Anchor Media -አንከር ሚዲያ
Open in Telegram
ለፈጣን መረጃ የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ፣ትክክለኛው የአንከር ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል❗
Show moreEthiopia9 274The category is not specified
2 305
Subscribers
-424 hours
-167 days
-16530 days
Posts Archive
ለመረጃ ያህል❗👇
ዶክተር ደብረፂዮን፣ አለም ገብረዋህድ እና ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ቅዱስ ፓትራያርኩ ትናንት ወደ መቀሌ ከመሄዳቸው በፊት እሁድ ዕለት በትግራይ ክልል ያሉ ዋና ዋና የሀይማኖት መሪዎችን ሰብስበው ነበር፣በዚህም የወልቃይት እና የራያ ጉዳይ እልባት ሳያገኝ ከኢትዮጵያ ተቋማት ጋር ግንኙነት እንዳታደርጉ ብለዋቸዋል ሲሉ ምንጮቼ ገልፀዋል። ትናንት ፓትርያርኩ ወደ መቀሌ ባመሩበት ወቅት ቤተመቅደስ ዘግተው መጥፋታቸው የሚታወስ ነው። ያው ከጀርባ ያለው ነገር ስለሚታወቅ ነው። ጳጳስ ለመሾም የምትፈልጉ ተብሎም በአደባባይ ማስታወቂያ አውጥተው ነበር።
ለትግራይ ህዝብ ግን ይሄ አይገባውም ነበር።
#“ከፋኖ ጋርአንዋጋም” ፦ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ!!!
የመከላከያ ሰራዊት አባላት “የፋኖ” ታጣቂዎችን “በመምከር ወደ ህዝባቸው እንዲመለሱ” እንዲያደርጉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጥሪ አቀረቡ።
የመከላከያ ሰራዊትን “ከፋኖ ጋር የሚያዋጋ አጀንዳ አለመኖሩን” ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናግረዋል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 4፤ 2015 በጅማ ከተማ በተካሄደው የሰራዊቱ የማዕከላዊ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ካሉ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግሮችን በማድረግ “ሰላም እንዲፈጠር” ማድረጉን ያነሱት ኤታማዦር ሹሙ፤ የ“ፋኖ” ታጣቂዎችን ጉዳይም ከዚሁ ጋር አያይዘው ጠቅሰዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ፤ “ፋኖ በሚል አማራ ክልል ላይ የነበረውን እንቅስቃሴ በአብዛኛው በሰላም ወደ ቤተሰቡ እንዲመለስ ያደረገው መከላከያ ነው። በጣም ብዙ ሺህ የፋኖ አባላት ነው የነበረው” ብለዋል።
በጫካ ከነበሩ የ“ፋኖ አባላት” መካከል፤ በሀገር ሽማግሌዎች እና በሃይማኖት አባቶች በተደረገ ጥረት “በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ” ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ኤታማዦር ሹሙ በዚሁ ንግግራቸው አስታውቀዋል።እኛ የቀሩትም እንዲመለሱ ነው የምንፈልገው።
ከፋኖ ጋር መዋጋት አንፈልግም ምንም አጀንዳ የለንም ከፋኖ ጋር የሚያዋጋን አጀንዳ የለንም” ሲሉም አክለዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት የፋኖ አባላትን በመምከር፤ “የሌላ መገልገያ እንዳይሆኑ፣ ወደ ህዝባቸው እንዲመለሱ” እንዲያደርጉም ጥሪ አስተላልፈዋል።
===[==========
ለወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇👇
http://t.me/anchoemediaa
በሰሜን ወሎ ዞን ጋዙ በስምሪት ላይ የነበሩ 6 የፀጥታ አካላት ከእነ ትጥቃቸው መጥፋታቸውን ምንጮቼ ገልፀዋል። እነዚህ ፖሊሶች ልዩ ሀይል የነበሩ እና በተሃድሶ የገቡ ናቸው ተብሏል።
የትግራይ ቴሌቪዥን ትናንት ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ መቀሌ ባቀኑበት ወቅት ምዕመናን ሰብስቦ በትግርኛ የሰራውን ዘገባ ትርጉም ይሄን ይመስላል👇❗👇👇🤔
"ሰይጣንን ከሚያመልክ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ጋር ህብረት የለንም፣ከመንበረ ሰላማ ጎን ነን!'' - ምእመናን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቋም በትግራይ ሕዝብ ላይ በተፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኗን ተቃውሟቸውን ገለጹ።
