷ ባላሳወቀችውና ባልተፈራረሙበት ሁኔታ ለልጅ ተቆራጭ ማድረግ እኩልነት አይደለም፣ ልጆች አባታቸው ተቆራጭ እያደረገ ሳለ እናትየዋ አባትነቱን የምትፈልገው ለገንዘብ ብቻ እንጂ በአባትነት ድርሻ ላይ አባታቸውን እንዲጠሉ ታደርጋለች የሚሉ ይገኙበታል። በተጨማሪም... የአባት ተቆራጭ ማስተካከያ ይደረግበት፣ በአስገድዶ መድፈር ሳብያ የልጅ አባት የሆነ ወንድ፣ ልጅ እንዲያሳድግ አይገደድ። ( አንድ ሴት ወንድን አስገድዳ ብትደፍር እና ብታረግዝ ተደፋሪው አባት ለልጁ ተቆራጭ እንዲያደርግ ይገደዳል) የመሳሰሉት...ይቀጥላል......
2 774
#Phenomenology ምንድን ነው??
#phenomenology ዓለምን በውስጣችን በሚፈጠሩ ስሜቶችና ሃሳቦች አማካኝነት እንዴት እንደምናውቅና እንደምንረዳ የምትመረምር የፍልስፍና ዘርፍ ናት። የዚህ ፍልስፍና መነሻ ሃሳብ እያንዳንዱ ግለሰብ ዓለምን በተለየ መንገድ እንደሚለማመድና እውነታውም በነዚህ ግላዊ ተሞክሮዎች የተገነባ እንደሆነ ማመን ነው። ፌኖሜኖሎጂስቶች አንድን ነገር ስንመለከት፣ ስንሰማ ወይም ስናስብ የሚሰማንን ስሜትና የሚፈጠሩብንን ሃሳቦች በመመርመር የእውነታውን ምንነት ለመረዳት ይጥራሉ። ስለዚህም ፌኖሜኖሎጂ እውነታን ከውጭ ሳይሆን ከውስጥ፣ በግላዊ ተሞክሮዎች አማካኝነት ለመረዳት የሚያግዝ የፍልስፍና መንገድ ነው።
2 774
ስለዘውገ ጾታ ማወቅ ያሉብን ነገሮች.
ፌምኒዝም የሚባለው ሀሳብ ብዙ ወንድ ጆሮው ሲደርስ ይከረክረዋል። በሀገራችን ብቻ ሳይሆን በሌላውም ሀገር ጾታ ላይ መሰረት ያደረገ አድማ ተብሎ ይታሰባል። «ሴቶች ተበደሉ ወይንም አልተበደሉም?» የሚለውን ጥያቄ ከማየት በፊት ታሪካዊ አውዶቹን በአግባቡ መረዳት ያስፈልጋል።
ሴት እህት፣ ሴት ጓደኛ፣ ሴት እናት እስካለን ድረስ በሴቶች ሰውነት ማመናችን ግዴታ ይመስለኛል። ሴቶች ሰዎች አይደሉም የሚል ምልከታ ካለ ጽሑፉ ሴቶች ሰው ናቸው ብሎ ስለሚጀምር ለእርሱ አይሆንም። ሴቶች ከወንዶች «እኩል ሰዎች» ናቸው ተብሎ ከታመነ ወንዶች የሚያገኙት የዜግነት መብት፣ እና ግዴታ እኩል መሆን አለበት። ይህ የፌምኒዝም መነሻ ትግል ነበር።
የመብት ተሟጋች እስከሆኑ ድረስ ከጥንት መነሻቸው አንስተው ሌሎች ተጨቁነዋል ላሉ ሰዎችም አብረው ሲቆሙ ነበር። ከእራሳቸው መብት በዘለለም የባርያ ንግድ ይቅር ባርያዎች ነጻ ወጥተው ከወንዶቹ እኩል መብት ይኑራቸው የሚል ሀሳብም ያቀነቅኑ ነበር። የመጀመርያው ፌምኒዝም በአጭሩ «ሰዎች ነን» የሚል ትግል ነበር። የፌምኒዝም ንቅናቄ «ምርጫ እንምረጥ፣ ትምህርት እንማር፣ ማህበራዊ ተሳትፎ ይኑረን፣ ድምጻችን ይሰማ፣ ጾታችን ላይ መሰረት ያደረገ ጥላቻ ንቀት ይቅር» የሚሉ መሰረታዊ ጥያቄዎችን አንግቦ ነበር። ዓላማቸው ይህ ቢሆንም የጥቁር ሴቶች መብትን ልክ እንደ ነጮቹ ሁሉ ትኩረት ሳይሰጡት አልፏል።
