Anchor Media -አንከር ሚዲያ
Open in Telegram
ለፈጣን መረጃ የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ፣ትክክለኛው የአንከር ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል❗
Show moreEthiopia9 274The category is not specified
2 305
Subscribers
-424 hours
-167 days
-16530 days
Posts Archive
በላሊበላ ከተማ ብልቱ የተቆረጠው ወጣት ህዝቡን አስቆጥቷል።
ዝርዝር መረጃው👇👇👇
https://t.me/ayuzehabeshaofficial/13876
በመቐለ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ‼️
በጦርነቱ ወቅት “የህወሓት አመራሮች ተጠቅመው ጣሉን” በሚል በመቐለ ከተማ ተቃቀወሞ ተቀሰቀስቅሷል ሲል የዘገበው አዩዘሀበሻ ነው።
የኦሮሚያ ልዩ ኃይል በሸዋ ፋኖዎች ቀምሶ ተመልሷል‼️‼️
ከትላንት በፊት ቅዳሜ ዕለት የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል ከሸኖ ከተማ ወደ አማራ ክልል በመንቀሳቀስ ከደብረብርሃን በቅርብ ርቀት ላይ ከምትገኘው አርብ ገበያ ላይ ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሞ ነበር። ለሁለት ቀን በፈጀው ውጊያ በርካታ ኃይሉን አስጨርሶ ዛሬ በዕለተ ሰኞ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ለመከላከያ ቦታው በመልቀቅ ወደ 10 መኪና የሚጠጋ ኃይሉን ይዞ ወደ መጀመሪያው ካምፑ ተመልሷል። በዚህ ሰዓት ሸኖ ከተማ ጉልት ሰፈር እና 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሰፍሮ ይገኛል።
ደራ ጉንዶመስቀል ዙሪያ በነበረው ውጊያ ፋኖ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ወስዷል። የጉንዶ መስቀል ከተማን ፋኖ ተቆጣጥሯል።
ሰበር❗
ደብረታቦር፣እብናት እና አካባቢ ከፍተኛ ተጋድሎ እየተደረገ ነው።
ደብረታቦር ዙሪያ ሙሉ ለሙሉ ኔትወርክ ተቋርጧል።
ቆቦ❗❗
በቆቦ ወረዳ ሮቢት ከተማ የመከላከያ አመራሮች እና የወረዳው አመራረ ስብሰባ አድርገው ሲመለሱ ልዩ ስሙ መንጀሎ በሚባል አካባቢ የደፈጣ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ታውቋል። በዚህም የመከላከያ አመራሮችን ጨምሮ ጉዳት ስለደረሰባቸው ወደ ወልዲያ ለህክምና ተልከዋል ተብሏል።
እልህ አስጨራሹ ውይይት❗❗❗
በጎንደር እና ባህርዳር ከተሞች ማህበረሰቡ ከመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች ጋ ውይይት አካሂዷል።በአዳራሹ የነበረው ህዝብ ሁሉም በሚባል ደረጃ ፋኖም መከላከያም የኛው ነው እሚል ድምፅ አሰምቷል።አማራ በሌሎች አካባቢዎች እንደ ዜጋ መብቱ ተከብሮ እንዳይኖር በዬ አቅጣጫው መሳደዱ፣መታረዱ፣መፈናቀሉ፣መዋከቡ አንሶ አሁን ደግሞ በራሱ ክልል በሰላም ወጥቶ እንዳይገባ በገዥው ብልፅግና እየተዋከበ እና ከወንድም መከላከያ ጋ ጥል እንዲፈጥር እየተደረገ በመሆኑ ጉዳዩ በውይይት እንዲፈታ ተሳታፊው ጥሪ አቅርቧል።
የተሳታፊዎቹ አንኳር ነጥቦች.....!!
~ብልፅግና በህዝባችን ላይ የከፈተውን ጥቃት ያቁም
~መከላከያ እና ፋኖ ከህዝባችን የወጡ አብራኮች ናቸው
~በራያ እና ወልቃይት ጉዳይ አንደራደርም
~በሌላ ክልል እሚኖረው አማራ መብቱ ሊከበር ይገባል
~መከላከያ የፓርቲ መጠቀሚያ ከመሆን ራሱን ያግል
~በወያኔ እና ኦነጋዊያን ፅንፈኞች የተከፈተብን የስም ማጥፋት ዘመቻ በአስቸኳይ ይቁም
~ ያለ ወንጀላቸው የታሰሩ የአማራ ተወላጆች ይፈቱ
ወዘተ የመሳሰሉ ወቅቱን የዋጁ ጥያቄዎችን በማንሳት በሁለቱ ከተሞች ከማህበረሰቡ የተውጣጡ ተወካዮች ከመከላከያ ሀላፊዎች ጋ ረዝም ያለ ሰአታት የፈጀ ውይይት አካሂደዋል።አሁንም የመከላከያ እና የፋኖ ሀላፊዎች የተፈጠሩ ችግሮችን በመወያየት በመነጋገር ሊፈቱ ይገባል።
ለሰላም መምጣት መፍትሄው ይሄው ነው !!
