en
Feedback
Dilla Sport

Dilla Sport

Open in Telegram

Welcome to Dilla sport telegram channel Keep up to date with the latest news both man & woman dilla kenema FC and also s

Show more
366
Subscribers
-224 hours
+27 days
-130 days
Posts Archive
የጫወታ ውጤት ከፍተኛ ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የምድብ ሀ ይርጋጨፌ ቡና 0-0 ሞጆ ከተማ ዛሬ ህዳር2/2016 ዓ.ም የከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ የመጀመሪያ ሳምንት አምስተኛ ጨዋታ ቀን አስር ሰዓት ላይ
የጫወታ ውጤት ከፍተኛ ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የምድብ ሀ ይርጋጨፌ ቡና 0-0 ሞጆ ከተማ ዛሬ ህዳር2/2016 ዓ.ም የከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ የመጀመሪያ ሳምንት አምስተኛ ጨዋታ ቀን አስር ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም በይርጋጨፌ ቡና እና በሞጆ ከተማ ተደርጎ ዜሮ ለዜሮ በሆነ ውጤት ጨዋታው ተጠናቋል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በዘንድሮ አመት በከፍተኛ ሊጉ በመሳተፍ ላይ የሚገኘው ሞጆ ከተማም የመጀመሪያ ጨዋታውን አንድ ነጥብ በማግኘት ጨዋታውን አጠናቋል የምድቡ ቀሪ ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎች በነገው እለት ተደረጉ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች ፍፃሜ ያገኛሉ ➡️ቀን 8:00 ጅማ አባ ቡና 🆚 አዲስ አበባ ከተማ ➡️ቀን 10:00 ሀላባ ከተማ 🆚 ኢትዮ ኤሌትሪክ   

የጫወታ ቀን ወንዶች ከፍተኛ ሊግ 1ኛ ሳምንት ⚽ ይርጋጨፌ ቡና 🆚 ሞጆ ከተማ ⚽ ⌚️ 10:00 🏟️ አበበ ቢቂላ ስታድየም አዲስ አበባ

የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ኢትዮጵያ ከሜዳዋ ውጪ ማሊን 2-0 አሸንፋለች። - የመልሱ ጨዋታ እሁድ ህዳር 9 በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋል።
የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ኢትዮጵያ ከሜዳዋ ውጪ ማሊን 2-0 አሸንፋለች። - የመልሱ ጨዋታ እሁድ ህዳር 9 በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋል።

ከፍተኛ ሊግ | ይርጋጨፌ ቡና በበርካታ ዝውውሮች ራሱን ገንብቷል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪው ይርጋጨፌ ቡና አስራ ስድስት ተጫዋቾችን የስብስቡ አካል በማድረግ ውድድሩን ይጀምራል። በኢትዮጵያ ከ
ከፍተኛ ሊግ | ይርጋጨፌ ቡና በበርካታ ዝውውሮች ራሱን ገንብቷል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪው ይርጋጨፌ ቡና አስራ ስድስት ተጫዋቾችን የስብስቡ አካል በማድረግ ውድድሩን ይጀምራል። በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ስር የተደለደለው ይርጋጨፌ ቡና በውድድሩ ላይ ራሱን ጠንካራ ተወዳዳሪ ለማድረግ ቀደም ብሎ አሰልጣኝ አላዛር መለሠን የቀጠረ ሲሆን በሙከራ እና በቀጥታ አዳዲስ አስራ ስድስት ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ ቀላቅሎ ራሱን ለውድድሩ አዘጋጅቷል። በወላይታ ድቻ ፣ ደቡብ ፖሊስ እና ከምባታ ሺንሺቾ የሚታወቀው ግብ ጠባቂ መኳንንት አሸናፊ ፣ የአውስኮድ ግብ ጠባቂ የነበረው ቴዎድሮስ አካሉ ፣ ከአማራ ሊግ ውድድር የተገኙት የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቾቹ ሐይሌ ክፍሌ ፣ አገኘሁ ብርሀኑ እና ዘመድኩን ሺርኮ ፣ ከዶሬ ላንጋኖ የመጡት ተከላካዩ ጌታያውቃል ሮማን እና አማካዩ አየነው ሠለሞን ፣ ለፍኖተ ሰላም የተጫወቱት አማካዩ በረከት ታምራት እና አጥቂው ሔኖክ ሞገስ ፣ በኮልፌ ቀሬኒዮ ቆይታ የነበረው አማካዩ ተመስገን ኃይሉ ፣ በቦዲቲ የነበረው የመስመር አጥቂው ጌታሁን ሺርኮ ፣ ከሐረር ሲቲ የመጣው አጥቂው ልዑል ኃይሉ ፣ የቀድሞው የደቡብ ፖሊስ አጥቂ ይድነቃቸው ውበቱን ጨምሮ ከአካባቢው ፕሮጀክት አማካዮቹ ካሌብ ሽብሩ አማካይ እና አቤኔዘር ዘሪሁን እንዲሁም አጥቂእ ተስፋአለም ማሩ የክለቡ አዳዲስ ተጫዋቾች ሆነዋል። ይርጋጨፌ ቡና ነገ 10:00 ላይ ሞጆ ከተማን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በመግጠም የውድድር ዓመቱን ይጀምራል። ✍️ሶከር ኢትዮጵያ 

