en
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Assaye Derbie

Channel Assaye Derbie (@asayede) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 294 subscribers, ranking 2 654 in the Blogs category and 2 368 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 294 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -148 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 34.94%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 995 views. Within the first day, a publication typically gains 1 888 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 25.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Blogs category.

14 294
Subscribers
No data24 hours
-397 days
-14830 days
Posts Archive
የጣልኩባቸውን ተስፋ ያመከኑ ሁለት ፕሮፌሰሮች‼️ አሳዬ ደርቤ ፕሮፌሰር ብርሐኑ ▬▬▬▬▬ ከህውሓት የሥልጣን ዘመን አንስቶ እስከ ለውጡ ማግስት ድረስ ‹‹የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች›› ሆነኝ ከሚታዩኝ ሰዎች ዋነኛው እና ቀዳሚው ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነበር፡፡ ከሥልጣን ሽግግሩ በኋላ ግን እኒያ ፕሮፌሰር ወደ ትግል ሜዳ ይዘዋቸው የሄዱትን ታጋዮች ከሜዳ ላይ በትነዋቸው ወደ ቤተ-መንግሥት ሲያመሩ ዐየኋቸው፡፡ ➔ወንበር ተቀብለው አገር ሲሰጡ፣ ድርጅታዊ ትግልን በግላዊ ድል ሲለውጡ፣ የሕዝብ ፍቅርን በግለሰብ አምልኮ ሲሸጡ፣ ➔በመለስ ዜናዊ ላይ ደረታቸውን የሚነፉት ሰው ለወቅቱ መሪ ሲሽቆጠቆጡ፣ የዜግነት ፖለቲካ ትግላቸው ደጋፊ ሆኖ ገንዘቡን እና ጉልበቱን ሲለግሳቸው የኖረውን ዜጋ አሽቀንጥረው ከብሔርተኞች ስር ሲርመጠመጡ፣ ➔ግዙፍ ሥማቸውንና በሕዝብ ልብ ውስጥ የተቀመጠ ዙፋናቸውን ወርውረው ከቆማሪዎች ወንበር ላይ በእርካታ ሲቀመጡ…ዐየኋቸው፡፡ በህውሓት ጊዜ አገራዊ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት ቀድመው የሚተነብዩት ፖለቲከኛ በብልጽግና ጊዜ የተከሰተ ችግርን መመልከት ሲሳናቸው ዐየሁ፡፡ ያለፈውን ሥርዓት ‹‹አገር የሚያወድም ካንሰር ነው›› እያሉ የሚጠሩት ጉምቱ ፖለቲከኛ ሥልጣን ላይ ያለውን ሥርዓት ‹‹አገር የሚያክም ዶክተር ነው›› እያሉ ሲያወድሱት ሰማሁ፡፡ ፕሮፌሰር በለጠ ሞላ ▬▬▬▬▬▬ እንደ ሌሎች የአብን አመራሮች በሶሻል ሚዲያ ሳይሆን በአካልም ጭምር ያገኘሁትና በእርጋታው፣ በእውቀቱ፣ በብስለቱ በተለያዩ ጊዜያት እዚህ ገፄ ላይ አድናቆቴን የቸርኩት ፕሮፌሰር በለጠ በሰለጠነ መንገድ የዶክተር ደሳለኝን ሥልጣን ተረክቦ የአብን ፕሬዝዳንት ሲሆን ‹‹የተጀመረውን ድርጅታዊ ትግል ከፍ በማድረግ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመውን በደል እና ግፍ እንዲቀንስ ማድረግ ይችላል›› የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ ፍልስፍና ያጠና ሰው እንደመሆኑ መጠንም ከቁሳዊ እና ግላዊ ነገሮች ይልቅ ሕዝባዊ እና ሞራላዊ ጉዳዮችን ያስቀድማል የሚል ግምት ነበረኝ። የብልጽግናን ሥልጣን በተረከበ ማግሥት ግን ይሄንን ዐየሁ! ➔የነበረውን እርጋታ ወደ መኝታ አሳድጎ በእንቅልፍ ሲስለመለም፣ የተጀመረውን ድርጅታዊ ትግል እና የተባባሰውን ሕዝባዊ በደል እርግፍ አድርጎ ትቶ ከተሰጠው ወንበር ላይ ያገኘውን ድል ሲያጣጥም፣ ➔በብልጽግና ፓርቲ ተመስጦ አብንን ሲያከስም፣ ‹‹እውነት ምንድና ናት›› ለሚለው የፍልስፍና ጥያቄ ‹‹በሕዝብ ትግል የምትገኝ ግላዊ ጥቅም ናት›› የሚል መልስ ሰጥቶ ኑሮውን ሲያጣጥም፣ ➔ከአርባ በላይ የአብን አመራሮች ጋር በሺህዎች የሚቆጠሩ ፋኖዎች መታፈናቸውን የሚደግፍ መግለጫ ላይ ሲፈርም... በደል ፈጻሚው እሱ ሆኖ ሳለ እንደተበዳይ ሲያልጎመጉም፣ ከተማረው ፍልስፍና በተቃራኒ ተሰልፎ በእራስ ወዳድ ስብዕና ሥልጣኑን ለማስረከብ ሲለግም ዐየሁ፡፡ የአማራን ሕዝብ ያለመሪ ድርጅት አስቀርቶ አምሳ ሚሊዮን ግለሰብ ሲያደርገውም ታዘብኩ፡፡

