Anchor Media -አንከር ሚዲያ
Open in Telegram
ለፈጣን መረጃ የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ፣ትክክለኛው የአንከር ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል❗
Show moreEthiopia9 274The category is not specified
2 305
Subscribers
-424 hours
-167 days
-16530 days
Posts Archive
የደብረ ማርቆስ ከንቲባ ኮበለለ።
የብልጽግና ሹማምንት ወደ ባህር ማዶ እየኮበለሉ ነው። ብልጽግናን ክዶ ከአገር የኮበለለው የደብረ ማርቆስ ከንቲባ አቶ ይትባረክ አወቀ ነው።
አቶ ይትባረክ በአንድ በኩል በሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረበት ሲሆን፣ በሌላ በኩል ለክልል ቢሮ ኃላፊ ሹመት ታጭቶ እያለ አሜሪካ መግባቱን ለማወቅ ችያለሁ።
በአቶ ይትባረክ አወቀ ቦታም አቶ መንበሩ ዘውዴ የደብረ ማርቆስ ከንቲባ ሆኖ ተሹሟል።
በቅርቡም ሌሎች ወታደራዊ እና የፖለቲካ አመራሮች አገዛዙን በመፀየፍ እንደሚኮበልሉ መረጃው ደርሶኛል።
🔥#ሰበር_ዜና‼️
#አርበኛ_ዘመነ_ካሴን ለመያዝ የፍርድቤት ማዘዣ ወጦ በአዲስ ኦፕሬሽን ለመጀመር የአገዛዙ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
ሆኖም የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነዉ አርበኛ ዘመነ ካሴ የሚከተለውን ብሏል"ይምጡ እና ይለይልናል ጫካውን ከከተማው በላይ አውቀዋለሁ ::እንተያያለን አስፈላጊ ከሆነ ሁሉን ነገር በሶስት ቀን አፈርሰዋለሁ‼️" ሲል አርበኛው መልዕክቱን አስተላልፏል።
ሸዋሮቢት❗❗
ሸዋሮቢት በአረጋይ ፀበል በኩል ውስቴቦይ አካባቢ በከባድ መሳሪያ ጭምር ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንዳለ ምንጮቼ ገልፀዋል።
Updated❗
በጎንደር ዙሪያ ማክሰኚት ከተማ ትናንት አንድ የፋኖ አባል በመታሰሩ ምክንያት ዛሬ ጠዋት በሌሎች የፋኖ አባላት ባልደረቦቹ ቅሬታ በመፈጠሩ ውጥረት ነግሶ እና የተኩስ ልውውጥ እንደተደረገ ከሰዓታት በፊት መዘገቤ ይታወሳል።
አሁን ላይ የታሰረው የፋኖ አባል ከእስር ተለቋል።
ረፋዱን በከተማዋ ነግሶ የነበረውንም ውጥረት ማርግብ ተችሏል።
ሰበር❗ጎንደር❗❗
በጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ከተማ ዙሪያ ፀዳ አለፍ ብሎ መገጭ ወንዝ ላይ ፍኖ እና አድማ ብተና ተኩስ ከፍተው ነበር። አንድ አድማ ብተና ፖሊስ ሞቷል ብለዋል።
መኪናቸውም ተመታ ቁማለች ሌሎችም አድማ ብተና ፖሊሶች አምልጠዋል ብለዋል።
ጉዳዩ ወደ ከፍተኛ ደም መፋሰስ እንዳያመራ ጥንቃቄ ያስፈልጋል ሲሉ የአዩዘበሻ ምንጮች ገልጸዋል።
የከተማው አመራር ሴት ልጁም ተወስዳለች ብለዋል።
ከጎንደር ባህርዳር መንገድ ተስተጓጉሏል።
በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ቀያ ገብርኤል
በዛሬው ዕለት በቀን 10/11/2015 አ.ም በዘረት እና ክምር ድንጋይ ቀበሌ የወረዳው ሚኒሻዎች ከአካባቢው ፋኖ ጋር ተኩስ ገጥመው ሶስት ሚኒሻዎች ተመተው መሀልሜዳ ሆስፒታል ይገኛሉ። ከቆሰሉት ሚኒሻዎች መካከል የወረዳው ምኒሻ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጣይወጣ ይገኝበታል ።
#ሰበር ዜና/ሼር ይደረግ
ለነገው የሚሊሻ ስልጠና መካነ ሰላም ሊገቡ የነበሩ ከ60 በላይ ፖሊሶች ትናንት ምሽት በጉዞ ላይ እያሉ መጥፋታቸው ታዎቀ
በዚህ ምክንያት ነገ ሊጀምር የነበረው የሚሊሻ እና የከተማ ፖሊሶች ስልጠና ወደ ሚቀጥለው ሳምንት መዛውሩን የውስጥ ምንጮቼ ገልፀውልኛል።
ከተለያዩ የጎጃም አካባቢዎች፣በተለይም ከመርጦ ለማሪያም፤ከቢቸና፣ከሞጣ፣ከግንደዎይን እና አካባቢዋ ትናት ተመርጠው ወደ መካነ ሰላም ለስልጠና ሊገቡ የነበሩ ከ60 በላይ የ32ኛ ዙር የፖሊስ አባላት ናቸው ይጓዙበት የነበረውን አውቶብስ በማስቆም በሙሉ ስርዓቱን ከድተው ትናንት አመሻሹን የጠፉት።
