cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትውልድን ለወንጌል🔊

አላማችን ትውልድን ለወንጌል በእውነተኛ አስተምህሮ አንጸን ማዘጋጃት ነው። ጥያቄዎችና አስታያየት ካላችሁ በታቹ ማስፈንጠርያ በመንካት ማድረስ ትችላላችሁ። @Ayalewwakeyo

Show more
Advertising posts
293
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

“ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቦአል። እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ፥”   — 1ኛ ጴጥሮስ 4፥7 ራእይ 22 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ ለእኔም፦ ዘመኑ ቀርቦአልና የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል በማኅተም አትዝጋው። ¹¹ ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ። ¹² እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ። ¹³ አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
Show all...
ይህ ሰው የኢየሱስን ስቅለት ታሪክ በብቃት ተውኗል። በፊልሙ ባገኘዉ ትምህርት ከአለማችን 200 ሚሊዮን በላይ ሰው በወንጌል ተደርሷል፣ ኢየሱስንም የግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል። የምያሳዝነዉ ግን በሀገራችን እና በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ይህ ሰውዬ ኢየሱስ ነው ተብሎ ተብሏል ይመለካል፣ ይሰገድለታል፣ ሻማ ይበራለታል፣ ይታጠንለታል፣ በየ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ላይ ተሰቅሏል፣ በየቤቱና በየመኝታ ክፍሉ መድሃኔዓለም ነው እየተባለ ተሰቅሏል። ስዕለ አድኖ በሚል የተሰቀለዉ የተዋናዩ ፎቶ ተገቢ አይደለም እስቲ በእግዚአብሔር ፍቅር እንጠይቃችሁ ቆም ብላችሁ አስተውሉ የዚህን ተዋናይ ፎቶ በቤታችሁ የሰቀላችሁ @superchristiantube7 @superchristiantube7
Show all...
የክርስቶስ ትንሣኤና የከፊል ሞት እሳቤ በወንድም ትንሣኤ ታሪክን ተጠቅመን በቀላሉ ማረጋገጥ ከምንችላቸው የክርስትና አስተምህሮዎች መካከል አንዱ የክርስቶስ ትንሣኤ ነው። በታሪክ ተመራማሪዎች ዘንድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደፈጸማቸው ጥርጥር የሌለባቸውን እውነታዎችን ብቻ ብንወስድና ብንመዝን ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ ለመደምደም የሚከለክለን አንዳችም ምክንያት አይኖርም። ከነዚህ እውነታዎች ውስጥ የክርስቶስ መሰቀል፣ መቀበር፣ በሦስተኛው ቀን የመቃብሩ ባዶ ሆኖ መገኘትና ብዙ ተከታዮቹ እንዳዩት መዘገባቸው ይጠቀሳሉ። ትንሣኤውን የማይቀበሉ ወገኖች ታዲያ እነዚህን እውነታዎች በሌላ መንገድ ለማብራራት ከመሞከር አልቦዘኑም። ከነዚህ መንገዶች አንዱ በኢ-አማንያን ተጀምሮ በሙስሊም አቃቤ እምነታውያን ሲስተጋባ የሚስተዋለው የከፊል ሞት ወይም ራስን የመሳት እሳቤ (Swoon Theory) ነው። በዚህ እሳቤ መሠረት ከሆነ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ራሱን በመሳቱ ምክንያት (ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ የእንቅልፍ መድኃኒት ወይም ማደንዘዣ ሰጥቶት የሚሉም አሉ) የሞተ የመሰላቸው ሮማውያን ቢቀብሩትም ከእንቅልፉ ነቅቶ ለሐዋርያቱ ተገልጦ በመታየቱ ከሞት ተነስቷል የሚለው ትምህርት ሊስፋፋ ችሏል። እንደ ዛኪር ናይክ እና አሕመድ ዲዳት ያሉ እውቅ ሙስሊም ሰባኪያን ጭምር ይህንኑ እሳቤ በማስተገባት ይታወቃሉ።[1][2] ይህ አመለካከት ግን ካለን ታሪካዊና ስነ-አካላዊ ማስረጃ ጋር ፈጽሞ የማይስማማ ነው። ኤድዋርድ፣ ጋቤል እና ሆስመር የተባሉ ሦስት ዕውቅ የጤና ባለሙያዎች በጥምር ባሳተሙት ጽሑፍ በዘመኑ ከስቅለት በፊት ይደረግ ስለነበረው የግርፋት ሂደት የሚከተለውን ይላሉ- “…የተለመዱት መግረፊያዎች አጭር ጅራፍና በተወሰነ እርቀት የብረት ወይም የአጥንት ቁርጥራጮች የታሰረባቸው ቁመታቸው የተለያዩ የሆኑ የቆዳ መቆንጠጫዎች ነበሩ። የሚሰቀለው ሰው ልብሱን ይገፈፍና ቀጥ ያለ እንጨት ላይ ይታሰራል፤ ጀርባው፣ እግሩና መቀመጫው ይገረፋሉ። የግርፋቱ አላማ ሰውየውን ለሞት ትንሽ እስኪቀረው ድረስ ማድከም ነው፤ የሮም ወታደሮች በሙሉ ኃይላቸው የሰውየውን ጀርባ በሚመቱበት ሰዓት የብረት ቁራጮቹ ሰውነቱ ላይ ጥልቅ ቁስል እንዲፈጠር ያደርጋሉ። አጥንቶቹም ቆዳውን በስተው በመጥለቅ ከባድ ጉዳት ያደርሳሉ።…” [3] ይህ እንግዲህ አንድ የሚሰቀል ሰው ከመሰቀሉ በፊት የሚፈፀምበት የማዘጋጃ ግርፊያ ብቻ ነው። አንድ ሰው ይህንን መሰል ግርፋት ተገርፎ በሕይወት ቢተርፍ እንኳን ለወዳጆቹ ተገልጦ ከሞት ተነስቻለው ብሎ ሊያስተምር ይቅርና ምሑራኑ እንደሚሉት “ቢያንስ ለአንድ ወር ያህል መራመድ አይችልም” [4]  ክርስቶስ እስከ ስቅለቱ ፍጻሜ ድረስ በሕይወት ነበረ ቢባል እንኳን በወንጌላት እንደምናገኘው ሮማውያን ወንጀለኞቹ እንደሞቱ ለማረጋገጥ ሲሉ የሰዎቹን ጭን መስበር አልያም ጎናቸውን በጦር መውጋት ያዘወትሩ ነበር። ይህንን ከወንጌላት ውጪ ማርከስ ቁንጥሊያኖስ የተባለው የአንደኛ ክፍለዘመን የሮም ጸሐፊ ዘግቦት ይገኛል።[5] ስለዚህ የክርስቶስ መሰቀል በራሱ የአተነፋፈስ ስርአቱ ላይ ከባድ ችግር ስለሚያስከትል በጦር መወጋቱ መሞቱን ፈጽሞ እንዳረጋገጠው መደምደም እንችላለን። ከላይ ያየናቸው ሦስት ምሁራንም ይህንኑ በመደገፍ እንዲህ ይላሉ፦ “የናዝሬቱ ኢየሱስ የሮምና የአይሁድ የፍርድ ሂደትን አልፏል፣ ተገርፏል፣ ተሰቅሏልም። ግርፊያው በቆዳው ላይ ስንጥቅጥቆችንና በዛ ያለ የደም ፍሰትን አስከትሏል። መስቀሉን እስከ ጎሎጎታ መሸከም አለመቻሉን አይተን መረዳት እንደምንችለው ግርፋቱ ልቡ ወደ ሰውነቱ ክፍሎች ደም መርጨት እንዳይችልና፣ ድካም እንዲሰማው አድርጎታል። የስቅለቱ ቦታ ላይ ሲደርስ እጆቹ ተቸንክረዋል፤ እንጨቱን ካቆሙት በኋላ ደግሞ እግሩንም ቸንክረውታል። የስቅለት ዋነኛ ዓላማ ትክክለኛ አተነፋፈስን መከልከል ነው፤ በዚህም ምክንያት ኢየሱስ በትንፋሽ እጥረትና በደም ፍሰት ሊሞት ችሏል። የኢየሱስ ሞት ወታደሩ ጎኑ ላይ ባስገባው ጦር እርግጥ ሆኗል፤ ያለን ታሪካዊ መረጃ በዘመናዊው የኅክምና ትምህርት ሲተነተን ኢየሱስ ከመስቀል ሲወርድ ሞቶ እንደነበር ያሳያል።”