በመተከል ጥቃት ሲያልቅ ለኖረው ሕዝብ ፥ ድምጽ ስለሆነ፤ መሸለም ሲገባው በብአዴን ትዕዛዝ ፥ ታፍሶ የታፈነ። #ፍትሕ በሚያሸልማቸው ተግባር ለእስር ለተዳረጉ ሁሉ‼️
በመተከል ጥቃት ሲያልቅ ለኖረው ሕዝብ ፥ ድምጽ ስለሆነ፤ መሸለም ሲገባው በብአዴን ትዕዛዝ ፥ ታፍሶ የታፈነ። #ፍትሕ በሚያሸልማቸው ተግባር ለእስር ለተዳረጉ ሁሉ‼️

ጄኔራሉ በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ዋስ የመሆን እድሉን ባገኝ ደስታውን አልችለውም‼️
ጄኔራሉ በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ዋስ የመሆን እድሉን ባገኝ ደስታውን አልችለውም‼️

ፋሲል የኔ ዓለም ሰቦቃ ▬▬▬▬▬▬ ➔ፖለቲከኞችን እና ፖለቲካን በዘር መነጽር መመልከት የተጠናወተው፤ ➔ለአማራ ፖለቲከኞች፣ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች በጎ እይታ የሌለው፤ ➔የተረኝነት መንፈስ የሚሰማው፤ ➔ከብሔርተኞች ጎራ ለመቀላቀል የቋንቋ እጥረት ያጋጠመው፤ ➔ተወልዶ ላደገበት አካባቢ ቅን አመለካከት የሚጎድለው፤ ➔የክፋት አስተሳሰቡን በዜግነት ጭምብል እና በለስላሳ ቃል መጠቅለል የሚቀናው፤ ➔"የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሰሜን ኢትዮጵያ መራቅ አለበት" በሚል እሳቤ እነ አንዱዓለም አራጌን ሳይቀር ሲታገል የምታገኘው፤

ሶስቱ የበቀለ ልጆች ▬▬▬▬ ➔ዶክተር ስለሽ በቀለ ➔ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ➔ሽመልስ በቀለ ሦስቱ የመኮነን ልጆች ▬▬▬▬▬ ➔ናትናኤል መኮነን ➔ደመቀ መኮነን ➔መሳይ መኮነን ጋሽ በቀለን እናመሠግናለን! ጋሽ መኮነን ግን በጣም ታናድዳለህ 😆