" aint I a woman " በሚል ድንቅ ስራ ብቅ ብትልም እንደነጮች ትግል አጋሮቿ ትኩረት አላገኘም ነበር። የመጀመርያው ፌምኒዝም ምንጭ የምትባለው ሜሪ ዎልስተንክራፍት ነች። " vindication of the rights of women " የሚል ተወዳጅ ስራዋ ለመጀመርያው ፌምኒዝም እንደ ጥንስስ አገልግሏል።በእሷ ስራ የተሳቡት እነ ኤልሳቤት ካንዲ ፣ማርጋሬት ፉለር በአሜሪካ የፌምኒዝም ታሪክ ውስጥ ፊት አውራሪዎቹ ናቸው። ይህቺ እንግሊዛዊት ጸሐፊ በፈረንሳይም የፌምኒዝም ሰዎች ነን እንቅስቃሴ መሰረት እንደጣለች ብዙዎች ይስማማሉ። በ 1848 ዓ.ም ቤተክርስትያን በተሰበሰቡ 200 ሴቶች ህብረት «12 የሰው እንሁን ጥያቄዎች» መሰረቱን የጣለው የመጀመርያው ፌምኒዝም በስኬት 1920 ሴቶች ለሰው የሚሰጠውን መብት እንዲያገኙ አድርጓል። ፌምኒዝምን በወጀብ(wave) ማዕቀፍ የሚያስቀምጡ ገለጻዎች ችግር ያለበት አካሄድ መሆኑ ብዙዎችን የሚያስማማ ነው። ስለ ፌምኒዝም ለማወቅ በወጀብ የሚያስቀምጡ ጽሑፎችን ከማንበብ ይልቅ የንቅናቄ መሪዎቹን ጥያቄዎች እና ጽሑፎቻቸውን ማንበብ mispresent እንዳናደርጋቸው ያደርጋል። «ፌምኒዝም» ሴቶች በየጊዜው በጾታቸው ምክንያት የሚያጋጥሙዋቸውን ችግሮች የመታገል ሂደት እንደሆነ ብዙ ጸሐፊዎችን ያስማማል።
እንግዲህ ሴቶች ሰዎች መሆናቸው ከታመነ ዘንዳ "the second sex" የሚል መጽሐፍ ይዛ አንድ ፈረንሳዊት ፈላስፋ ብቅ አለች። የመጀመርያው ፌምኒዝም ንቅናቄ ልክ እንደፓንዶራ ሳጥን ነበር።በወቅቱ ሴቶች ቤታቸው ይቀመጡ፣ የሴት ልጅ ተፈጥሮ መማር ሳይሆን ባልና ልጆቿን መንከባከብ ብቻ ነው የሚል ቋሚ ማኅበራዊ አመለካከት ነበር። ታድያ ይህቺ ፈረንሳዊት existentialist philosopher ሴት ይህንን አመለካከት «the second sex» ወይንም በአማርኛ ሁለተኛው ጾታ ትለዋለች። የሴትነት እና የወንድነት ሐላፊነት የሚበየነው በማህበረሰቡ ነው። ሴት ልጅ ወንድ የሆነውን፣ ያደረገውን ነገር ማድረግ ትችላለች። የወንድነት እና የሴትነት ሐላፊነቶች ማህበረሰባዊ መስመር እንጂ ሴቶች በተፈጥሯቸው የወንድ አገልጋዮች ሆነው አልተፈጠሩም የሚል ሀተታ አቀረበች። የፈረንሳይኛ ጽሑፏ ዘጠኝ መቶ ገጽ የተሻገረ ቢሆንም በእንግሊዝኛ መቶ ዘጠና ገጽ ተደርጎ ተተርጉሟል። እንደ «ሲሞን ዲ ቦቪር» ምልከታ ሴቶች እና ወንዶች በአይምሮ ማሰላሰል ብቃታቸው በመንፈሳዊ መረዳቃቸው እኩል ናቸው። ብዙ ሰዎች ይሄንን መጽሐፍ ሁለተኛው ዙር የሴቶች መብት ጥያቄ ትግል አስጀማሪ ነው ይሉታል። ታድያ በዚኛው የመብት ጥያቄ ዘመቻ የትግሉ አጠያየቅ ሁኔታ በሶስት ሊከፈል ተገዷል። 