የ201 6የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ህዳር 1/2016 ዓ.ም ይጀምራል በሁለት ምድቦች ተከፍሎ የሚካሄደው የዘንድሮ ውድድር በሁለት የተለያዩ ከተሞች የሚደረግ ሲሆን የምድብ ሀ የመጀመሪያ ዙር ጨዋ
የ201 6የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ህዳር 1/2016 ዓ.ም ይጀምራል  በሁለት ምድቦች ተከፍሎ  የሚካሄደው የዘንድሮ ውድድር በሁለት የተለያዩ ከተሞች የሚደረግ ሲሆን የምድብ ሀ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች በአዲስ አበባ ከተማ አበበ ቢቂሊ ስታድየም የሚደረጉ ሲሆን ውድድሩም ነገ ረፊድ አራት ሰዓት ላይ ጅማ አባ ጅፋራ ከ ወልድያ ከተማ በሚያደርጉት የመክፈቻ ጨዋታ ይጀምራል። ውድድሩ እሁድም ቀጥሎ የሚደረግ ሲሆን በአሰልጣኝ አላዛር መለሰ የሚመራው ይርጋጨፌ ቡና ቀን አስር ሰዓት ላይ ሞጆ ከተማን የሚገጥም ይሆናል።

ውድ የይርጋጨፌ ቡና እግርኳስ ቡድን ደጋፊዎች ና ስፖርት አፍቃሪያን በሙሉ!!! ⚽️ ይርጋጨፌ ቡና🆚 ከሞጆ ከተማ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ 1ኛ ሳምንት ⚽️ይርጋጨፌ ቡና 🆚 ሞጆ ከተማ የፊታ
ውድ የይርጋጨፌ ቡና እግርኳስ ቡድን ደጋፊዎች ና ስፖርት አፍቃሪያን በሙሉ!!! ⚽️ ይርጋጨፌ ቡና🆚  ከሞጆ ከተማ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ 1ኛ ሳምንት ⚽️ይርጋጨፌ ቡና 🆚  ሞጆ ከተማ  የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ!! የጨዋታ ዕለት 🗓 እሁድ 02/03/016ዓም          🕣ሰዓት 10:00          🏟አዲስአበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም  በዕለቱ የሚያደርገውን ጨዋታ ሄዳችሁ መደገፍ የምትፈልጉ ባሉን ውስን ቦታ በእነዚህ ስልክ ቁጥሮች ማለትም  📞 0916428457 ወይም 📞 0993287581  በመደወል እንድትመዘገቡ እየገለጽን በዕለቱ ከዲላ እስከ አዲስአበባ የሚደረገው መሄጃ የትራንስፖርት ወጪ ነፃ ሲሆን፣ የመመለሻ 🍝ምግብ እና የአልጋ ወጪ ሙሉ በሙሉ ከኪሳችሁ የምትሸፍኑ መሆኑን አውቃችሁ ቅዳሜ ለሊት ልክ 11:00 ሰዓት በተባረክ ማደያ እንድትገኙ ተጋብዛችኋል ይላል የይርጋጨፌ ቡና የደጋፊዎች ማህበር።            

የ2016 የኢትዮጵያን ወንዶች ከፍተኛ ሊግ የእግርኳስ ውድድር በሁለት ምድቦች ተከፍሎ ህዳር አንድ ጅማሬው ያደርጋል የመጀመሪያ ዙር ውድድሮች የምድብ ሀ አዲስ አበባ ከተማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ሲደረ
የ2016 የኢትዮጵያን ወንዶች ከፍተኛ ሊግ የእግርኳስ ውድድር በሁለት ምድቦች ተከፍሎ  ህዳር አንድ ጅማሬው ያደርጋል የመጀመሪያ ዙር ውድድሮች የምድብ ሀ አዲስ አበባ ከተማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ሲደረግ የምድብ ለ ጨዋታዎች ደግሞ በሃዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ  በከፍተኛ ሊጉ በምድብ ሀ የተደለደለው ይርጋጨፌ ቡናም  የመጀመሪያ ጨዋታውን ከሞጆ ከተማ ጋር የሚደርግ ሲሆን ቡድኑ ከዚህ ጨዋታ በፊት ዘንድሮ በድጋሚ በተጀመረው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ላይ ጥቅምት 24 ጠዋታ አራት ሰዓት  ከነቀምቴ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።  

