650
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+3630 days
Posts Archive
Repost from ABGS GRADE 9
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼ቀን 2/13/2018
የተከበራችሁ ወላጆች ፣የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንዲሁም የትምህርት ቤታችን መምህራንና ሰራተኞች ከወዲሁ እንኳን ለ2019 ዓ/ም አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ።
እንሆ የ2019 የትምህርት ዘመን የሚጀምረው መስከረም 04/01/2019 ዓ/ም መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል ስለሆነም ሁሉም ተማሪዎች ፣ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ወላጆች በመክፈቻ መርሃ ግብሩ እንድትገኙ በታላቅ አደራ ጥሪያችንን እናቀርባለን !
መልካም አውደ ዓመት !
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌼🌼🌼🌼🌻🌻🌻🌻🌻
Repost from ABGS GRADE 9
ቀን 2/13/2018
የተከበራችሁ ወላጆች ፣የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንዲሁም የትምህርት ቤታችን መምህራንና ሰራተኞች ከወዲሁ እንኳን ለ2019 ዓ/ም አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ።
እንሆ የ2019 የትምህርት ዘመን የሚጀምረው መስከረም 04/01/2019 ዓ/ም መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል ስለሆነም ሁሉም ተማሪዎች ፣ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ወላጆች በመክፈቻ መርሃ ግብሩ እንድትገኙ በታላቅ አደራ ጥሪያችንን እናቀርባለን !
መልካም አውደ ዓመት !
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!
በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/
የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።
ውድ ወላጆች እንደምን ቆያችሁ?
ከዚህ በፊት በላክነው መልክት ልጆቻችችንን የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎችን ከሁሉም ቅርንጫፍ በጋራ ይዘን ሄደን ጉብኝት ምናደርግበት ቀን ጳጉሜ አንድ ስለሆነ እስከ ነሀሴ 29 ድረስ ትላንት በለጠፍነው መልክት ላይ ባስቀመጥናቸው ስልኮች እየደወላቹ እንድትመዘገቡ በድጋሚ እንጠይቃለን።
<iframe src="https://www.google.com/maps/embed?pb=!1m18!1m12!1m3!1d3796.8184332469805!2d38.710066974845724!3d9.019723291041215!2m3!1f0!2f0!3f0!3m2!1i1024!2i768!4f13.1!3m3!1m2!1s0x164b87ebe984882b%3A0x46c02d79581465bf!2zSG9sbGFuZCBQYXJrIOGIhuGIi-GKleGLtSDhjZPhiK3hiq0!5e1!3m2!1sen!2set!4v1788264762222!5m2!1sen!2set" width="600" height="450" style="border:0;" allowfullscreen="" loading="lazy" referrerpolicy="strict-origin-when-cross-origin"></iframe>
ውድ ወላጆች እንደምን ቆያችሁ?
ሰሞኑን ልጆቻችንን በክርምቱ መውጫ
ከነሐሴ 29 እስከ መስከረም 3
የተዘጋጀ ዓውደ ርዕይ ላይ እንዲታደሙ በሐመረ ብርሃን ግብዣ ቀርቦላቸው እንደነበር ይታወሳል።
ልጆቻችን የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች በመሆናቸው የመግቢያ ቲኬቱ
ከ500 ብር ታላቅ ቅናሽ ተደርጎ 300 ብር
እንደረደረገላቸው ያሳወቅናችሁ ሲሆን ይህ የሚሆነው ዓውደ ርዕዩን
በጋራ ሂደን ስንታደም ብቻ
ነውና ሁላችሁም ወላጆች ልጆቹ የዚህ ታሪካዊ ዓውደ ርዕይ ተካፋይ መሆን አለባቸው ብላችሁ ካሰባችሁ ከታች ባሉት ስልኮች ደውላችሁ ክፍያ በመፈጸም ቦታ ማስያዝ እንደምትችሉ እናሳውቃለን። ከሁሉም የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፎች የሚነሱ መኪናዎች ስላሉ በመረጣችሁት ቅርጫፍ መኪና መሳፈር ትችላላችሁ፤ትችላላችሁ፤ ውድ ወላጆች
ቦታ ለማስያዝ ስትደውሉ የመረጣችሁትን ቅርንጫፍ እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።
ቅናሹ የሚሠራው በጋራ በመኪና በተያዘው ቀን ለሚመጡ ተማሪዎች ብቻ እንጂ በግል ጉዞውን ለሚመጡ ቤተሰቦች ስላልሆነ
እስከ ቅዳሜ ነሐሴ 29 ድረስ
ብቻ ደውሎ በማስመዝገብ ይህን እድል እንድትጠቀሙ እንጠይቃለን።
☎️ 0913332445 ማርታ ዓለሙ / ወይራ ቅርንጫፍ/
☎️ 0988470647 ሳባ ዓለም / መሪ እና ሰሚት ቅርንጫፍ/
☎️ 0911921383 ሰለሞን ዘለቀ / ለቡ ቅርንጫፍ
☎️ 0912635036 ዐይን አበባ /ቃሊቲ ቅርንጫፍ/
☎️ 0911660911 ሐይማኖት ቃኘው / አዋሬ እና እግዚአብሔር አብ ቅርንጫፍ/
☎️ 0943172425 ሶስና ተስፋው / 22 እና ሰንሻይን ቅርንጫፍ/
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል።
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ።
ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡
በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል።
የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 👇
https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements
ሰላም በስኩል ኦፍ ቱሞሮው ክላስተር ማዕከል የውጤት ማላቂያ የክረምት ትምህርት ተሳታፊ የሆናችሁ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በዚህ ሳምንት ትምህርቱ ስለሚጠናቀቅ (22/12/2018) ቀሪ ሶስት ቀናትን በአግባቡ ተከታትላችሁ እንድታጠናቅቁ ማስታወስ እንወዳለን
🟣በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
🟢ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።
🔵ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው።
🟠ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው
🟪ከፍተኛ ውጤት !
በተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ 591.6 ከ600 ተመዝግቧል። ተማሪው የኦዳ ስፔሻል ቦርዲንግ - አዳማ ተማሪ ነው።
ከሴት ደግሞ 583 ከ600 ሲሆን ከእንጅባራ አገው ምድር ትምህርት ቤት ነው።
• 576.25/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ወንድ — ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት
• 569/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ሴት
ዋና ዋና መረጃዎች
🌔565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
🌔 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች
• አምና — 62
• ዘንድሮ — 88
🌍 በፈተና አሰጣጥ ዘዴ
• በኦንላይን የተፈተኑ — 18.37% አልፈዋል።
• በወረቀት የተፈተኑ — 4.2% አልፈዋል።
🔥 የክልሎች የማለፊያ ምጣኔ
🥇 አዲስ አበባ — 32.4%
🥈 ሀረሪ — 22.76%
🥉 አማራ — 15%
• ድሬዳዋ — 11.92%
• ትግራይ — 11.2%
• ጉምዝ — 10.53%
• ደቡብ — 9.2%
• ሶማሌ — 9%
• ሲዳማ — 6.95%
• ጉምዝ — 6.1%
• ደቡብ ኢትዮጵያ — 4.2%
• 3.74% — የክልሉ ስም አልተጠቀሰም።
🌒 በአጠቃላይ፦ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ምጣኔ 12.8% ሲሆን፣ አዲስ አበባ 32.4% በማስመዝገብ ከፍተኛውን የክልል ደረጃ ይዟል። በተጨማሪም 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ከ62 ወደ 88 ከፍ ብለዋል።
ቀን 15/12/2018
ማሳሰቢያ ፦
ለ11 እና 12ኛ ክፍል በክላስተር ማዕከል (ስኩል ኦፍ ቱሞሮው ) እየተማራችሁ ላላችሁ በየዕለቱ ክትትል የሚደረግ በመሆኑ በመጨረሻም ሰርተፊኬት የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ እንድትገኙ ማሳሰብ እንወዳለን !
ትም/ት ቤቱ
ቀን 30/11/2018
ለ2019ዓ/ም የ12ኛ ከፍል ተማሪዎቸ የሲኒየር ዩኒፎርም በተማሪዎች በተመረጡ ኮሚቴዎች የልብሱ ጥራትና አይነት የተመረጠ ሲሆን የአንድ ዩኒፎርም ዋጋ 2600.00 ሲሆን ሁለት ለሚፈልጉ በእጥፍ የሚከፈል ይሆናል ። ስለሆነም የተማሪ ኮሚቴዎች ገቢ እንዲሆን የተስማሙበት አካውንት ቁጥር የሚከተለው ነው
1000576121435
መሰረት ታሪኩ በቀለ
ቴሌ ብር 0993578557
መሆኑን እናሳውቃለን።
የተማሪ ኮሚቴዎች
ማሳሰቢያ፦ ገቢ የተደረገበትን ደረሰኝ ስክሪን ሹት በማድረግ በሁሉም ተማሪዎች የጋራ ቻናል መላክ ይኖርባችኋል ።
ማስታወቂያ፦
ስኩል ኦፍ ቱሞሮ እንድትማሩ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ ከግቢያችን ከሚማሩት ተማሪዎች ጋር የይዘት ልዩነቶች በመኖሩ ይህንን ልዩነት ለማጥበብ ከቀጣይ ቅዳሜ (1/12/2018) ጀምሮ ትምህርት ስለሚሰጥ ከጠዋቱ 2:00_6:30 እንድትገኙ እንጠይቃለን !
ትም/ት ቤቱ
ቀን 29/11/2018
ሰላም የተከበራችሁ ወላጆች እና የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት እየተማራችሁ ያላችሁ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንደምን አላችሁ !
ውድ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስትመጡ የትምህርት ቤት የተከለከሉ ጉዳዮችን ይዛችሁ እንዳትመጡ ለአብነት ሞባይል ምክንያቱም ባለፈው ሳምንት በሌላ ትምህርት ቤት ሞባይል ለመንጠቅ በነበረ ግርግር በአካል ላይ ጉዳት መድረሱ በሪፖርት ተገምግሟል ። ስለዚህ ለደህንነታችሁም ሲባል በፍፁም እንዳትይዙ ። ሌላው ዩኒፎርም በአግባቡ መልበስ ፣ በሰዓት መገኘት ፣ ፀጉርን በአግባቡ ማስተካከል (ለወንዶች) በተገቢ ሁኔታ መሰራት (ለሴቶች)፣ አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁስ ይዞ መገኘት የሚሉት ጉዳዮች በትክክል ተግባራዊ እንዲሆኑ እናሳስባለን ።
ትምህርት ቤቱ !