እራስዎን ይፈትሹ!! አሳዬ ደርቤ ታላላቅ ስብዕናዎች፡- ▬▬▬▬▬ ➔መልካሞች ሆነው ለሌሎች ይኖራሉ፡፡ ➔ከጥቅም ይልቅ መልካም ሥምን ያስቀድማሉ፡፡ ➔ለሌሎች ነጻነት የእራሳቸውን ሕይወት ይሰዋሉ፡፡ ➔በጭቆና ሜዳ ውስጥ አፈናን ሲጠየፉ፣ በቅጥፈት ፖለቲካ ውስጥ እውነትን ሲለፍፉ፣ የእራሳቸውን ግላዊ ሲሳይ ንቀው ስለ ሌሎች ስቃይ ሲባዝኑ ለአፈና እና ለካቴና ይዳረጋሉ፡፡ በባርነት የብስ ላይ ነጻ የሆነች ነፍስ ታቅፈው ሲሟገቱ በተላላኪዎች ጥይት ይቀጠፋሉ፡፡ አንዳንዶቹም የታገሉለት ዓላማ ሲሳካ የማየት እድሉን ያገኛሉ፡፡ ኖርማል ስብዕናዎች ▬▬▬▬▬▬ ➔እነሱን ነጻ የሚያወጣ መሲህ ወይም መሪ እስኪመጣ ድረስ ‹‹ሕዝብ›› በሚል ሥም ታሽገው በባርነት ዘመን ባሪያነትን፣ በአፈና ዘመን ዱዳነትን፣ በብዝበዛ ዘመን ርሐብን…. ይለማመዳሉ፡፡ ➔አቅማቸውን ሳይፈትሹት፣ ሕልማቸውን ሳይኖሩት፣ መክሊታቸውን ሳያዉቁት ከሌሎች በተሰጣቸው ነጻነትና በተፈቀደላቸው ሕይወት ልክ ይኖራሉ፡፡ ሞታቸውን የያዘ ቀን እስኪመጣ ድረስ ‹‹ይሄም ያልፋል›› ሲሉ ኖረው ያልፋሉ፡፡ (ነፍስ ይማር) 😭 ውዳቂ ስብዕናዎች ▬▬▬▬▬ ➔አንዳንዶቹ ወንበር ይዘው ሕዝብን ለእጦት፣ አገርን ለፍርሰት፣ ንጹሐንን ለእልቂት… ሲዳርጉ አብዛኞቹ ደግሞ ከመጣ ከሄደው ሥርዓት ጋር መልካቸውን እንደ እስስት እየለዋወጡ ከአምባገነኖች ጎን ተሰልፈው የነጻነት ታጋዮችን ያሳፍናሉ፡፡ ሆዳቸውን ለመሞላት ሲሉ እራሳቸውን ጨምሮ ሕዝባቸውንና አገራቸውን ይሸጣሉ፡፡ ➔በመንግሥትና በሕዝብ መሃከል የሚመላለሱ ደላላዎች እንደመሆናቸው መጠን ባርነትን፣ ጭቆናን፣ እልቂትን፣ ርሐብን፣ ግፍን… የሚያሻሽጡበት አካውንት ከፍተው የወገን ድምጽ ለመሆን የሚሞክሩትን ‹‹በአመጽ ቀስቃሽነት›› ይወነጅላሉ፡፡ ‹‹እናንተን አስሮ የጀግንነትና የታዋቂነት ካባ የሚደርብ የለም›› በሚል ተልካሻ አስተያየት የልባቸውን ንቅዘት ይፋ ያወጣሉ፡፡ ➔እንደ ታላቁ እስክንድር በርካታ መስዋዕትነት ሲከፍሉ የኖሩ ጀግኖችን ‹‹ንኮች ናቸው›› እያሉ ያጥላላሉ፡፡ እንደ ጎበዜ ሲሳይ ያሉ ጋዜጠኞች ሲታፈኑ ‹‹እራሳቸውን ደብቀው ነው›› የሚል ዘመቻ ይከፍታሉ፡፡ ከእለታት ባንዱ ቀንም ከሰፊ ጨጓራቸው ጋር ወደ መቃብር ይወርዳሉ፡፡ (ነፍስ ይማር ያላልኩት ነፍስ ስለሌላቸው ነው፡፡) 😆