ጨዋታው ተጠናቋል 🏆:የ2024 የፓሪስ ኢሎምፓክ የሴቶች እግር ኳስ ሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ 🇪🇹 ኢትዮጵያ : 1-1 : ናይጄሪያ 🇳🇬 📅 : 14 ጥቅምት 2016 🏟 : አበበ ቢ
ጨዋታው ተጠናቋል 🏆:የ2024 የፓሪስ ኢሎምፓክ  የሴቶች እግር ኳስ  ሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ  🇪🇹 ኢትዮጵያ : 1-1 : ናይጄሪያ 🇳🇬 📅 : 14 ጥቅምት 2016 🏟 : አበበ ቢቂላ ስታዲየም 

የጨዋታ ቀን ! 🏆:የ2024 የፓሪስ ኢሎምፓክ የሴቶች እግር ኳስ ሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ 🇪🇹 ኢትዮጵያ : 🆚 : ናይጄሪያ 🇳🇬 ⏰ ፡ ከቀኑ 9፡30 ሰዓት 📅 : 14 ጥቅምት
የጨዋታ ቀን ! 🏆:የ2024 የፓሪስ ኢሎምፓክ  የሴቶች እግር ኳስ  ሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ  🇪🇹 ኢትዮጵያ : 🆚  : ናይጄሪያ 🇳🇬 ⏰ ፡ ከቀኑ 9፡30 ሰዓት 📅 : 14 ጥቅምት 2016 🏟 : አበበ ቢቂላ ስታዲየም  ጨዋታውን በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ዩቲዩብ ቻናል  በቀጥታ ስለሚተላለፍ ከስር ባለው ሊንክ በመግባት መከታተል ይቻላል  👉https://www.youtube.com/c/ethiopiaff 🇪🇹 ድል ለኢትዮጵያ ! 🇪🇹

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ውድድሮች የሚጀመርባቸው ቀናት በሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የማጣርያ ጨዋታ ምክንያት የቀን ሽግሽግ ተደርጎባቸዋል። በዚህም መሰረት
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ውድድሮች የሚጀመርባቸው ቀናት በሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የማጣርያ ጨዋታ ምክንያት የቀን ሽግሽግ ተደርጎባቸዋል። በዚህም መሰረት የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ጥቅምት 26 በጁፒተር ሆቴል ሲከናወን የውድድር መጀመርያ ቀን ኅዳር 16 መሆኑን የውድድር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል።

የኢትዮጲያ ከፍተኛ ሊግ እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የኢትዮጲያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ በ2016 ከአመታት መቋረጥ በኋላ በድጋሚ ተመልሷል በዚህም መሰረት ውድድሩ ስያሜውን ቀይሮ
የኢትዮጲያ ከፍተኛ ሊግ እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የኢትዮጲያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ በ2016 ከአመታት መቋረጥ በኋላ በድጋሚ ተመልሷል በዚህም መሰረት ውድድሩ ስያሜውን ቀይሮ  የኢትዮጲያ ዋንጫ በሚል ዘንድሮ እንደሚደረግ ተረጋግጧል ።  በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ተካፋይ የሆነው ይርጋጨፌ ቡናም የመጀመሪያውን ጨዋታ ከነቀምት ከተማ ጋር እንደሚጨዋታ ታውቋል።  

የ2016 የኢትዮጵያ ዋንጫ ይርጋጨፌ ቡና የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ከነቀምት ከተማ ጋር ያደርጋል።
የ2016 የኢትዮጵያ ዋንጫ ይርጋጨፌ ቡና የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ከነቀምት ከተማ ጋር ያደርጋል።

የ2016 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ጨዋታ ይርጋጨፌ ቡና የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ከነቀምት ከተማ ጋር ያደርጋል።
የ2016 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ጨዋታ ይርጋጨፌ ቡና የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ከነቀምት ከተማ ጋር ያደርጋል።