[6] ይኸው ጥናት ኢየሱስ (Most probably) በጦር ከመወጋቱ በፊትም ሞቶ እንደነበርና ማንኛውም አይነት የከፊል ሞት እሳቤ ከዘመናዊ የኅክምና ሳይንስ ጋር ፈጽሞ ሊስማማ እንደማይችል ይደመድማል።[7] የዚህን እሳቤ ደካማነት የሚያረጋግጠው ሌላው ነጥብ እሳቤው የተፈጠረበትን አላማ በቅጡ ማሳካት ያልቻለ መሆኑ ነው። የዚህ እሳቤ አቀንቃኞች ይህንን ሐሳብ የሚነዙት በዋነኝነት የኢየሱስን ለሐዋርያቱ መገለጥ ለማብራራት ነው። ነገር ግን ዴቪድ ስትራውስ የተባለ የ 19ኛ ክፍለዘመን ሊቅ እንደሚለው “አንድ ከሞት በከፊል ነቅቶ ድካምና ህመም እየተሰማው ኅክምና ሲፈልግ የነበረ ሰው ለደቀመዛሙርቱ “የሞት አሸናፊና የሕይወት ልዑል” እንደሆነ ሊያሳምናቸው ይችላል ብሎ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም”[8] በተጨማሪም መቃብሩን ይጠብቁ የነበሩትን ሮማውያን መርሳት የለብንም። ፖሊቢየስ የተባለ የታሪክ ጸሐፊ በጥበቃ ሰዓት ጥፋት ስላጠፉ ወታደሮች እንዲህ ይላል- “ግዴታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ ወታደሮች ‘ፉስታሪየም’ የተባለውን በድንጋይ የመወገር ቅጣት ይቀጡ ነበር። ከዚህ ድብደባ እንደምንም በሕይወት ቢተርፉ እንኳን ወደ ሀገራቸውም ሆነ ቤታቸው የመመለስ ምንም ተስፋ የላቸውም።”[9] ወታደሮቹ ላይ ከባድ ቅጣት ይጣል እንደነበረ ከወንጌላትም መረዳት ይቻላል (ማቴዎስ 28:14 ስራ 16:27)። ስለዚህ ለሮም ወታደሮች በስቅለትና ግርፋት አልፎ በቅጡ መራመድ እንኳን የማይችል ሰው ቋጥኝ አንከባልሎ ሲያመልጥ ተቀምጦ መመልከት ሕይወት ላይ መቆመር ነው የሚሆነው። ስናጠቃልል ይህ እሳቤ ሦስቱን የታሪክ እውነታዎች (የክርስቶስ መቀበር፣ በሦስተኛው ቀን ባዶ መቃብር ትቶ መነሳትና ለሐዋርያቱ መገለጥ) ከማረጋገጥ ባለፈ ትንሣኤው ላይ አንዳች ጥርጣሬ የሚጭር አይደለም። ማጣቀሻ [1] https://youtu.be/jICKPV5BJKQ [2] Ahmed Deedat, Crucifixion or Crucifiction , Chapter 16. [3] The American Medical Association, On the physical death of Jesus Christ, page 255. [4] Fredrick Zugibe, The Crucifixion of Jesus a forensic inquiry, page 161. [5] Marcus Quintilian , Declarationes Maiores , 6:9. [6] The American Medical Association, On the physical death of Jesus Christ, page 255. [7] Ibid. [8] David Strauss, The Life of Jesus for the people, Volume 1 page 412. [9] Polybius, The Histories, Volume 6 pages 36-37.
Show all...
FULL - Was Christ Really Crucified? Dr. Zakir Naik debates Pastor Ruknuddin

Show all...