የተፈናቀሉ ወገኖች በተለይም የኢትዮጵያ ሲኖዶስ አባላትና አመራሮች በትግራይ ተወላጆች ላይ በደረሰው የዘር ማጥፋት ተግባር ላይ በግልጽ መሳተፋቸውን ገልጸዋል"ይላል ዘገባው።
👉 አባቶችን የሚያንቋሽሽ የተለያዩ ፅሁፎችን በመያዝ አባቶችን ለማሸማቀቅ ሞክረዋል። አሳዛኝ ነው።
ትርጉም👉@ayuzehabeshaofficial
♦ቅዱስነታቸው በመቐለ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ወደ ሚገኘው ቅዱስ ሚካኤል ደብር ለጸሎት ቢያመሩም፤ የቤተ ክርስቲያኑ በር ተዘግቶባቸው ቅዱስነታቸው እና የመሩት የሰላም ልዑክ በር ላይ ጸሎት ለማድረስ ተገደዋል።
ከደቡብ ጎንደር ደራ ወረዳ የተውጣጡ አርሶደሮች በባህርዳር በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የአፈር ማዳበሪያ ችግራቸውን አሰምተዋል።
በቆቦ ከተማ ከትናንት በስተያ ለሊት በሁሉም መውጫ በሮች አካባቢ ከለሊቱ 7:30 ላይ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ መኖሩን ትናንት መዘገቤ ይታወሳል።
በዚህም በፖሊስ ጣቢያው ላይ ሶስት ቦንብ የተወረወረ ሲሆን በዚህም በፖሊስ ጣቢያው ታስረው የነበሩ በርካታ እስረኞች እንዲያመልጡ ተደርጓል።
ንቅሳት ያለበት አዲስ አበባአይገባም🙉
ከስር ባለዉ ሊንክ አንብቡት👇👇
https://t.me/ayuzehabeshaofficial/12812
#የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል በአዲስ አበባ በርካታ “የአማራ ተወላጆች ታስረዋል” አሉ‼️
ጽንፈኛ” እና “ጸረ ሰላም” በሚል ከታሰሩ ከአስር ሺህ በላይ ግለሰቦች መካከል፤ “አብዛኞቹ የአማራ ተወላጆች” መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ተናገሩ።
ከየካ ክፍለ ከተማ ገዢው ብልጽግና ፓርቲን ወክለው የከተማይቱን ምክር ቤት የተቀላቀሉት ዶ/ር ካሳ ተሻገር ይህን ያሉት፤ ቅዳሜ ሐምሌ 1፤ 2015 እየተካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ በሰጡት አስተያየት ነው።
ዶ/ር ካሳ “የታሳሪዎች አያያዝ ሰብዓዊነትን ታሳቢ ያደረገ አይደለም” ሲሉም ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ምክርቤት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በፍርድቤት ሊከሰስ ነው!
ከሰሞኑ የአማርኛን የትምህርት ክፍልን እዘጋለሁ ብሎ በእነ ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በኩል የእውር ድንብር ውሳኔ ያሳለፈው ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በፍርድቤት ክስ ሊመሰረትበት እንደሆነ ተሰምቷል።
ዩንቨርስቲው አማርኛ ቋንቋን ጨምሮ የባህል ማዕከሉን የአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ታሪክ ጥናት ማዕከልን፣ ታሪክንና ሌሎች 18 ዲፓርትመንቶችን እዘጋለሁ በማለት ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም ዩኒቨርሲቲው ክስ ሊመሰረትበት መሆኑን እና በቅርቡ ፍርድቤት ሊቀርብ እንደሆነም ታውቋል።
#በህግ ጥላ ስር ያለን እስረኛ መረሸን በጣም ያሳዝናል‼️
ይህ ምስል ሰኔ 29/2015 ዓ.ም ማታ ላይ በአማራ ክልል ከባህርዳር ሰባታሚት ማረሚያ ቤት ሲያመልጡ ያዝናቸው በሚል ምክንያት በጥይት የተመቱ ልጆች ናቸው።
አጠቃላይ ሶስት እስረኞች ይህን እንደምክንያት በመጠቀም ተመተዋል ተብሏል።
ሰበር‼️
ትናንት ከመሸ በግምት 12:00 አካባቢ በመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ የጉምዝ ታጣቂዎች ማንነትን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈፀማቸውን በስፍራው የሚገኙ የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል። በርካታ ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀሩ ጠቁመዋል። የሰው እንቅስቃሴ የለም። ባስቸኳይ የፀጥታ ስምሪት ያስፈልጋል ሲሉ ምንጮቼ ገልፀዋል(አዩዘሀበሻ)።
ምንጭ👉@ayuzehabeshaofficial
'#በዚህ ሁሉ መዓት ሚሊዮኖች ተፈናቅለው ሚሊዮኖች ተርበው ግሽበት ሀገሪቱን እግሯን እያሽመደመደ!!!