አስቀድመው "ወያኔ ስለወረረን ነው ስልጠና የምትገቡት" የሚል የሃሰት ማስረጃ ነግረዋቸው ነበር።ይሁን እንጅ ሰከስልጠናው በኋላ ከምስራቅ አማራ ፋኖ እና ከሸዋ ፋኖ ጋር ሊያዋጓቸው መሆኑን ሲያዉቁ"ከወንድሞቻችን ጋር እንዋጋም" በሚል በኋላ ነው ጥለው የጠፉት።
"ስልጠና ካልገባችሁ መሳሪያችሁን እንዎስድባችኋለን"ተብለው ለነገ ስልጠና እንዲዘጋጁ ተነግሯቸው የነበሩ ከ400 በላይ የሚሊሻ አባላት ገሚሱ "መሳሪያችንን ውሰዱ እንጂ፣ከፋኖ ጋር ልንዋጋ አንሰለጠንም"የሚል አቋም ይዘዋል።ገሚሱ ደግሞ ለነገ ስልጠና ዛሬ ምሽት ወደ እየተመደቡበት እንዲገቡ ቢነገራቸውም የት እንደገቡ አልታዎቀም ተብሏል።
የኦህዴድ ስርዓት አማራ ክፍለ ሀገር ላይ ባዶ ቀፎን ቀርቷል።ፋኖ ጠንክሯል፤ህዝቡ ከፋኖ ጎን ቆሟል፣ሚሊሻው እና ፖሊሱ እየከዳ ነው።
በትራፊክ አደጋ 9 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።
በትላንትናው እለት ከምሽቱ አራት ሰአት ገደማ በስልጤ ዞን ምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ በጃረሞ ሰምቦዬ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጀኔ ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሙሽራ አጅበው ሲሄዱ በነበሩ ኣጃቢዎች በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን 9 እድሜያቸው ከ30 በላይ የሆኑ ሴቶች መሞታቸው ተረጋግጧል።
በትራፊክ አደጋው ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች ሰዎች ሆሰዕና ንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንዳሉና የሞት አደጋውም ከዚህ ልያሻቅብ እንደምችል የምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሀባ አልዬ ገልፀዋል።
መረጃው የምዕ/አዘርነት በርበሬ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽ ነው
ሰበር❗
የደብረብርሃን ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ምንውየለት ጭንቅሎ በተለምዶ ሰማያዊ ሆቴል ፊት ለፊት ዛሬ 11:00 አካባቢ ደረታቸው አካባቢ በክላሽ ጥይት ተመተው ወደ ሆስፒታል ቢገቡም ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ነፍስ ይማር❗
ምንጭ👉@ayuzehabeshaofficial
ሰበር ዜና❗❗መድፍ❗❗
በቆቦ ከተማ ከ8:20 ጀምሮ የመድፍ ድምፅ አየተሰማ ይገኛል። እስከ አሁን 3 ጊዜ ተተኩሷል ብለዋል።
ቆቦ❗❗
በቆቦ ረፋዱን ምንም ተኩስ የለም፣ መንገድ ዝግ ነው፣ እንቅስቃሴ የለም።
ትናንት አየር ሀይል ቅኝት ማድረጉንም ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃት ፈፅሟል የተባለው ግን ስህተት ነው ብለዋል።
ምንጭ:- 👉ayuzehabeshaofficial
የጦር ጀት በቆቦ #ግርማካሳ
የብልፅግና ጦር በአማራ ክልል ህዝብ ልይ ጦርነት በይፋ የከፈተው ሚያዚይ 20 ቀን 2015 ዓ/ም ነበር:: ሁለት ተኩል ሆነው:: የአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ የብልፅግና ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ስምሪቶች አድርጏል::ከባባድ መሳሪያዎች: መድፍች: ዲሽቃ: ብሬል: ዙ23 የመሳሰሉትን:: ድሮኖችንም ሳይቀር ተጠቅሟል::
በሁሉም ቦታ ማለት ይቻላል ሽንፈት የተከናነበው የብልፅግና ጦር ሐሙስ ሐምሌ 7 ቀን በቆቦና አካባቢው ከምስራቅ አማራ ፋኖ ጋር ባደረገው ከባድ ውጊያ ለመጀመሪያ ጊዜ እነ ይልማ መርዳሳ የጦር ጀቶች ተጠቅመዋል:: የወልዲያና የአላማጣ ሆስፒታሎች በብልፅግና ወታደር ቁስለኞች ተሞልተዋል:: ከአላማጣ ጀምሮ እስከ ወልዲያ በጉቦ ላፍቶና ቆቦ ከተማን ጨምሮ በቆቦ ወረዳ የእገዛዙ ጦር ትልቅ ችግር ውስጥነው ያለው::
አገዛዙ በቆቦ ጥቃት የጀመረው: በዋናነት ራያን ለወያኔ ለመስጠት ስላሰበ: በአካባቢው ተቃውሞ ሊያሰሙ የሚችሉትን : የምስራቅ እማራ ፋኖን ትጥቅ ለማስፍታት እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ::
ይነበብ እና ሼር ይደረግ!