CHURCH HISTORY

የክርስቶስ ትንሣኤና የከፊል ሞት እሳቤ በወንድም ትንሣኤ ታሪክን ተጠቅመን በቀላሉ ማረጋገጥ ከምንችላቸው የክርስትና አስተምህሮዎች መካከል አንዱ የክርስቶስ ትንሣኤ ነው። በታሪክ ተመራማሪዎች ዘንድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደፈጸማቸው ጥርጥር የሌለባቸውን እውነታዎችን ብቻ ብንወስድና ብንመዝን ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ ለመደምደም የሚከለክለን አንዳችም ምክንያት አይኖርም። ከነዚህ እውነታዎች ውስጥ የክርስቶስ መሰቀል፣ መቀበር፣ በሦስተኛው ቀን የመቃብሩ ባዶ ሆኖ መገኘትና ብዙ ተከታዮቹ እንዳዩት መዘገባቸው ይጠቀሳሉ። ትንሣኤውን የማይቀበሉ ወገኖች ታዲያ እነዚህን እውነታዎች በሌላ መንገድ ለማብራራት ከመሞከር አልቦዘኑም። ከነዚህ መንገዶች አንዱ በኢ-አማንያን ተጀምሮ በሙስሊም አቃቤ እምነታውያን ሲስተጋባ የሚስተዋለው የከፊል ሞት ወይም ራስን የመሳት እሳቤ (Swoon Theory) ነው። በዚህ እሳቤ መሠረት ከሆነ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ራሱን በመሳቱ ምክንያት (ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ የእንቅልፍ መድኃኒት ወይም ማደንዘዣ ሰጥቶት የሚሉም አሉ) የሞተ የመሰላቸው ሮማውያን ቢቀብሩትም ከእንቅልፉ ነቅቶ ለሐዋርያቱ ተገልጦ በመታየቱ ከሞት ተነስቷል የሚለው ትምህርት ሊስፋፋ ችሏል። እንደ ዛኪር ናይክ እና አሕመድ ዲዳት ያሉ እውቅ ሙስሊም ሰባኪያን ጭምር ይህንኑ እሳቤ በማስተገባት ይታወቃሉ።[1][2] ይህ አመለካከት ግን ካለን ታሪካዊና ስነ-አካላዊ ማስረጃ ጋር ፈጽሞ የማይስማማ ነው። ኤድዋርድ፣ ጋቤል እና ሆስመር የተባሉ ሦስት ዕውቅ የጤና ባለሙያዎች በጥምር ባሳተሙት ጽሑፍ በዘመኑ ከስቅለት በፊት ይደረግ ስለነበረው የግርፋት ሂደት የሚከተለውን ይላሉ- “…የተለመዱት መግረፊያዎች አጭር ጅራፍና በተወሰነ እርቀት የብረት ወይም የአጥንት ቁርጥራጮች የታሰረባቸው ቁመታቸው የተለያዩ የሆኑ የቆዳ መቆንጠጫዎች…

Hunda dura Gooftaa keenya Iyesuus  Kristoosiin isa nuuf jecha gad of deebisee dhimma keenya hunda dhiphatee fannifamuu isaatiin xumureef galanni dachaa dachaa isaaf haa ta'u. Itti aansuun baga guyyaa yaaddannoo du'aa ka'uu Gooftaa keenya Iyesuus Kristoosin maatii keessan waliin ittiin isin ga'e. Dhaamsa Koo ayyaana kanaan yeroo itti ayyaana dabalatan siniif haa ta'u, "Isa jiraataa maaliif warra du'an keessa barbaaddu?” Luq. 24:5 Obboleessa keessan
Show all...
🛑እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ዘርቶ ብዙ ልጆችን አጨደ:: እኛም ህይወታችንን ለእርሱ በመኖር መኸሩ ላይ በደንብ እነስራ እና ለብዙዎች መዳን በር እንሁን!!! “ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”   — ኢሳይያስ 53፥12 ▶️መልካም የትንሳኤ በአል
Show all...
1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁴ ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። ²⁵ እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።
Show all...
ቅዱስ ዮስጢኖስ ሰማዕት (Ἰουστῖνος ὁ μάρτυς/ Justin Martyr) ፦ የቤተክርስቲያን አቃቤ እምነት የነበረና የሰማዕትነትን ክብር የተቀናጀው ይህ አባት አባት በ100 ዓ.ም ተወልዶ በ165 ዓ.ም እንደ ሞተ ይገመታል። ይህ አባት ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦ <<የዓለማት ጌታ በሆነው በእግዚአብሔር በስመ አብ፣ በመድሐኒታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በውሃ መታጠብን ያገኛሉ>>
Show all...