@በየቦታው ግጭትና ዘረፋ በርክቶ አንድ መሪ ቤተመንግስት ልገንባ ካለ ይህ ጥልቅ የሆነ የስነአእምሮ ህመም ነው ይህ ሰው በጣም ታሟል። ''
@ከሰሞኑ የአንከር እንግዳ ሆነው የሚቀርቡ የስነልቦና ባለሙያ ከሰጡት አስተያየት የተወሰደ ነው ወዳጄ ጋዜጠኛ ዘሪሁን ተስፋዬ ስለሰውዬው ሲገልጽ የኡጋንዳውን ሰው በላ መሪ ያስታወሳል።
@ኤዲያሚን ዳዳ ድንገት የክብር ጠባቂ ጦሩን ይጠራና ታንክ ይዞ ካምፓላ አጠገብ የሚገኝ ተራራ ላይ ይወጣል ከዚያም ሚዲያዎቹን ጠርቶ 'የጎላን ኮረብታን ተቆጣጥረናል' ሲል ዜና ያስነግራል።
@አብይ ማለት ኤዲያሚን ዳዳን ቁርጥ ነው የደቀቀችና የረሃብ ጉንፋን የምታስል ሀገር አናት ላይ ጉብ ብሎ፥ ፓርላማውን ጠርቶ 'ብልጽግናን ጨብጠናል' የሚል ወፈፌ።
መሳይ መኮንን
ትናንት በአሰበ ተፈሪ አቅራቢያ መሳሪያ አስቀምጠው አካላዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ በነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ በኦነግ ሸኔ ጥቃት መፈፀሙን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም ከእነ ዩኒፎርማቸው በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በኦነግ ሸኔ ተገድለዋል። ምንጮች አያይዘው እንደገለፁት ከበባ ከፈፀሙ በኋላ ብሄር እየጠየቁ አማራ የሆኑትን ብቻ መርጠው እንደረሸኗቸው ገልፀዋል።
አላማጣ❗❗
በአላማጣ ከተማ በመጪው እሁድ "ለማንነቴ እሮጣለሁ" በሚል ከ3000 በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት ሩጫ ይካሄዳል ተብሏል።
አዩዘሀበሻ
"አንድ ትውልድ ለሌላ መስዋዕትነት ይዘጋጅ"
ይህን የተናገረው ጄኔራል ዮሐንስ ወልደጊዮርጊስ በመፅሀፍ ምረቃ መድረክ ያለው የተናገረው የአማርኛ ትርጉም❗👇👇
- የትግራይ ሉዓላዊ መሬት ተወሮ ባለበትና ተፈናቃዮች ባልተመለሱበት ሁኔታ ላይ እያወቁ ገና ለገና "የሰላም ተስፋ ተገኘ" ብለው የሚያጨበጭቡ ተጋሩዎችን ማየት ያሳዝናል
- ጠላቶቻችን እኛን ለማጥፋት ካራቸውን ስለው እየተጠባበቁ እንደሆነ ያልተረዱ ሰዎች አሉ።
- ጠላቶቻችን እኛን ለማጥፋት ሁሌም ዝግጁ ናቸው።የትግራይ ህልውናና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከፈለግን ጠላቶቻችን ዳግም እንዳይተናኮሱን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መደምሰስ አለብን።በየጊዜው እነሱ የለኮሱትን እሳት እያጠፋን መዝለቅ አንችልም። ለዚህ ስኬት ደግሞ ለመስዋዕትነት ዝግጁ የሆነ ትውልድ ያስፈልጋል።
ቢያንስ አንድ ትውልድ ለመስዋዕትነት ዝግጁ መሆን አለበት።
ሰበር❗❗ አሳዛኝ ነው❗
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዱ ዛሬ አመሻሹን በስራ ቦታው አቅራቢያ መገደሉን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልፀዋል።
ከስራ ሲወጣ መኪናው ውስጥ እንዳለ ነው 11 ሰዓት አካባቢ የተገደለው(አዩዘሀበሻ)።👇
ምንጭ👉@ayuzehabeshaofficial
በደጀን ወረዳ በዛሬው ዕለት የተገደሉት የወረዳው የፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለና ምክትላቸው ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ እነዚህ ናቸው።
የደጀን ከተማ ዋና ፖሊስ አዛዥ ዛሬ ተገድለዋል። በርካታ የፋኖ አባላትን በመጠቆም እና በማሳሰር ቀዳሚ ጠቋሚ እንደነበሩ ታውቋል።
በደቡብ ወሎ ደላንታ ወረዳ ኮረት እና ደንጎላት በሚባል አካባቢ ሰሞኑን ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ ነው የከረመው። በዚህ የተኩስ ልውውጥ ከሁለቱም በኩል ጉዳት የደረሰ ሲሆን እስካሁን ያልተነሳ አስኬረን ጭምር እንደለ እና የቆሰሉትም ወደ ወልደያ እንደተላኩ ምንጮች ገልጸዋል።