ከትናንት በስተያ በሰሜን ሸዋ ዞን በጣርማበር ከተማ አቅራቢያ ልዩ ስሙ ጉዶበረት በሚባል አካባቢ በአካባቢው በሚንቀሳቀስ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የደፈጣ ጥቃት ተፈፅሟል። በዚህ የተነሳ በአካባቢው የተኩስ ልውውጥ የተደረገ ሲሆን ዋናው መንገድም ለሰዓታት ተዘግቶ እንደነበር የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል።
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ማጀቴ ዛሬ ከጠዋቱ 11:00 ጀምሮ ከፍተኛ ውጊያ መኖሩን የመረጃ ምንጮቼ ገልፀዋል።
ባህርዳር❗❗👇
ትናንት ከባህርዳር በቅርብ እርቀት በምትገኘው መራዊ ከተማ አቅራቢያ በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መኪና ላይ በደፈጣ ጥቃት ተፈፅሟል ተብሏል። በዚህም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እና ሌሎች አመራሮች ለጥቂት አምልጠዋል ተብሏል። መኪናው ግን የተወሰነ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል።
ሰበር❗❗❗
ጠለምት❗❗
በጠለምት መከላከያ ሠራዊት የአካባቢውን አስተዳደር እየተረከበ መሆኑ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። ከየአካባቢው 15 ሰዎች ተዋቅረው የትግራይ ተፈናቃዮችን እንዲቀበሉ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ተብሏል። በዚህም በአካባቢው ነዋሪዎች በኩል ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል ተብሏል።
ምንጭ:-👉@ayuzehabeshaofficial
#አልተሳካም
• ፋኖን ትጥቅ እናስፈታለን ፤ ምስራቅ አማራ ፋኖን እናፈርሳለን ብለው ውግያ ጀመሩ ነገርግን አንድም ፋኖ ትጥቅ ማስፈታት አልተቻላቸውም።
• ልዩ ሀይሉን ተራ ፖሊስ ለማድረግ ሞከሩ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ "ከ 50% በላይ የሚሆነው የልዩ ኃይል ውሳኔውን በመቃወም ከነትጥቁ መጥፋቱን አመኑ።
• የተበተነውን ልዩ ሀይል ሰብሰበው ፖሊስ ለማድረግ በከፈቱት ዘመቻ ጉዳዩ የተገላቢጦሽ ሆኖ “አብዛኛዎቹ” ልዩ ሀይሎች ፋኖን እንደተቀላቀሉ አመኑ።
• የአቶ ግርማ የሺጥላን ሞት አስታከው ውግያ ከጀምሩ በኋላ መልሰው "ፋኖ ዘግናኝ የሚባል ጥቃት አደረሰብን የሚል እሪታ አሰሙ።
• አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከማወጃቸው በፊት በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የሚመራ ውግያ ጀመሩ በአስደናቂ ሁኔታ ጥቃቱ ተቀልብሶ ብአዴን ክልሉን ለቆ ፈረጠጠ።
• በ 3 ቀን እናጠናቅቀዋለን ብለው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ በአገሪቱ ካለው ሰራዊት ባሻገር በሶማሊያ ሰላም ሲያስከብር የነበረን ጦር ቢያመጡም አልተሳካም።
___
Fyi:- ፋኖ ለመጀመርያ ጊዜ "ዙ-23" ፣ "ሞርታር" እና "RPG" መታጠቅ የቻለው በአሁኑ ውግያ ማርኮ ነው። በተረፈ ብልፅግና ባለፉት 4 ወራት አንድም ያሳካው ግብ የለም።
ደንበጫ❗❗
ትናንት በደንበጫ ተንጫ ወንዝ ከፍተኛ ውጊያ ሲካሄድ ውሏል።
በዚህም ተንጫ ወንዝ ላይ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል፣የደረሰ ጉዳት ግን የለም።
ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ የአማራ ህዝብ ትግል ይቀጥላል አሉ::
ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ ከሰሞኑ በፀጥታ ሃይሎች የታሰሩትን ባለቤታቸውን ወ/ሮ መነን ሀሃይሌን እስካሁን ለማየት እንዳልተፈቀደላቸው ገልፀዋል።
ጀነራሉ ከአዲስ ድምፅ ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ አያይዘው ያነሱት ሌላኛው ጉዳይ የአማራ ክልሉ ወቅታዊ ሁኔታን ነው።
ጀነራል ተፈራ የብልፅግና አላማ አጠቃላይ የአማራን ህዝብ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ አስፈትቶ በምርኩዝ ማስኬድ ነው ብለዋል።
የአማራ ህዝብ የተከፈተበትን ጥቃት ነው የተከላከሉት ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ የመሳሪያ ብልጫ ስላለውም ንፁሃን ተጎድተዋል ሲሉ ገልፀዋል።
የአማራ ህዝብ መፍትሄ የሚያገኘው በትግል ነው ያሉት ጀነራሉ፣ መመራት ያለበት በራሱ ልጆች ነው ሲሉም ተደምጠዋል።
ጀነራሉ የአማራ ህዝብ ከጫፍ እስከጫፍ ተነቃንቋል ያሉም ሲሆን ዳር ሆኖ በመንጫጫት የሚመጣ ነገር የለም ብለዋል።
"መንግስት የወሰነው ውሳኔ የጎዳው ራሱን ነው፣ የአማራ ልዩ ሃይል ትጥቅ እንዲፈታ ሲወስን አማራ ትጥቅ በትጥቅ ሆኗል" ብለዋል።
ህክምና መከልከላቸው እንደቀጠለ መሆኑን አንስተው የእርሳቸው ችግር ግን የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ካለው ችግር እንደማይብስ ገልፀዋል።
ዘገባው የሮሃ ቲቪ ነው❗
“ፋኖ ከገመትነው እና ከገመገምነው በላይ ሆኖብናል!”
- ጠቅላይ ኢታማዡር ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮችን ሰብስበው የተናገሩት
“ፋኖ ትዕዛዝ የሚቀበለው ከማን ነው? ማጥቃት ሲኖርበት በአንድነት በአራቱም አቅጣጫ ጥቃት ይከፍታል። ማቆም ሲኖርበትም በአንድነት ፀጥ ይላል! ይሄን ኃይል ትዕዛዝ እየሰጠ ያለው አካል ማነው? ይሄ ኃይል ከገመትነው እና ከገመገምነው በላይ ሆኖብናል። የፀጥታ መዋቅራችንን በአንድ ሳምንት ከላይ እስከ ታች ሙሉ በሙሉ ብትንትኑን አውጥቶታል! አድማ ብተና ኃይላችንም 50 በመቶ ዲሞብላይዝ ሆኖብናል። መከላከያም እንደዛው! የፈጀውን ፈጅቶ ፣አሉ የተባሉ የቴክኖሎጂዎችንም ቢሆን ተጠቅመን ይሄን ኃይል እየመራ ያለ አካል ማወቅ ይኖርብናል። ጎበዝ አደጋ ላይ ነን!”
ህወሀት ከኦህዴድ ጎን በመሰለፍ በጎንደር ውጊየ ተሳትፈዋል❗❗
ከመሳይ መኮነን❗
ጎንደርን ለመያዝ ከየቦታው ሃይል ሰብስቦ የመጣው የአገዛዙ ሰራዊት መግባት አቅቶት አድፍጦ እየጠበቀ ሌሊቱን አሳልፏል። የፋኖ ታጣቂዎች የተሰዉ አባላትን የቀብር ስነስርዓት ሲፈጽሙ አርፍደዋል። ጎንደር የያዘችውን ይዛ ለሌላ ድል እጇን እያሟሸች ነው። በነገራችን ላይ በጎንደሩ ውጊያ ህወሀትና የመከላከያ ሰራዊት አንድ ላይ ተሰልፈው ነው ፋኖና ህዝቡን የገጠሙት። የማይካድራውን ጭፍጨፋ የፈጸመው የሳምሪ ገዳይ ቡድን አባላት በስደተኛ ስም ገብተው ከህወሀት ጎን በመሰለፍ በጎንደሩ ውጊያ ተሳትፈዋል። የቅማንትን ካርድ ለመሳብ የአብይ አገዛዝ ሰፊ እንቅስቃሴ ጀምሯል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በዚህ ጉዳይ ከህወሀቶች ጋር በቅርበት እየሰራ ነው። መከላከያ ብቻውን አቅቶታል ማለት ነው❗❗
አሁን ጎንደር ላይ ውጊያ ተከፍቷል። ይህን እየጻፍኩ የደረሰኝ መረጃ ነው። ሃይሉን አጠራቅሞ ዳግም የመጣው የአገዛዙ ሰራዊት ከተማዋ ላይ ከባድ መሳሪያ እየተኮሰ ነው። ተከታትዬ መረጃውን ይዤ እመለሳለሁ❗❗