«አልሞት ባይ ተጋዳይ፣ የሞት የሽረት ትግል ነው እያደረግን ያለነው አሁን።» -ፋኖ አበበ ፈንታው_የምስራቅ አማራ ፋኖ
የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
የኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ በሰሜን ወሎ ራያ ቆቦ ያሰማራው ጦር በምስራቅ አማራ ፋኖ እና በቆቦ እና አካባቢው ማህበረሰብ ላይ ሀምሌ 6/2015 ከጠዋት ጀምሮ ሙሉቀን ጦርነት ከፍቶ ውሏል። በዚህ ጥቃትም በቆቦ መሀል ከተማ ላይ በመግባት መሳሪያ ባልያዙ ንጹሃን አማራዎች ላይ በተለይም በወጣቶች ላይ ግድያ ፈጽሟል።
አንደኛው የዐይን እማኝ እንደሚለው የአገዛዙ ጦር መሃል ቆቦ ከተማ ላይ በአምስት ወጣቶች ላይ ተኩሶ ባደረሰው ጉዳት ሁለቱ ወዲያውኑ ሲሞቱ ሶስቱነወደ ህክምና ተወስደዋል። ሌላኛው እንዳለው ካራንቡላ ሲያጫውት የነበረ አንድ ጠቋር የተባለ ወጣትን ተኩሰው ገድለውታል። ሴቶች እና ህጻናትም የጸረ አማራው ጥቃት ሰለባ ሆነዋል።
የብልጽግናው አገዛዝ ጦር በምስራቅ አማራ ፋኖዎች እና በህዝቡ የሚደርስበትን ጥቃት ባለመቻሉ እግሬ አውጭኝ እያለ ሲሸሽ ቢስተዋልም ያለ የሌለ ኃይሉን ከወልድያ እና ከራያ አላማጣ መስመር እያስመጣ መሆኑ መስተዋሉን ምንጮች ገልጸዋል።
አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) በራያ ቆቦ፣አራዱም ፣አሳመምቻ ፣ቀመሌ ተክለሃይማኖት ፣ጠዘጠዛ ፣ሮቢት እና ጎብዬ ዙርያ ባሉ አካባቢዎች የምስራቅ አማራ ፋኖ አዛዥ እነ ዋርካው ምሬ ወዳጆ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አበበ ፈንታው እና ሌሎችም የጦሩ መሪዎች ከህዝብ ጋር በመሆን የተከፈተባቸውን ጦርነት ለመመከት እና ለመቀልበስ እያደረጉት ስላለው ተጋድሎ ከምስራቅ አማራ ፋኖ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ከሆነው ከፋኖ አበበ ፈንታው ጋር ቆይታ አድርጓል።
ከፋኖ አበበ ፈንታው ንግግር ከተቀነጨቡ መልዕክቶች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል።
▪የኦሮሙማው ብልጽግና መንግስት በመከላከያ ሰራዊት ህግ ማስከበር በሚል ሽፋን በአማራ ህዝብ ላይ መደበኛ የሆነ ጦርነት ከከፈተ ሶስት ወር አልፎታል።*ህዝባችን በዚህ መዘናጋት የለበትም፤ ጦርነት፣ ኦፕሬሽን እንጀምራለን በማለት የሀገር ሽማግሌዎችን እያስፈራራ ከጀመረ ግን ሶስት ወር አልፎታል። በተሳካ መልኩ እየሄደላቸው ስላልሆነ ወደ ህዝብ እየተኮሰ ማንም ያሸነፈም ስለሌለ እስከ ዛሬ የተገፋ ህዝብ፣ ሀቅ የያዘ፣ እውነት የያዘ ህዝብ ነው፤ ይህንን የተከፈተበትን ጦርነት እየተጋፈጠ ያለበት ሁኔታ ነው ያለ። በሽምግልና ሲባል በሽምግልና እየገባ በደሉን እየቻለ ነገሮችን እያለፈ የነበረበት ሂደት አለ።
