uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 333 підписників, посідаючи 2 647 місце в категорії Блоги та 2 350 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 333 підписників.

За останніми даними від 25 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -108, а за останні 24 години на -4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 38.62%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.61% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 538 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 808 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 26 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 333
Підписники
-424 години
-317 днів
-10830 день
Архів дописів
የቀድሞው ሥርዓት በሕዝቦች መሃከል ያለውን መፈቃቀር ሲያጠፋ ለሃያ ሰባት ዓመታት ያህል ኖረ፡፡ በስተመጨረሻም ጥላቻ ላይ ባመጹ ወጣቶች ድባቅ ተመትቶ ተባረረ፡፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲም በመደመር ተቀየረ፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ግን ሸክስፒር በሎሬት ብዕር ‹‹ማክቤዝ እንቅልፍን ገደላት›› እንዲል ወደ ሥልጣን የመጣው ብልጽግናም ፍቅርን ገደላት፡፡ በህውሓት ጊዜ ከመሬት ተፈናቅላ ወደ ዜጎች ጭንቅላትና ልብ የገባችውን አገርም አንኮታኮታት፡፡ አምባገነን መንግሥታት በነገሱበት ዘመን ዜጎች አገራቸውን ጥለው ወደ ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፡፡ አረማውያን መንግሥታት ግን ፍቅር፣ አገር እና እግዜር አልባ ልብ ያላቸው ዜጎችን ይፈጥራሉ፡፡ ከአገር በሚፈናቀሉ ዜጎች ፈንታ አገራቸውን ከልባቸው ያፈናቀሉ መንጋዎችን ያደራጃሉ፡፡ ‹‹ጠላት መጣ›› ብለው ዓድዋ ላይ፣ ማይጨው ላይ፣ ካራማራ ላይ፣ መተማ ላይ… ለእናት አገራቸው ክብር ሲሞቱ ከነበሩ አባቶች መወለዳቸውን ዘንግተው ከክልላቸው ሲወጡ በጠላት መሃከል የተገኙ ይመስል ሥጋት የሚሰማቸው ዜጎችን ይቀፈቅፋሉ፡፡ አገር እያፈረሱ ቪላና ሕንጻ የሚቀልሱ፣ ግጭት እየቀሰቀሱ ሐብት የሚያግበሰብሱ፣ የሆነን ክልል ለማስደሰት ሌላውን ክልል የሚያተራምሱ…. ነጋዴዎችን ‹‹አመራሮች›› በሚል ማዕረግ የሚጠራው የብልጽግና መንግሥትም ቀደምት አባቶች ከአንዱ ጫፍ ወደ ሌላው ጫፍ ዘምተው የሞቱለትን ‹‹አገር›› እና ‹‹ዳር ድንበር›› ቆፋፍሮ የጅምላ መቃብር አድርጎታል፡፡ በዘረኝነት የጎደፈ እጁን ከሃይማኖት ውስጥ አስገብቶ በሠራው ሥራም የእረኞችን ቦታ በተኩላዎች ማስወረር ችሏል፡፡ ለወንጀለኞች የተሠራውን እስር ቤትም ወንጀሉን እና ጥፋቱን የሚነግሩትን ዜጎች ማፈኛ ሥፍራ አድርጎታል።

ሥልጣን ላይ ያለው ‹‹ሥርዓት የለሽ ሥርዓት›› በሰሞኑ የአፈና ድርጊቶቹ ከሕዝብ በተጨማሪ ለሕግ ያለውን ንቀት በግልጽ አሳይቷል፡፡ ሕግን የማያከብር አካል ደግሞ ሕግን ሊያስከብር አይቻለውም፡፡

ትናንት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ በሜሮን ታደለ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመው አፋኙ መንግሥት ከ24 ሰዓት የምርመራ ጥያቄ በኋላ "በጋብቻ ካልሆነ በቀር በወንጀል የሚያሳስር ጥፋት አላገኘሁብሽም" ከ
ትናንት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ በሜሮን ታደለ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመው አፋኙ መንግሥት ከ24 ሰዓት የምርመራ ጥያቄ በኋላ "በጋብቻ ካልሆነ በቀር በወንጀል የሚያሳስር ጥፋት አላገኘሁብሽም" ከሚል ኑዛዜ ጋር ስልክ ቁጥሯን ተቀብሎ ወደ ቤቷ መልሷታል።😆 እንኳን ለቤትሽ በቃሽ እኅታለም‼️

ለታፈኑ ሰዎች ድምጽ ሆና የሰነበተችው እኅታችን ሜሮን ታደለ ከምሽቱ 3:00 ሠዓት ላይ ታፍና ተወስዳለች። ካልጠፋ ቀን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ሴትን ልጅ ማፈን ጠልፎ ከመውሰድ በምን ይለያል?
ለታፈኑ ሰዎች ድምጽ ሆና የሰነበተችው እኅታችን ሜሮን ታደለ ከምሽቱ 3:00 ሠዓት ላይ ታፍና ተወስዳለች። ካልጠፋ ቀን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ሴትን ልጅ ማፈን ጠልፎ ከመውሰድ በምን ይለያል?