1) ለዘብተኛ ሴታዊነት ( liberal feminism) 2) አጥባቂ ሴታዊነት ( radical feminism) 3) ባህላዊ ሴታዊነት (cultural feminism) ብዙ ሰዎች «አጥባቂ ሴታዊነት» ላይ ጥያቄ አላቸው። «androgyny» ወንድ ጠል ንቅናቄ ነው በሚል ብዙ ሰዎች ከእራሳቸው ከሌሎች ሴታዊነት አቀንቃኞች እራሱ ጥያቄዎች ይቀርቡበታል። አጥባቂ ሴታዊነት ወንድ ላይ ያተኮረ ማህበራዊ ስሪት(patriarchy) መሰረዝ እንዳለበት አጥብቀው ያምናሉ። ለጊዜው እሱን ትተን ለዘብተኞቹ እና ባህላውያኑ ጋር እንሻገር።
ቤቲ ፍሪደን " The feminine mistique " በሚባለው ድንቅ መጽሐፏ «የሴቶች ጭቆና ከትግሉ ስኬት(ከመጀመርያው) በኋላ ወደኋላ እንደተመለሰ ታትታለች።ሴቶች ሰዎች መሆናቸው እውቅና ቢሰጥም፣ ሴቶች የእራሳቸውን ገቢ ለማግኘት ቢፈቀድላቸውም፣ ሴቶች ትምህርት እንዲማሩ ቢፈቀድላቸውም መሬት ላይ ግን እንዘጭ እንቦጭ ነው ትላለች። «ስም የሌለው ችግር» በሚል ንዑስ ርዕስ ስር ባተተችው ሀተታ መሰረት« ሴቶች ትምህርት እንዲማሩ የሚፈቀድላቸው ባሎቻቸው ረጅም እድሜ እንዲኖሩላቸው የሚያደርጉበትን ጥበብ፣ ወንድ ልጆቻቸው ዱርዬዎች እንዳይሆኑባቸው የአስተዳደግ ጥበብን ፣ ባልን የመንከባከብ ጥበብ፣ ከዙያም በዘለለ የሚሰሩት ስራ ቤት ለቤት የሚሰቀሉ የግርግዳ ጥበቦች፣ ኮሌጅ የሚገቡ ሴቶች አብዛኛዎቹ የወንድ ጓደኛ ለማግኘት እንደሆነ፣ በርትታ ትምህርቷን ብትጨርስ እንኳ አጣማጅ የማግኘቱ ተስፋ የመመናመን ስጋት እንዳለባት፣ በካንሰር ምክንያት ልትሞት ያለች እናት መዳኒት እንዳትወስድ እየተደረገ ልጇን ጡት እንድታጠባ እንደምትገደድ...ብዙ ብዙ ሰቆቃዎችን ደርድራ አቅርባለች። ከዚህም በተጨማሪ ሀገራቸው በሶቭየት ህብረት «የህዋ ትንቅንቅ» የተቀደመችው ሴቶችን ያላሳተፈ በመሆኑ ሊሆን እንደሚችል የሳይንቲስቶች ሀሳብ መሆኑን አቅርባ አትታለች። የሴታዊነት እንቅስቃሴ(Feminist) «ከሰው ነን ወደ እንስራ፣ እንለወጥ፣ የባሎቻችን እጅ ብቻ ጠባቂ» አታድርጉን ተቀየረ። ይሄንን ሁለተኛው ዙር(second wave) ብለው ይጠሩታል። ይቀጥላል . . . . . . . . .
