Dilla Sport
Open in Telegram
Welcome to Dilla sport telegram channel Keep up to date with the latest news both man & woman dilla kenema FC and also s
Show more366
Subscribers
-224 hours
+27 days
-130 days
Posts Archive
366
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ
ሶስተኛ ሳምንት የሙሉ ሰዓት ውጤት
ይርጋጨፌ_ቡና 0-3 አርባምንጭ_ከተማ
⚽️26' ፎዚያ መሀመድ
⚽️64' 84' ስርካለም ባሳ
366
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 3ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ህዳር 24/2016 ይጀምራሉ
በዚህም መሰረት ቀን አስር ሰዓት ላይ ይርጋጨፌ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።
መልካም ዕድል ለይርጋጨፌ ቡና
366
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 4ኛ ሣምንት የሁለተኛ ቀን የከሰዓት ጨዋታዎች ውጤት !
ምድብ ሀ - አበበ ቢቂላ ስታዲየም
- ሀላባ ከተማ 2-0 ይርጋ ጨፌ ቡና
70' ከማል አቶም
74' ፀጋ ከድር
366
ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ
የ2016 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ተጠናቋል
በእለቱ የተመዘገቡ ውጤቶች
ቅዱስ ጊዮርጊስ 1-3 ሀዋሳ ከተማ
መቻል 0-0 ሲዳማ ቡና
ንግድ ባንክ 3-1 ሀምበርቾ
ሊጉን ሁለቱንም ጨዋታዎችን መርታት የቻሉት ሀዋሳ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ በስድስት ነጥብ በጎል ተበላልጠው ሊጉን ይመሩታል።
የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች የፊታችን ህዳር 24/2016 ዓ.ም በሚደረጉ ጨዋታዎች የሚቀጥል ይሆናል።
366
ወንዶች ከፍተኛ ሊግ
የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ የእግርኳስ ጨዋታ የምድብ ሀ ሶስተኛ ሳምንት ዛሬ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ተጀምሯል
በዛሬው መርሃግብር መሰረትም ሶስት ጨዋታዎች ተከናውነዋል
ዛሬ የተመዘገቡ ውጤቶችን ስንመለከት:-
✔️ስልጤ ወራቤ 1-2 ሞጆ ከተማ
✔️ኮልፌ ቀራንዮ 0-1 ንብ
✔️አዲስ አበባ ከተማ 2-1 ቤንቺ ማጂ ቡና
የምድቡ ቀሪ 4 ጨዋታዎች ነገ ህዳር 22/2016 ዓ.ም ይደረጋሉ
3:30 ኢትዮ ኤሌትሪክ ከ ወልድያ ከተማ
5:30 ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ከ ነቀምቴ ከተማ
7:30 ሀላባ ከተማ ከ ይርጋጨፌ ቡና
9:30 ጅማ አባ ቡና ከ ጅማ አባ ጅፋር ጨዋታቸውን በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም ያደርጋሉ
366
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 2ኛ ሳምንት የዛሬ ውጤቶች
አርባምንጭ ከተማ 2-2 ድሬዳዋ ከተማ
ሰርካለም ባሳ እና ፎዚያ መሐመድ // ቃልኪዳን ጥላሁን (2)
☑️የጫወታው ኮከብ ቃልኪዳን ጥላሁን ከድሬዳዋ ከተማ
አዳማ ከተማ 4-0 ይርጋጨፌ ቡና
ሔለን እሸቱ፣ ርብቃ ጣሰው እና ሳባ ኃ/ሚካኤል (2)
☑️የጫወታው ኮከብ ሳባ ኃይለሚካኤል ከአዳማ ከተማ
ቦሌ ክ/ከተማ 3-1 ልደታ ክ/ከተማ
ትዕግስት ወርቄ ፣ ጤናዬ ለታሞ፣ አምሳል ፍሰሐ // ህድአት ካሡ
☑️የጫወታው ኮከብ ቃልኪዳን ቅንበሸዋ ከቦሌ ክ/ከተማ
366
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት የ8:00 ጨዋታ ውጤት
አዳማ ከነማ 4-0 ይርጋጨፌ ቡና
21' ሄለን እሸቱ
76' ርብቃ ጣሰው
79' 89' ሳባ ኃ/ሚካኤል
366
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ
ሁለተኛ ሳምንት ጨወታ
ተጠናቀቀ
ውጤት
አርባምንጭ 2-2 ድሬዳዋ ከተማ
37' ሰርካለም ባሳ 61' ፎዚያ መሐመድ |9' 85'ቃልኪዳን ጥላሁን
የሳምንቱ ጨዋታዎች ከሰዓትም ቀጥሎ የሚደረግ ሲሆን ስምንት ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከ ይርጋጨፌ ቡና እንዲሁም አስር ሰዓት ላይ ቦሌ ክ/ከተማ ከ ልደታ ክ/ከተማ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