የMeskerem Abera ችሎት ላይ የተሰማ ክርክር #ፖሊስ:- የመስከረም አበራን ቤት ስፈትሽ ባገኘሁት የውጭ አገር ገንዘብ ዙሪያ ከብሔራዊ ባንክ ማጣራት ስለሚገባኝ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ #ጠበቃ:- ክቡር ፍ/ቤት ተገኘ የተባለው 2 ባለ 50 የኬንያ ሽልንግ ነው ! 😂

በዚህ ወቅት እስክንድር ነጋ ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ የተወሰኑ ዓመታትን በእስር ቤት ከማሳለፍ ውጭ ምንም ነገር ማበርከት ስለማይችል ባለበት አገር ሆኖ ትግሉን ማጠናከር ይኖርበታል። ፈጽሞ መምጣት የለበትም።

የሚታገላችሁ እንጂ የሚያሸንፋችሁ የለም። ከእስራታችሁ ጀርባም የከሳሾቻችሁ ፍርሐት እንጂ የእናንተ ጥፋት አይገኝም።
የሚታገላችሁ እንጂ የሚያሸንፋችሁ የለም። ከእስራታችሁ ጀርባም የከሳሾቻችሁ ፍርሐት እንጂ የእናንተ ጥፋት አይገኝም።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን በዝምታ የሚያልፋቸውን መንግሥታዊ ጥፋቶች "ልማቶች ናቸው" የሚል ትንታኔ ሲሰጥ የኖረ ጋዜጠኛ ለአገራዊ ውድቀቱ የድርሻውን ማበርከቱን ማወቅ ቢሳነው እንኳን "ቋቅ" ሊለው አይገባም!

"ከመደበኛ የጸጥታ ኃይል በላይ የነበረውን 'አገር አፍራሽ አሸባሪ' የመከተ ኃይል ትክክለኛ ሥሙ አርበኛ እንጂ ጽንፈኛ ስላልሆነ ከፋኖ ላይ እጃችሁን አንሱ!" ዲሲዎች‼️
+1
"ከመደበኛ የጸጥታ ኃይል በላይ የነበረውን 'አገር አፍራሽ አሸባሪ' የመከተ ኃይል ትክክለኛ ሥሙ አርበኛ እንጂ ጽንፈኛ ስላልሆነ ከፋኖ ላይ እጃችሁን አንሱ!" ዲሲዎች‼️

እነ ጄኔራል ክንፈን እና አቦይ ስብሐትን በነፃ ያሰናበተ መንግሥት ሕግ የሚያስከብርበት ሞራል ስለሌለው... ወንድሞቻችንን ፍታ‼️ እኅቶቻችንን ልቀቅ‼️
እነ ጄኔራል ክንፈን እና አቦይ ስብሐትን በነፃ ያሰናበተ መንግሥት ሕግ የሚያስከብርበት ሞራል ስለሌለው... ወንድሞቻችንን ፍታ‼️ እኅቶቻችንን ልቀቅ‼️

መዓዛ መሐመድ፥ ቲና የበላይ ልጅ፥ መስከረም አበራ ተመስገን ደሳለኝ፥ ሰሎሞን ሹምዬ፥ ጄኔራል ተፈራ ያለለት ወንድዬ፥ ኮማንደር ቢሰጠኝ፥ ጋሽ ታዲያስ ታንቱ አዲሱ ጌታነህ፥ አያሌው ታለማ፥ ግርማቸው መ
መዓዛ መሐመድ፥ ቲና የበላይ ልጅ፥ መስከረም አበራ ተመስገን ደሳለኝ፥ ሰሎሞን ሹምዬ፥ ጄኔራል ተፈራ ያለለት ወንድዬ፥ ኮማንደር ቢሰጠኝ፥ ጋሽ ታዲያስ ታንቱ አዲሱ ጌታነህ፥ አያሌው ታለማ፥ ግርማቸው መንግሥቱ እልፍ አእላፍ ጀግና ፥ አምሥት ሺህ ፋኖ እንዴት ዝም እላለሁ፥ ለእኔ ሲል ታፍኖ? አሳዬ ደርቤ