ጎበዟ እኅቴ "የአማራ ሕዝብ የትግል ዳራ እና አቅጣጫዎች" የሚል እጅግ አስገራሚ ሰነድ አዘጋጀች። ብአዴንም ሰነዱን ካነበበ በኋላ ለበላይ አካል ሪፖርት አደረገ። "ከምድር ላይ መጥፋት አለበት" የሚል
ጎበዟ እኅቴ "የአማራ ሕዝብ የትግል ዳራ እና አቅጣጫዎች" የሚል እጅግ አስገራሚ ሰነድ አዘጋጀች። ብአዴንም ሰነዱን ካነበበ በኋላ ለበላይ አካል ሪፖርት አደረገ። "ከምድር ላይ መጥፋት አለበት" የሚል ውሳኔ ያስተላለፈበትን ሕዝብ የሚታደግ ሰነድ በማዘጋጀቷ የተበሳጨው የብልጽግና መንግሥትም መስኪን አፈናት። ቤቷን ሲፈትሽም ያገኘውን አምሳ የኬንያ ሽልንግ እንደ ወንጀል ቆጥሮ "በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር" ከሰሳት። 😆 እንኩቶዎች‼️

የቀድሞው ሥርዓት በሕዝቦች መሃከል ያለውን መፈቃቀር ሲያጠፋ ለሃያ ሰባት ዓመታት ያህል ኖረ፡፡ በስተመጨረሻም ጥላቻ ላይ ባመጹ ወጣቶች ድባቅ ተመትቶ ተባረረ፡፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲም በመደመር ተቀየረ፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ግን ሸክስፒር በሎሬት ብዕር ‹‹ማክቤዝ እንቅልፍን ገደላት›› እንዲል ወደ ሥልጣን የመጣው ብልጽግናም ፍቅርን ገደላት፡፡ በህውሓት ጊዜ ከመሬት ተፈናቅላ ወደ ዜጎች ጭንቅላትና ልብ የገባችውን አገርም አንኮታኮታት፡፡ አምባገነን መንግሥታት በነገሱበት ዘመን ዜጎች አገራቸውን ጥለው ወደ ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፡፡ አረማውያን መንግሥታት ግን ፍቅር፣ አገር እና እግዜር አልባ ልብ ያላቸው ዜጎችን ይፈጥራሉ፡፡ ከአገር በሚፈናቀሉ ዜጎች ፈንታ አገራቸውን ከልባቸው ያፈናቀሉ መንጋዎችን ያደራጃሉ፡፡ ‹‹ጠላት መጣ›› ብለው ዓድዋ ላይ፣ ማይጨው ላይ፣ ካራማራ ላይ፣ መተማ ላይ… ለእናት አገራቸው ክብር ሲሞቱ ከነበሩ አባቶች መወለዳቸውን ዘንግተው ከክልላቸው ሲወጡ በጠላት መሃከል የተገኙ ይመስል ሥጋት የሚሰማቸው ዜጎችን ይቀፈቅፋሉ፡፡ አገር እያፈረሱ ቪላና ሕንጻ የሚቀልሱ፣ ግጭት እየቀሰቀሱ ሐብት የሚያግበሰብሱ፣ የሆነን ክልል ለማስደሰት ሌላውን ክልል የሚያተራምሱ…. ነጋዴዎችን ‹‹አመራሮች›› በሚል ማዕረግ የሚጠራው የብልጽግና መንግሥትም ቀደምት አባቶች ከአንዱ ጫፍ ወደ ሌላው ጫፍ ዘምተው የሞቱለትን ‹‹አገር›› እና ‹‹ዳር ድንበር›› ቆፋፍሮ የጅምላ መቃብር አድርጎታል፡፡ በዘረኝነት የጎደፈ እጁን ከሃይማኖት ውስጥ አስገብቶ በሠራው ሥራም የእረኞችን ቦታ በተኩላዎች ማስወረር ችሏል፡፡ ለወንጀለኞች የተሠራውን እስር ቤትም ወንጀሉን እና ጥፋቱን የሚነግሩትን ዜጎች ማፈኛ ሥፍራ አድርጎታል።