አግናጢዮስ ዘአንጾኪያ (Ignatius of Antioch) ፦ የአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረና በ98 ዓ.ም ወይም በ117 ዓ.ም እንደሞተ የሚገመት ክርስትናን ከመናፍቃን በመከላከሉ ዙሪያ ብዙ የጻፈ ዐቃቤ ክርስትና ነው። ስለ ሥላሴ እንዲህ ብሎ ነበር፦ <<በእምነትና በፍቅር፤ በወልድ፣ በአብና በመንፈስ ቅዱስ፤ በመጀመሪያው እና በመጨረሻው፤ ከሚያስደንቅ ጳጳስችሁ ጋር እናም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካሉ ዲያቆናት ጋር በሚገባ በጠበቀ መንፈሳዊ አክሊል የምታደርጉትን ሁሉ በስጋና በመንፈስ እንዲከናወን በጌታችንና በሐዋርያት ትምህረት እድትጸኑ አጥኑ። ክርስቶስ ኢየሱስ ለአብ በስጋው እንደተገዛለት እናም ሐዋርያት ለክርስቶስ፣ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ እደሚታዘዙ እናንተም ለጳጳሳችሁ እና እርስ በእርሳችሁ ተገዙ(ታዘዙ) በዚያን ጊዜ በስጋችሁም በመንፈሳችሁም አንድነት ይኖራችኋል።>>
Show all...
. "አማላጄ" ዘማሪ በረከት ተስፋዬ 〰〰〰〰〰〰〰 የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው የጌታዬ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው የሰው ዘር ሁሉ የአዳም ስህተት ይዞት ወደቀ ወደ ጥፋት 2x ማንም እንዳይድን ይሄን ቢረዳ ሊከፍለው መጣ ለሃጥያት እዳ የሃጥያት ደሞዝ ነውና ሞት ሞቴን ሞተልኝ ሰጠኝ ህይወት ሃጥያት ተሻረ ከኔ ላይ በፈሰሰልኝ ጎልጎታ ላይ ቀራንዮ ላይ በገዛ ደሙ እርቅ አወረደ የጠፋሁትን ስለወደደ ሃጥዕ ተብዬ ስም ለወጣልኝ በደሙ አንፅቶ ጻድቅ አስባለኝ ከደጉ አባቴ አሁን ታረቅኩ በቅዱስ ደሙ ስለታጠብኩ ሌላ አማላጅ ሳያስፈልገኝ በቀኙ ሆንኩኝ ደሙ አቀረበኝ የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው የጌታዬ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ የማን ጸሎት ነው የሚያስታርቀኝ የኢየሱስ ደም ያላነፃኝ የማን ጸሎት የሚያነፃኝ የኢየሱስ ደም ሳያስታርቀኝ የማን ምልጃ  የሚያስታርቀኝ የኢየሱስ ደም ያላጠበኝ የማን ምልጃ  የሚያጥበኝ ያስታረቀኝ ከአባቱ አማላጅ የሆነልኝ ስለሃጥያቴ ጥብቅና በአብ ፊት የቆመልኝ የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው የጌታዬ ደም ዛሬም ትኩስ ነው 2x አማላጄ ነው ለሆንኩት ለኔ ለሞት ፍርደኛ በአብ ቀኝ ያለ አንዱ ብቸኛ ስለበደሌ እሱ ነው ዋሴ የሚቆምልኝ ልክ እንደ ራሴ መሰላል ያየው ያዕቆብ በህልሙ መካከለኛ ነው ክቡር ደሙ ሰማይ ከኔ ጋር እርቅ ያደረገው በማንም አይደል በኢየሱስ ደም ነው ያስታረቀኝ ከአባቱ አማላጅ የሆነልኝ ፣ ስለሃጥያቴ ጥብቅና በአብ ፊት የቆመልኝ 🎼🎼  𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚  🎼🎼 https://t.me/+I6ZkQ0gvdw00Mjc0 @ye_Protestant_mezemur ─── ❖ ──  ✦ ── ❖ ───
Show all...