የሰው ቅኔ
Open in Telegram
🎯ዓላማ፦ ማወቅ፣መረዳትና መተግበር... ⨳ከምለቃቸው ፅሁፎች የተለዬ ሃሳብ ብላችሁ የምታስቡት ነገር ካለ በዚ @yesewkene መፃፍ ትችላላችሁ⨳ @yesewqene
Show more648
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-530 days
Posts Archive
648
ግጥም
አስደግማብኝ ነው...
ለሰባት ጠንቋይ ልጅ ለደብተራ ምርኩዝ
ጠጠር ገበጣ አርጋ ላኬር ዕጣው እርኩዝ
"ይቺን ያየ' አስብላ
መሬት ልታስገባ ድቼ ልታስበላ
የስር ማሽ እንጉዳይ
የኮከብ ቆጣሪ
የነ መገን ቦቃ
የነ ጥና ጠሪ
ያንደርቢ ቁጣ
የአመድ ላይ ዘዋሪ
የመዳፍ አንባቢ
የሞራ መርማሪ
ለመቃብር አፈር
መንገድ ላይ ቀጣሪ
መተተኛ ፍቅር
ልብ ላይ ቀባሪ
የቀን ስደተኛ
አርጋኝ የሌት ዟሪ
አቅሌን እያሳተች
ምታስብለኝ እሪ
አስደግማብኝ ነው...
አስደግማብኝ ነው "በርሶ መጀን" ብላ
"ላሜ ላቴ ዱርዱራ ገደፈሬ ኡብዝራ
ጮርቃ ጩቃ ገጠ ለፌ ሊስ መላሌ ወአክናፌ"
"በርሶ መጀን" ብላ
የልቤ ሳይበቃት
ልቦናዬን በልታ
ጨፌ እየነከሰች
በጉልበት ተደፍታ
ኩራቴን ልትነጥቀኝ
ኮርታ ልትማታ
ተማ'ታም ልትረታ...
ጥላዬን ጀማው ፊት
መሬቱ ላይ ዘርታ
"ያዙልኝ" እያለች
በጠንቋይ ቱፍታ
መለመላ ነፍሴን
ወናየን ዘርግታ
"ታሞ ይኑር" ብላ
እኔን አስወግታ
እርጋታዬን ነጥቃ
እኔን ከኔ አጣልታ
በደብተራው ምርኩዝ
ባስነካችው ኩታ
እንዳነክስላት
ጅስሜን አስመትታ
ህልሜን እንዳልሰማ
ልቤን አስደምታ
አስደግማብኝ ነው
''ናልኝ'' ብላ ጠርታ
የሆንኩ አንገት ደፊ
የሆንኩት ከርታታ
መለየት ያቃተኝ
ቀኑንና ማታ
አስደግማብኝ ነው...
አስደግማብኝ ነው
ለነ ጥላ ወጊ
ለመጫኛ ነካሽ
ለነ አፍዝ አደንግዝ
ለዱር ቅጠል በጣሽ
ላውልያ ለጠንቋዩ
ለኑግ ቂጣ ቆራሽ
ለመንገድ ገርጋሪ
ለውቃቢ ዘራሽ
ለገሃድ ስውሩ
ለነ ጽናት አፍራሽ
ለምድር ላየሩ
ለየሎስ አጎንባሽ
ለባሕር ለየብሱ
ለጠቋሪት ደጋሽ
አስደግማብኝ ነው
ወለም ያላለኝን ዘላለም የምታሽ
አስደግማብኝ ነው👨🦯
-ሰለምን ሳህለ
@yesewqene
648
°ምነው ከፋሽ??
ምነው አፈርሽ??
ያለበሽው ቀሚስ ሰፋሽ??
°ስላንቺ ቀና ባለ ፊትት፡
ስለለምን አንገትሽን ደፋሽ?
ለምን??
°እርቃኑን ፊትሽ ከቆመ፣
እቅፍሽን ጠባቂ ወንዴ፣
°እርቃንሽን ፊቱ መቆምሽ፣
ለሐፍረት ይሰጣል እንዴ?
°ስለምን ሀዘን ተሰማሽ?
°ስለምን እራስሽን አማሽ?
°ሰው መሆን አንዱ ላንዱ ነው፣
ሰውነት የጋራ ድፍድፍ
°ሂወቱን ፆሞ ማያቅ ሰው፣
ምናላት አንዲት ቀን መግደፍ?
ስለምን ሰላምሽን አጣሽ?
ስለምን እራስሽን ቀጣሽ?
°የሰው ሰውነቱ..
አብሮ አንድላይ መንቃት፡
አልያ አብሮ ማሸለብ፣
°ፃድቅ አያሰኝም-
ባልንጀራን ቀድሞ፡
እራስን መለብለብ፣
°እራቁቱን ላለ..፡
እራቁት ገላሽን-ኑሮ ለሚመጥን፣
°ስሜት ክር መጠንጠን..