የ2016 ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የውድድር ዘመን የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ ጥቅምት 10/2016 ዓ.ም በጁፒተር ሆቴል ተካሂዶል። በዚህም መሰረት ይርጋጨፌ ቡና በምድብ ሀ ተደልድሏል በሁለት ምድቦ
የ2016 ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ  የውድድር ዘመን የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ ጥቅምት 10/2016 ዓ.ም በጁፒተር ሆቴል ተካሂዶል።  በዚህም መሰረት ይርጋጨፌ ቡና በምድብ ሀ ተደልድሏል በሁለት ምድቦች የሚደረገው የ2016 የከፍተኛ ሊግ ውድድር የመጀመሪያ ዙርን ጨዋታ ምድብ ሀ በአዲስ አበባ ከተማ ምድብ ለ ደግሞ በሀዋሳ ከተማ እንደሚደረግ ታውቋል።  

መስከረም 26/2016 በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ ባገናኘው ጨዋታ እና ሶስት አቻ በተጠናቀቀው ጨዋታ ዘንድሮ አፄዎቹን የተቀሊቀለው ጌታነህ ከበደ የ
+2
መስከረም 26/2016 በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ ባገናኘው ጨዋታ እና ሶስት አቻ በተጠናቀቀው ጨዋታ ዘንድሮ አፄዎቹን የተቀሊቀለው ጌታነህ ከበደ የመጀመሪያ ጎሉን ለክለቡ ፋሲል ከነማ አስቆጥሯል። የኢትዮጵያ የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ሁለተኛ ዙር የመጀመርያ ጨዋታውን ከሜዳው ውጪ ከኢኳቶርያል ጊኒ ጋር ያደረገው እና አንድ አቻ የተለያየው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ላይ የተካተተቺው እፀገነት ግርማ በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብታ ጨዋታዋን ማድረግ ችላለች። በሌላኛው የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታ በዘንድሮ አመት ቡድኑ በመረከብ ማሰልጠን የጀመሩት የመቻሉ በአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ የመጀመሪያ ጨዋታ ሙሉ ሶስት ነጥብ በማግኘት ጅማሮን አሳምሯል። ሀድያ ሆሳዕና ሁለት መቻል ሶስት።

በ2016 የውድድር አመት በኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪ የሆነው ይርጋጨፌ ቡና እግርኳስ ቡድን የመጀመሪያ ቀን የተጫዋቾች ምልመላ ዛሬ በዲላ ሁለገብ ስታድየም አድርጓል በዛሬው የምልመላ ፕሮ
በ2016 የውድድር አመት በኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪ የሆነው ይርጋጨፌ ቡና እግርኳስ ቡድን የመጀመሪያ ቀን የተጫዋቾች ምልመላ ዛሬ በዲላ ሁለገብ ስታድየም አድርጓል በዛሬው የምልመላ ፕሮግራም በ2015 በዲላ እና በይርጋጨፌ ከተማ በተደረገው ምልመላ ከተካፈሉ ስፖርተኞች ውጪ በርከት ላይ በዲላና በአካባቢው የሚገኙ ወጣት ስፖርተኞች በምልመላው ራሳቸውን ለማሳየት ጥረት አድርገዋል። ምልመላውም በቀጣይ ሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።

የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ 2016
የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ 2016

ምስጋና ሞያውን ለመሰሎቹ በማካፈል ሞያተኞችን ለማፍራት ጥረት በማድረግ የሚታወቀው አሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ያለፈውን ክረምት ወራት ለሀገሬ ዲላ ፕሮጀክት ለታዳጊ ቡድኑ ተከታታይ የእግር ኳስ ስል
ምስጋና ሞያውን ለመሰሎቹ በማካፈል ሞያተኞችን ለማፍራት ጥረት በማድረግ የሚታወቀው አሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ያለፈውን ክረምት ወራት ለሀገሬ ዲላ ፕሮጀክት ለታዳጊ ቡድኑ ተከታታይ የእግር ኳስ ስልጠና ፕሮግራም በማዘጋጀት ለቡድኑ ስልጥና ሲሰጥ የነበረው አስልጣኙ አሁን ደግሞ ለ2016 ለፕሮጀክቱ ለስልጠና የሚግዙ የመጫወቻ ኳሶችን ለታዳጊ ፕሮጀክቱ አበርክቷል። በዲላ ከተማ በቅርብ ጊዜ ከተመሰረቱ የእግርኳስ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው እና በቢኒያም ተሾመ የሚመራው ሀገሬ ዲላ ፕሮጀክት ለቀጣይ የስልጠና ጊዜው ቅድመ ዝግጅት ላይ ይገኛል። በዲላ ከተማ በአሁኑ ሰዓት ከተማውን በቀጥታ የሚወክል እና በከተማ አስተዳደር ስር ያለ ተወካይ ቡድን ባይኖር ለስፖርቱ ፍቅር እና ተነሳሽነት ባለቸው ወጣት አስልጣኞች የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ታዳጊዎችን በስፖርቱ ዘርፍ በማሰልጠን የማብቃት ስራን እየሰሩ ይገኛሉ እኛም በዲላ ስፖርት የፌስቡክ ገፅ ስም አሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ላበረከተው አስተዋጽኦ እንዲሁም በጣም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሆናችሁም ቢሆን በከተማው ስፖርት እንዳይዳከም ጥረት ለምታደርጉ ወጣት የእግርኳስ አሰልጣኞች ለሆናቹ በአጠቃላይ ከልብ እናመሰግናለን።