366
🧠 + ⚽️ = ወገኔ ገዛኸኝ
👉 ብዙ ሰው እንዲያየው ጠቁሜው ያላሳፈረኝ።
👉 ከበፊት ጀምሮ በኔ ፌስ ቡክ ላይ በተደጋጋሚ እንደዚህ ልጅ በብዛት የተፖሰተ ተጨዋች የለም።
👉 አደለም 90 ደቂቃ ቀርቶ ሁለት ቀን ሙሉ ያለ እረፍት ሲጫወት ባየው የማይሰለቸኝ።
👉 ገና ከመድን ተስፋ ቡድን ጀምሮ ሲጫወት ያየሁት።
👉 ከለምለሚቷ ዲላ ከተማ የተገኘው።
👉 ከመድን ተስፋ ቡድን ወደ ዋናው ቡድን ባደገ አመቱ ለዋናው ብሔራዊ ቡድን የተመረጠ።
👉 በእግር ኳስ የ8 ቁጥር ቦታ ምን ምን እንደሚፈልግ በድንብ የገባው ወጣት።
👉 ከኳስ ጋር እና ከኳስ ውጪ ያለው እንቅስቃሴው ጥሩ ነው በተለይ ከኳስ ውጪ ያለው እንቅስቃሴ በጣም ይለይብኛል ለዛ ነው ከኳስ ውጪ ያለው እንቅስቃሴው በጣም ጎበዝ ስለሆነ በብዙ ሰው አይን ውስጥ መግባት ያልቻለው ቲፎዞ የሚበዛልህ ከኳስ ጋር ባለ እንቅስቃሴ ላይ ብቻ ጎበዝ ስትሆን ነው።
👉 ይሄ ተጨዋች ለብዙዎች በብዙ እርቀት ይለይብኛል።
👉 ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ እዮት ብያቹሀለው አሁንም ደግሜ ልጠቁማቹ እዮት ምን አልባት ደጋግሜ እዮት ብዬ የምጠቁማቹ ለልጁ ፕሮሞሽን ብዬ አይደለም ምክንያቱም እሱ አሁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋናው ቡድን ላይ ቤስት ሆኖ እየተጫወተ ነው በክለብ ደረጃም ከታች ለተስፈ ቡድን ላሳደው መድን ኢትዮጵያ ዋናው ቡድን ቤስት ሆኖ እየተጫወተ ነው እዮት እዮት የምለው እናተው አይታቹት በደንብ እንድትዝናኑበት ብቻ እና ብቻ ነው።
👉 የሚጫወተው ለመድን ኢትዮጵያ 18 ቁጥር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 21 ቁጥር መለያ ለብሶ ነው የሚጫወተው።
✍️ ከዚህ በፊት ከ10 ጊዜ በላይ ይሄን ስም እንዳትረሱት ብዬ ፖስቼ ነበር አሁንም ለ 11 ደኛ ጊዜ ይሄን ስም እንዳትረሱት (👉 ወገኔ ገዛኸኝ ) ከዲላ ምድር የተገኘ ድንቅ ወጣት ተጨዋች።
366
የ2016 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ተጀምሯል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል የሚካሄደው የ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዛሬ ረፋድ አራት ሰዓት ላይ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በነበረው ሀዋሳ ከተማ ከ የኢትዮ ንግድ ባደረጉት የመክፈቻ ጨዋታ ሲጀመር ጨዋታው በባለሜዳው ሃዋሳ 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል
የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ከተማ የሚከናወን ሲሆን ውድድሩ ከሰዓት በኋላም ቀጥሎ የእለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ልደታ ክ/ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ በሚያደርጉት ጨዋታ ሲቀጥል በነገው እለት ደግሞ አራት ጨዋታዎች ይካሄዳል
በዚህም መሰረት የሁለተኛ ቀን ጨዋታ በይርጋጨፌ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስ መካከል በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል
⚽️ ይርጋጨፌ ቡና 🆚 ቅ.ጊዮርጊስ ⚽️
🗓 ቀን 17/03/2016
⌚️ሰዓት ጠዋታ 3:00
🏟️ ቦታ ሃዋሳ ዩንቨርስቲ ስታድየም
መልካም ዕድል ለይርጋጨፌ ቡና
366
👉የጨዋታው ኮከብ #ዘላለም_አበራ
በትላንትናው እለት በተደረገው የከፍተኛ ሊግ ሶስተኛ ሳምንት የይርጋጨፌ ቡና ከ አዲስ አበባ ከተማ ዜሮ ለዜሮ በሆነ አቻ ውጤት በተጠናቀቀው ጨዋታ የይርጋጨፌ ቡናው የመሃል ተከላካይ ዘላለም አበራ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተመርጧል።
366
🇪🇹 ከፍተኛ ሊግ
ምድብ ሀ
3️⃣ኛ ሳምንት
⚽️ይርጋጨፌ ቡና 🆚 አዲስ አበባ ከተማ⚽️
🗓 ቀን ህዳር 11/2016
⌚️ ሰዓት 8:00
🏟️ ቦታ አዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም
ሶስተኛ ሳምንት ላይ የደረሰው የከፍተኛ ሊጉ ጨዋታዎች በነገው እለትም በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ሲቀጥል የእለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ በምድቡ በተመሳሳይ ነጥብ በጎል ክፍያ የሚበላለጡትን ይርጋጨፌ ቡናዎቹን ከአዲስ አበባ ከተማዎች ጋር ያገናኛል።
ዛሬ በተደረጉ የምድቡ ሶስት ጫወታዎች ሁሉም በአቻ ውጤት የተጠናቀቁ ሲሆን በነገው እለት የሚደረጉ ቀሪ የምድቡ ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
☑️የዛሬ ውጤቶች
ንብ 0- 0 ሞጆ ከተማ
ቤንቺ ማጂ ቡና 1-0 ስልጤ ወራቤ
ወልድያ 0-0 ኮልፌ ቀራንዮ
ቀጣይ ጨዋታዎች
☑️ህዳር 11/2016
8:00 ይርጋጨፌ ቡና 🆚 አዲስ አበባ ከተማ
10:00 ጅማ አባ ጅፋር 🆚 ኢትዮ ኤሌትሪክ
☑️ህዳር 12/2016
3:00 ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ 🆚 ሀላባ ከተማ
5:00 ነቀምት ከተማ 🆚 ጅማ አባ ቡና
መልካም ዕድል ለይርጋጨፌ ቡና
366
ከፍተኛ ሊግ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ የሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረገው እና ሀላባ ከተማ በጅማ አባ ቡና ሁለት ለዜሮ ከመመራት ተነስቶ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች አከታትለው ባስቆጠሩት ሶስት ጎል አሸነፈው በመውጣት የሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፍፃሜውን አገኝቷል
አሁን ባለው ጊዚያዊ ውጤት መሰረት ሁለቱንም ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው ኢትዬ ኤሌትሪክ በስድስት ነጥብ በ4 የጎል ክፍያ ምድቡን ሲመራ ይርጋጨፌ ቡና ወልድያ ቤንቺ ማጂ ቡና እና አዲስ አበባ ከተማ በተመሳሳይ 4 ነጥቦች ተከታዩን ደረጃ ይዘዋል
ሶስተኛ ሳምንት የምድቡ ጨዋታዎች ከሁለት ቀን እረፍት በኋላ የፊታችን ሰኞ ህዳር 10/2016 ይደረጋሉ
በዚህም መሰረት ቀጣይ ጨዋታዎች፦
☑️ህዳር 10/2016 ዓ.ም
⌚️4:00 ንብ ከ ሞጆ ከተማ
⌚️8:00 ቤንቺ ማጂ ቡና ከ ስልጤ ወራቤ
⌚️10:00 ወልድያ ከ ኮልፌ ቀራኒዮ
☑️ህዳር 11/2016 ዓ.ም
⌚️8:00 ይርጋጨፌ ቡና ከ አዲስ አበባ ከተማ
⌚️10:00 ጅማ አባ ጅፋር ከ ኢትዮ ኤሌትሪክ
☑️ህዳር 12/2016 ዓ.ም
⌚️8:00 ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ከ ሀላባ ከተማ
⌚️10:00 ነቀምት ከተማ ከ ጅማ አባ ቡና
366
እንኳን ደስ አላችሁ አሸንፈናል
ከፍተኛ ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታ
ይርጋጨፌ ቡና 2-0 ስልጤ ወራቤ
ረፋድ ሶስት ሰዓት ላይ በተደረገ የከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታ ቡናዎቹ ዱል አድርገዋል
የመጀመሪያውን ጉል ጨዋታው በተጀመረ ስምንተኛ ደቂቃ ላይ የመሃል ተከላካዩ ዘላለም አበራ ሲያስቆጥር ሁለተኛውን ጎል ደግሞ የጫወታው መጠናቀቂያ ላይ አማኑኤል ከበደ አስቆጥሮ ጨዋታው ተጠናቋል
ይርጋጨፌ ቡና ሶስተኛ ሳምንት ጨዋታውን የፊታችን ማክሰኞ ስምንት ሰዓት ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።
366
🏆| የ2026ቱ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ
🌍| 🇪🇹 ኢትዮጵያ 🆚 ሴራሊዮን 🇸🇱
🏟| በኤል አብዲ ስታዲየም
📅| ዕሮብ ህዳር 5 - 2016 ዓ.ም
⏰| ዛሬ ምሽት 4:00
💚💛❤️ ድል ለዋልያዎቹ 💛💚❤️
366
የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ አንደኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ፍፃሜውን አግኛቷል
አራት ጨዋታዎች በመሸናነፍ ሲጠናቀቁ ቀሪ ሶስት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል ምድቡን ነቀምት በሶስት ነጥብና በሁለት የጎል ክፍያ ምድቡን መመራት ሲጀምር የንብ ቡድኑ ተጫዋች ኪዳኔ አሰፋ እና የወልድያው ቢኒያም ላንቃሞ በሁለት ጎሎች ኮከብ ጎል አስቆጣሪነቱን ይሐሩታል
የምድቡ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች የፊታችን ሀሙስ ህዳር ስድስት ረፋድ ሶስት ሰዓት በሚደረጉው የስልጤ ወራቤና ይርጋጨፌ ቡና ጨዋታ ይጀምራል።