ባልጋ ቤቱ እጣን-ቤተ መቅደስ ማጠን፣
°ፅድቅ እኮ አይደለም
እሺ ብሎ አውልቆ እንዳዲስ ማውጠንጠን❕
°ታድያ ለምን ዝም አልሽ?
እጅሽ አፍረትሽ-ላይ አሁን ምን ያረጋል?
°ችላ ሲሉት እኮ..
አይደለም ይህ ምሽት-የሰው ሌት ይነጋል።
°ተይ ነጋብን ሌቱ.......
°ዝሙት ሀጥያት አበይ
ሌላ ነው እውነቱ፣
°በዚ እርቃን ገላሽ
አንዴ እቀፊኝ እንጂ
አይደለም ያንቺ ልብ-ይደሰታል ቤቱ
ምነው??
ማፈር ነካሽ??
°ሐፍረቱን ለሸጠ
በግልብ ድፍረቱ-ለጠየቀሽ ወጣት፣
°አይደለም መከልከል..
ለመከልከል ማሰብ-እሱ ራሱ ሐጥያት❕
ምኞት ነክቶን ነበር
ምኞት ደርሶን ነበር
°ይኸውልሽ ውዴ
በሌለ እሳት ላይ፡
ምድጃ ማራገብ-ቤትን አያሞቅም፣
°ምኞት ተነካክቶ...
ስሜት ላይ መራመድ፡
በግብር ላይ ማፈር-ፈፅሞ አያፀድቅም።
ምነው??
ከፋሽ??
https://t.me/Ewuket_bet
648
ተለይተህ ስትገኝ እብድ ነህ።ፈጠን ስትል ነቀልህ ተበለህ ትዋከባለህ። እንዳትቀበለው ደግሞ ስህተትህን ለማረም የመጣ ሃሳብ ሳይሆን ተለይተህ መገኘትህን የሚኮንን በመሆኑ ነው። በልዩነትህ የተነሳ ነቀልህ የሚልህ እሱ አንድ ቦታ ቆሞ ነው። አንተን የሚበልጥህ አለመንቀሳቀስ በመቻሉ ብቻ ነው። የለውጥ ስሜትን መገደብ በመቻሉ ብቻ ተለይተህ መገኘትህ ላይ የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማህ የማድረግ ጥረት ነው። እርምት እንዳትለው ተሳሳትህ የተገኘኸው በመለየትህ ብቻ መሆኑ ነው። አንተን መረዳት ሲያቅተው በሽተኛ የሚልህ ሰው መሀል መኖር በራሱ በሽታ ነው። ሳትታመም ያሳምምሀልል፤ ነቀልህ የሚልህም ለማረም ሳይሆን ልዩነትህን የመጥላት በሽታ ምልክት ነው። አንተው ለተከልከው የገዛ ሕይወትህ ነቀልህ ለሚልህ ሰው መልሱ አንድ ብቻ ነው፦
ብነቅልም ራሴ የተከልኩት ሕይወት ነው፡፡@yesewqene
648
ከዛሬ 6 ቀን በፊት በ Instagram
ገፁ ላይ ይሄንን ፅሁፍ አጋርቶ ነበር
post link:
https://www.instagram.com/p/DTYTAYrCMXk/?igsh=MXg2NG9zc2h3YjN2dA==
648
ህይወት ዥዋዥዌ አንዴ ግራ አንዴ ቀኝ "የቱ ጋ ነህ?" ብሎ ጊዜ ሲጠይቀኝ መሃል ተቀምጬ ምን ልሁን ጨነቀኝ የቱ ጋ ህኜ ነው ሙቀቱ ሲበርደኝ ብርዱ የሚሞቀኝ-በረከት ዘውዱ @yesewqene
648
"በአፍላ ትጀምራላችሁ በወረት ትተውታላችሁ። ያወቃችሁትን ትረሳላችሁ፣ ያላወቃችሁትን ለማወቅ ትጥራላችሁ፤ የያዛችሁትን ትረግጣላችሁ፤ የረገጣችሁትን ትይዛላችሁ። ምኞታቸሁ ልክየለውም፤ አምሮታችሁ ብዙ ነው። የአማራችሁን ስታገኙ ወዲያው ይሰላቻችኋል። ተው የተባላችሁትን ትሽራላችሁ፤ የተከልከላችሁትን ትደፍራላችሁ፤ የተፈቀደላችሁን ችላ ትሉታላችሁ። ቤተ መቅደስ እንዳትገቡ ብትከለከሉ ወደ ፊት ቤተ መቅደሱን በመስታዎት ሠርታችሁ መቅደስ ባትገቡም እንኳን ሁሉን ከውጪ ሆናችሁ ማየት ትፈልጋላችሁ። ሁሉን ማወቅ ትፈልጋላችሁ፤ በአንዱም ግን አትጠቀሙበትም። ሁሉ አላችሁ፤ ግን ባዷችሁን ናችሁ። ሃይማኖት እንጅ እምነት የላችሁም!" ቀጠሉ አባ ሰውነታቸው እንደ ቅኔ ዘራፊ በስሜት ይናጣል...
@yesewqene