▪የምስራቅ አማራ ፋኖ ለመከላከያ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን “አንተ የሀገር ጠባቂ ነህ፤ እንደ ተቋም የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነህ። እኛም ራሳችን ከቤት ለቤታችን እናቶችም ከመቀነታቸው እየፈቱ ደመወዝ የሚከፍሉህ ሰራዊት ነህ። አትድረስብን፤ አንደርስብህም። ጠላታችን የብልጽግና መንግስት ነው። ይህ ስርዓት በህዝብ ተመርጫለሁ ቢልም ህዝብን በሰላም፣ በፍቅር፣ በአንድነት እንዲያስተዳድር ነውና ከዛ በዘለለ መንገድ ግን በአማራ ህዝብ ላይ በክልሉም ከክልሉ ውጭም ጦርነት ከፍቶ ያለበት ሁኔታ ስላለ አትድረስብን” ብለን ነበር ያው እንግዲህ አልሆነም።
የሚያዙት የአማራ ጠላቶች ናቸው፤ የኦሮሞ ብልጽግና ነው እያዘዘው ያለው መከላከያውን። የእነሱን ትዕዛዝ ተቀብሎ ዛሬ ማለዳ ሰራዊቱ የተወለደበትን አካባቢ ለቆ በርሃ ለበርሃ ነው እየተንከራተተ ያለው። ባለንበት ድረስ መጥተው ነው ተኩስ የከፈቱት ገበሬዎቹ አይተዋቸው ጥቆማ ሰጥተውን ነው ሰራዊታችንን ማትረፍ የቻልነው። አልሞት ባይ ተጋዳይ፣ የሞት የሽረት ትግል ነው እያደረግን ያለነው አሁን።
ከፋኖ ሰራዊት ጋር መዋጋት ሲያቅተው ወደ ከተማ እየገባ ንጹሃን ላይ እየተኮሰ ነው።
በሰሜን ወሎ ቆቦ ከባድ ውጊያ‼️
ጠዋት 12:30 አካባቢ የጀመረው ተኩስ ቀጥሏል። በቆቦ ከተማ ውስጥ እንዲሁም ዙሪያውን በተለይ ድንኳን ተራራ በሚባል ቦታ በዚህ ሰዓት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ ነው። አሁን ወደ ከተማዋ ውስጥ ገብቷል ፈንጅም ተወርውሯል። አንድ ወጣት ተመቶ ሆስፒታል ገብቷል ሲሉ የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል።
ጥንቃቄ‼️‼️‼️
ከመገናኛ ወደ ላምበረት በሚወስደው መንገድ እስራኤል ኤምባሲ አካባቢ የመሬት መንሸራተት በመከሰቱ ምክንያት መገናኛ አካባቢ ጭምር መንገድ ስለተዘጋ በዚህ አካባቢ የሚጓዙ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ እና እግረኞችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ትናንት በላሊበላ ከተማ አንድ የትራፊክ ፖሊስ ሶስት የባጃጅ ሹፌሮችን ፋኖ ናችሁ በሚል አቁስሏል። በዚህም በከተማው ያሉ የፋኖ አባላት በ24 ስዓት ውስጥ ለህግ ካላቀረባችሁ እርምጃ እንወስዳለን ስላሏቸው ወዲያውኑ በፖሊሶች እና በአድማ ብተናዎች በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል ሲሉ የመረጃ ምንጮቼ ገልፀዋል።
ሀምሌ 5 ሲታወስ❗❗❗
በመጀመሪያው ፎቶ ላይ የምታውት ሺ አለቃ ደጀኔ ማሩ ይባላል በዘመነ ወያኔ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ሀምሌ 5/ 2008 ዓ.ም በአጋዚ ኮማንዶዎች የተከበበት ወቅት ነው።
በዚህ ጊዜ ሺዓለቃ ደጀኔ :- ስንት ጥይት አለህ
ኮሎኔል ደመቀ :- የተወሰነ አለኝ
ሺዓለቃ ደጀኔ :- 1 ጥይት ጠረጴዛ ላይ አስቀምጥ በቀረው ጥይት ተዋደቅ፣ ጥይት ከጨረስህ ጠረንጴዛ ላይ ያስቀመጥካትን ጥይት ጠጥተህ ሙት፣ እጅህን በፍፁም እንዳትሰጥ እኔ ጠዋት እደርስልሃለሁ። እንዳለውም ኮለኔል ደመቀን እነዛን የአጋዚ ኮማንዶዎች ረፍርፎ ከእገታ አወጣው። የትግል ችቦውም ተለኮሰ። ህወሃትም ብዙ ሳትቆይ ወደ መቀሌ ሸከፈች❗
ይህ የሆነው ሀምሌ አምስት 2008 ዓ.ም ነው።