2 774
ድርሰት ጥይት አይመክትም ፣ ሙዚቃም ፈንጂ አያከሽፍም ፤ አቅመ ቢስ ግን አይደለንም እውነታችንን በዜማ እናወራለን የውሸታሞችን ስም በገጸ ባህሪ እንስላለን የስነጽሁፍ ዓላማ ደምን ወደ ቀለም መቀየር ነው ።:- DEAD POETS SOCIETY MOVIE
2 774
ለሰነፍ ሰው የሚነገር በፅኑ እንቅልፍ ለተያዘ ሰው እንደሚነገር ነው ፥ ነግረኸው ከጨረስክ በኋላ " ምን ተናገርክ ይልሃል? " ብርሃኑ አልፏልና ለሞተ አታልቅስለት ፥ አይምሮ ጠፍቷልና ለሰነፍ ሰው አልቅስለት። ከሞቱ በኋላ አይመለስምና ለሞተ ሰው ታለቅስለት ዘንድ አግባብ ነው፤ ከሞቱ መኖሩ ይከፋበታልና ፤ ለሰነፍ በህይወት ሳለ አልቅስለት።፦ መፅሀፈ ሲራክ 22 ፥ 8-10
2 774
የሊነጋ ሲል ይጨልማል ስህተት
ከጥቂት አመታት በፊት ለሽርሽር በሄድኩበት ከተማ እያለሁ ታመምኩ። የበሽታው ምልክቶች ለእኔ አዲስ ሆኑብኝ፤ ህመሙም በየቀኑ እየጨመረብኝ ሄደ፡፡ በመሆኑም በአካባቢው ካለ የጤና ክሊኒክ እርዳታ ለመጠየቅ ወሰንኩና ሄድኩ፡፡ እንደደረስኩ ያገኘሁት ወጣት ሀኪም ይመረምረኝ ጀመረ። ሆዴን እያሻሸ፣ ጉልበቴን እና ትከሻዬን እየሳበና የጀርባ አጥንቶቼን እየደባባሰ ምርመራውን ቀጠለ፡፡ በሽታዬ ምን እንደሆነ መገመት እንኳን እንዳልቻለ ጠረጠርኩ፡፡ እርግጠኛ ግን አልነበርኩምና ይህን አዲስ ምርመራ ተቋቁሜ ዝም አልኩ፡፡ መጨረሻውን ለማብሰር በሚመስል ሁኔታ ማስታወሻውን አወጣና ‹‹አንቲ ባዮቲክስ በቀን ሶስት ጊዜ አንዳንድ ፍሬ ውሰድ። ሊሻልህ ሲል ሊብስብህ ይችላል፡፡›› አለኝ፡፡ አሁን ታክሜያለሁ በሚል ደስታ ከመድኃኒቶቼ ጋር ወደያዝኩት ሆቴል ተመለስኩ፡፡
ህመሙ ግን እየጨመረ በሚሄዱ ሁኔታ እየባሰብኝ ሄደ - ልክ ዶክተሩ እንደገመተው። እውነትም ዶክተሩ ችግሬ ምን እንደሆነ በሚገባ ተረድቶት ይሆናል። በሶስት ቀን ውስጥ አልቀንስልህ ሲለኝ ግን ደወልኩለት፡፡ በቀን የምትውጠውን ክኒን ወደ አምስት ከፍ አድርገው።ያው ለተወሰነ ጊዜ ትንሽ ያምሃል›› አለኝ፡፡ ከተጨማሪ ሁለት የስቃይ ቀናት በኋላ አንቡላንስ ጠራሁ። የስዊዙ ዶክተር በጥድፊያ መርምሮኝ ትርፍ አንጀት እንደሆነ አውቆ ቀዶ ጥገናውን ካደረገልኝ በኋላ፡ ‹‹ይሄን ያህል ለምን ዘገየህ?› አለኝ፡፡ «እየሆነ የነበረው በሙሉ ልክ ዶክተሩ እንደነገረኝ ስለነበረ አምኜው ነበር» አልኩት፡፡ እሱም ቀጠል አደረገና ««ኦህ የሊነጋ ሲል ይጨልማል ስህተት ሰለባ ሆነሃላ፡፡ ያ የክሮሲካ ዶክተር ምንም የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ በእርግጠኝነት ባንተ ላይ የሆነው ነገር በሌሎች በብዙ ቱሪስቶችም ላይ ሆኗል› አለኝ፡፡