ሥልጣን ላይ ያለው ‹‹ሥርዓት የለሽ ሥርዓት›› በሰሞኑ የአፈና ድርጊቶቹ ከሕዝብ በተጨማሪ ለሕግ ያለውን ንቀት በግልጽ አሳይቷል፡፡ ሕግን የማያከብር አካል ደግሞ ሕግን ሊያስከብር አይቻለውም፡፡

ትናንት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ በሜሮን ታደለ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመው አፋኙ መንግሥት ከ24 ሰዓት የምርመራ ጥያቄ በኋላ "በጋብቻ ካልሆነ በቀር በወንጀል የሚያሳስር ጥፋት አላገኘሁብሽም" ከ
ትናንት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ በሜሮን ታደለ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመው አፋኙ መንግሥት ከ24 ሰዓት የምርመራ ጥያቄ በኋላ "በጋብቻ ካልሆነ በቀር በወንጀል የሚያሳስር ጥፋት አላገኘሁብሽም" ከሚል ኑዛዜ ጋር ስልክ ቁጥሯን ተቀብሎ ወደ ቤቷ መልሷታል።😆 እንኳን ለቤትሽ በቃሽ እኅታለም‼️

ለታፈኑ ሰዎች ድምጽ ሆና የሰነበተችው እኅታችን ሜሮን ታደለ ከምሽቱ 3:00 ሠዓት ላይ ታፍና ተወስዳለች። ካልጠፋ ቀን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ሴትን ልጅ ማፈን ጠልፎ ከመውሰድ በምን ይለያል?
ለታፈኑ ሰዎች ድምጽ ሆና የሰነበተችው እኅታችን ሜሮን ታደለ ከምሽቱ 3:00 ሠዓት ላይ ታፍና ተወስዳለች። ካልጠፋ ቀን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ሴትን ልጅ ማፈን ጠልፎ ከመውሰድ በምን ይለያል?

የMeskerem Abera ችሎት ላይ የተሰማ ክርክር #ፖሊስ:- የመስከረም አበራን ቤት ስፈትሽ ባገኘሁት የውጭ አገር ገንዘብ ዙሪያ ከብሔራዊ ባንክ ማጣራት ስለሚገባኝ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ #ጠበቃ:- ክቡር ፍ/ቤት ተገኘ የተባለው 2 ባለ 50 የኬንያ ሽልንግ ነው ! 😂

በዚህ ወቅት እስክንድር ነጋ ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ የተወሰኑ ዓመታትን በእስር ቤት ከማሳለፍ ውጭ ምንም ነገር ማበርከት ስለማይችል ባለበት አገር ሆኖ ትግሉን ማጠናከር ይኖርበታል። ፈጽሞ መምጣት የለበትም።

የሚታገላችሁ እንጂ የሚያሸንፋችሁ የለም። ከእስራታችሁ ጀርባም የከሳሾቻችሁ ፍርሐት እንጂ የእናንተ ጥፋት አይገኝም።
የሚታገላችሁ እንጂ የሚያሸንፋችሁ የለም። ከእስራታችሁ ጀርባም የከሳሾቻችሁ ፍርሐት እንጂ የእናንተ ጥፋት አይገኝም።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን በዝምታ የሚያልፋቸውን መንግሥታዊ ጥፋቶች "ልማቶች ናቸው" የሚል ትንታኔ ሲሰጥ የኖረ ጋዜጠኛ ለአገራዊ ውድቀቱ የድርሻውን ማበርከቱን ማወቅ ቢሳነው እንኳን "ቋቅ" ሊለው አይገባም!