#ሽመልስ በቀለ ከ አስር ዓመት የግብፅ ሊግ በኃላ ወደ ሀገሩ ሊግ ተመልሷል ! "መቻል የውል ማፍረሻ በመክፈሉ ክለቡን ምርጫዬ አድርጌያለሁ "- ሽመልስ 👇 የዋልያዎቹ አምበል ሽመልስ በቀለ ያለፉትን
#ሽመልስ በቀለ ከ አስር ዓመት የግብፅ ሊግ በኃላ ወደ ሀገሩ ሊግ ተመልሷል ! "መቻል የውል ማፍረሻ በመክፈሉ ክለቡን ምርጫዬ አድርጌያለሁ "- ሽመልስ 👇 የዋልያዎቹ አምበል ሽመልስ በቀለ ያለፉትን አስር ዓመታት በግብፅ ቆይታን ካደረገ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ #ለመቻል እግር ኳስ ክለብ ፊርማውን አኑሯል። በግብፅ ሊግ በፔትሮጀት ፣ ኤል መካሳ ፣ ኤል ጉና እና ኢ ኤን ፒ ፒ አይ መጫወት የቻለው ሽመልስ በቀለ ቀጣዮቹን ሁለት ዓመታት በመቻል ለማሳለፍ ከስምምነት ደርሷል። ሽመልስ ከዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ስለተመለሰበት ምክንያት ለቲክቫህ ሲናገር "በግብፅ አሁንም ቢሆን እንደ አስዋን ፣ ሴራሚክ እና ዜድ ክለቦች ጥያቄ ቢቀርብልኝም ቀጣይ አመታቶችን ለቤተሰብ ቅርብ ሆኜ መጫወት ስለምፈልግ ወደ ሀገሬ ተመልሻለሁ " ብሏል። አያይዞም " መቻል እግር ኳስ ክለብ የተጠየቀውን የውል ማፍረሻ በመክፈሉ ክለቡን ምርጫዬ አድርጌያለሁ " ሲል " ወደ ሀገሬ መመለስ ስለፈለኩኝ በዚሁ ምክንያት መቻልን ተቀላቅያለሁ " ሲል ገልጿል። ሽመልስ በቀለ በግብፅ ቆይታው ከሰማንያ በላይ ጎሎችን ሲያስቆጥር በፔትሮጀት ክለብ ቆይታው ክለቡን በአምበልነት መምራትም ችሎ ነበር። ሽመልስ ወደ ግብፅ ሊግ ከማቅናቱ አስቀድሞ በሊቢያ ኢቲሀድ ትሪፖሊ እና በሱዳን ለአል ሜሪክ መጫወቱም የሚታወስ ነው።

አሰልጣኝ አላዛር መለሰ አሰልጣኝ አላዛር መለሰን የይርጋጨፌ ቡና የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን በዛሬው እለት ከክለቡ ጋር የፊርማ የማኖር ስነስርዓት አከናውኗል። አሰልጣኝ አላዛር
አሰልጣኝ አላዛር መለሰ አሰልጣኝ አላዛር መለሰን የይርጋጨፌ ቡና የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን በዛሬው እለት ከክለቡ ጋር የፊርማ የማኖር ስነስርዓት አከናውኗል። አሰልጣኝ አላዛር ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዚያት ደቡብ ፖሊስን በረዳት አሰልጣኝነት እንዲሁም በዋና አሰልጣኝነት ማሰልጠን የቻለ ሲሆን ለ2016 የውድድር አመት በኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪ ለሆነው ይርጋጨፌ ቡናን በዋና አሰልጣኝነት እንዲመራ ሀላፊነት ተሰጥቶታል፡፡