ሌላ ምሳሌም እንመልከት። አንድ የድርጅት ስራ አስኪያጅ የሆነ ሰው በድርጅቱ ስራ መቀነስ ምክንያት አብዝቶ ይጨነቃል፡፡ የሽያጭ ሰራተኞቹ ስራ ተነሳሽነትም ይወድቃል። የሽያጭ ማነቃቂያ ዘመቻ ቢያስደርግም ምንም ውጤት ሳያመጣ ይቀራል። ለዚህ ችግር መፍትሄ ለመፈለግ በማሰብ በቀን 5,000 ብር የሚከፍለው አማካሪ ለመቅጠርና ችግሩን ለመፍታት ወሰነ፡፡ አማካሪውም መጠነኛ ምርመራ ካደረገ በኋላ ሽያጭ ክፍሉ ምንም ራዕይ የለውም፡፡ ብራንድህም በግልፅ አልተሰረዘም፡፡ ትንሽ የተወሳሰበ ነገር ነው። ላስተካክለው እችላለሁ፤ ነገር ግን ባንድ ምሽት የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ለማስተካከል የሚወሰዱት ነገሮች ጠንከር ያሉም ስለሚሆኑ ችግሩ ከመቀረፉ በፊት የሽያጭ መዳከሙ የተወሰነ ሊብስበት ይችላል›› የሚል ሪፖርት ለስራ አስኪያጁ አመጣለት፡፡
ስራ አስኪያጁም ሪፖርቱን ከተመለከተ በኋላ አማካሪውን ቀጠረው። ከዚያ በኋላ ባለው ሂደት የተቀጠረው አማካሪ ድርጅቱ እንደገመተው እየሄደ እንደሆነ እየደጋገመ ተናገረ። የሽያጭ ድቀቱ ግን ለቀጣዮቹ ሶስት አመት ሊስተካከል አልቻለም፡፡ ስራ አስኪያጁም አማካሪውን አባረረው፡፡
ይህ የሊነጋ ሲል ይጨልማል ስህተት የማረጋገጥ መድልዖ አንድ ዝርያ ነው፡፡ ችግሩ እየባሰበት ከሄደ የተገመተው ነገር ተረጋገጠ ማለት ነው፡፡ ችግሩ ባንድም በሌላ ምክንያት ከተስተካከለ ደግሞ ደንበኛው ደስተኛ ስለሚሆን ክብርና አድናቆትን ያተርፉበታል። ባለሞያው በሁለቱም መንገድ ያሸንፋል ማለት ነው፡፡
ለምሳሌ አንተ የሃገርህ ጠቅላይ ሚኒስተር ነህ እንበል። ሃገሪቱን እንዴት መምራት እንዳለብህ ምንም እውቀት እንደሌለህም እናስብ። ምንድን ነው የምታደርገው? ‹‹ከፊታችን ‹ከባድ አመታት ይጠብቁናል» ብለህ ዜጎች ቀበቷቸውን እንዲያጠብቁ ትጠይቃለህ፡፡ ከዚያም ከዚህ ሁሉ ችግርና ውጥንቅጥ በኋላ ወደ ጥሩ ሁኔታ እንደምትመልሳቸው ቃል ትገባለህ፡፡ በዚህ መንገድ የችግሩን መቆያ ጊዜ እና የችግሩን የግዝፈት መጠን ክፍት አድርገህ ትተዋለህ፡፡ ከዛም የከፉ ችግሮች ሲከሰቱ... ያለስቃይ የሚሆን ነገር የለም መጪው ጊዜ ብርሃናማ ይሆናል እያልክ የስልጣን ጊዜህን ታራዝማለህ ማለት ነው።
" ሊነጋ ሲል ይጨልማል " ወይም "ሊሻሻል ሲል ይብስበታል " የሚሉ ሀሳቦች ሲነገሩ አስተውል!! ነገሮች መጀመሪያ ወድቀው ከዚያ የሚሻሻሉባቸው ሁኔታዎች ቢኖሩም ተጨባጭ ምክንያቶች ሊኖራቸው ይገባል።አንዳንድ ፖለቲከኞች ሊያሰተካክሉት የማይችሉት ከፍተኛ የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚክ ቀውስ ሲከሰት ይህ ችግር ሀገሪቷን ያጠነክራታል ጨለማው የበረታው ሊንጋ ስለሆነ ነው ሲሉ ይስተዋላል ወዳጄ መሰራት ያለበት ስራ እስካልተሰራ ድረስ ጨልሞም ሊቀር ይችላልና አሰተውል ይህ የሊነጋ ሲል ይጨልማል ስህተት (The " It will get worse before it gets better" fallacy") ነው።✍ ሮልፍ ዶብሊ 📚 The art of thinking clearly