"ከመደበኛ የጸጥታ ኃይል በላይ የነበረውን 'አገር አፍራሽ አሸባሪ' የመከተ ኃይል ትክክለኛ ሥሙ አርበኛ እንጂ ጽንፈኛ ስላልሆነ ከፋኖ ላይ እጃችሁን አንሱ!" ዲሲዎች‼️
+1
"ከመደበኛ የጸጥታ ኃይል በላይ የነበረውን 'አገር አፍራሽ አሸባሪ' የመከተ ኃይል ትክክለኛ ሥሙ አርበኛ እንጂ ጽንፈኛ ስላልሆነ ከፋኖ ላይ እጃችሁን አንሱ!" ዲሲዎች‼️

እነ ጄኔራል ክንፈን እና አቦይ ስብሐትን በነፃ ያሰናበተ መንግሥት ሕግ የሚያስከብርበት ሞራል ስለሌለው... ወንድሞቻችንን ፍታ‼️ እኅቶቻችንን ልቀቅ‼️
እነ ጄኔራል ክንፈን እና አቦይ ስብሐትን በነፃ ያሰናበተ መንግሥት ሕግ የሚያስከብርበት ሞራል ስለሌለው... ወንድሞቻችንን ፍታ‼️ እኅቶቻችንን ልቀቅ‼️

መዓዛ መሐመድ፥ ቲና የበላይ ልጅ፥ መስከረም አበራ ተመስገን ደሳለኝ፥ ሰሎሞን ሹምዬ፥ ጄኔራል ተፈራ ያለለት ወንድዬ፥ ኮማንደር ቢሰጠኝ፥ ጋሽ ታዲያስ ታንቱ አዲሱ ጌታነህ፥ አያሌው ታለማ፥ ግርማቸው መ
መዓዛ መሐመድ፥ ቲና የበላይ ልጅ፥ መስከረም አበራ ተመስገን ደሳለኝ፥ ሰሎሞን ሹምዬ፥ ጄኔራል ተፈራ ያለለት ወንድዬ፥ ኮማንደር ቢሰጠኝ፥ ጋሽ ታዲያስ ታንቱ አዲሱ ጌታነህ፥ አያሌው ታለማ፥ ግርማቸው መንግሥቱ እልፍ አእላፍ ጀግና ፥ አምሥት ሺህ ፋኖ እንዴት ዝም እላለሁ፥ ለእኔ ሲል ታፍኖ? አሳዬ ደርቤ

በዚያኛው ወገን "ከድርድሩ በፊት ሙሰኛ እና ሽብርተኛ ተብለው የታሠሩ አመራሮቼ ሊፈቱ ይገባል" የሚል ቅድመ ሁኔታ መቅረቡን ሲሰማ "በክልሌ ውስጥ ያሉ ፋኖዎችን እና የሕዝብ ድምፆችን ሳላስር ወደ ድርድር አልገባም" የሚል ቅድመ ሁኔታ አስቀምጦ አፈና ሲያካሂድ የከረመ ድርጅት... በጠረጴዛ ዙሪያ ሲቀመጥ ሕዝባዊ ጥያቄውን እረስቶ የምግብ ጥያቄ እንደሚያቀርብ ጥርጥር የለውም።

"የጠቅላይ ሚኒስትሩን የወደፊት ሐሳብ ከእሱ በተሻለ መልኩ አውቀዋለሁ" የምልህ በምክንያት ነው‼️ በቀጣይ በእነ ዲያቆን እንትና ፈንታ ጌታቸው ረዳን አማካሪው ያላደረገ እንደሁ ከመላጣ ጭንቅላቴ ላይ
"የጠቅላይ ሚኒስትሩን የወደፊት ሐሳብ ከእሱ በተሻለ መልኩ አውቀዋለሁ" የምልህ በምክንያት ነው‼️ በቀጣይ በእነ ዲያቆን እንትና ፈንታ ጌታቸው ረዳን አማካሪው ያላደረገ እንደሁ ከመላጣ ጭንቅላቴ ላይ ጸጉር ይነቀል። 😆