በዚያኛው ወገን "ከድርድሩ በፊት ሙሰኛ እና ሽብርተኛ ተብለው የታሠሩ አመራሮቼ ሊፈቱ ይገባል" የሚል ቅድመ ሁኔታ መቅረቡን ሲሰማ "በክልሌ ውስጥ ያሉ ፋኖዎችን እና የሕዝብ ድምፆችን ሳላስር ወደ ድርድር አልገባም" የሚል ቅድመ ሁኔታ አስቀምጦ አፈና ሲያካሂድ የከረመ ድርጅት... በጠረጴዛ ዙሪያ ሲቀመጥ ሕዝባዊ ጥያቄውን እረስቶ የምግብ ጥያቄ እንደሚያቀርብ ጥርጥር የለውም።

"የጠቅላይ ሚኒስትሩን የወደፊት ሐሳብ ከእሱ በተሻለ መልኩ አውቀዋለሁ" የምልህ በምክንያት ነው‼️ በቀጣይ በእነ ዲያቆን እንትና ፈንታ ጌታቸው ረዳን አማካሪው ያላደረገ እንደሁ ከመላጣ ጭንቅላቴ ላይ
"የጠቅላይ ሚኒስትሩን የወደፊት ሐሳብ ከእሱ በተሻለ መልኩ አውቀዋለሁ" የምልህ በምክንያት ነው‼️ በቀጣይ በእነ ዲያቆን እንትና ፈንታ ጌታቸው ረዳን አማካሪው ያላደረገ እንደሁ ከመላጣ ጭንቅላቴ ላይ ጸጉር ይነቀል። 😆

ከወራት በፊት አንዲት ሴት ላይ የጫማ ጥፊና የካራቲ ችሎታቸውን ሲገልጹ ከታዩ ፖሊሶች ጋር አብረው የሰለጠኑ ኃይሎች በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ገልጿል።
ከወራት በፊት አንዲት ሴት ላይ የጫማ ጥፊና የካራቲ ችሎታቸውን ሲገልጹ ከታዩ ፖሊሶች ጋር አብረው የሰለጠኑ ኃይሎች በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ገልጿል። ያም ሆኖ በዚህ ዘመን "ፍትሕ" ማለት የተመስገን ደሳለኝ መጽሔት በመሆኑ ከሞራል የለሽ ባለሥልጣናት እጅ የሚጠየቅ ፍትሕ አይኖርም።

ብልጽግና ሆይ ወንጀለኛ ወይም ደግሞ ጽንፈኛ ብለህ ያፈንካቸው አማራዎች የሰነዘሩብህን ትችት እንደ ጥፋት ቆጥረህ ማንንም የማያሳምን ተራ የፈጠራ ክስ ስትደርት እራስህን ለትዝብት ከምትዳርግ እንዲህ አድርግ፡፡ አንድም ህውሓቶችን ወደ አዲስ አበባ አስመጥተህ ‹‹ከሳሾች›› አድርጋቸው፡፡ ወይንም ደግሞ ያፈንካቸውን ዜጎች በኢንተርፖል በኩል ለመቀሌው መንግሥት አሳልፈህ ስጣቸው፡፡ ያን ጊዜ ‹‹ለሕዝባችን እና ለአገራችን ቀጣይነት ስንል ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ለመሞት መዘገጃታችን ወንጀል አይደለም›› በማለት የሚሞግቱህ ፋኖዎች ‹‹ከመንግሥትና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን ተሰልፈን ስንወጋችሁ መክረማችን የሚካድ ስላልሆነ የትኛውንም ቅጣት ለመቀበል ዝግጁ ነን›› ብለው ጥፋታቸውን ያምናሉ፡፡ ‹‹በመንግሥት ላይ የፈጸምነው ጥፋት የለም›› ያሉህ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞችም ከህውሓት እጅ በገቡ ቅጽበት ‹‹ኢትዮጵያን ለማፍረስ እስከ እንጦሮጦስ ድረስ›› ከሚለው የእናንተ ዛቻ ይልቅ ‹‹ኢትዮጵያ አትፈርስም›› የሚለውን ዘመቻ ተቀላቅለን በተለያዩ ሚዲያዎች ስንዘምትባችሁ ነበር›› በማለት ጥፋታቸውን ያምናሉ፡፡ ወይም ደግሞ ‹‹እያደር ከመጠንከር ይልቅ መልፈስፈስ የሚወድ መንግሥት አገር እንዳያፈርስ በማሰብ ሦስት ዓመት ሙሉ እሱን ተሸክመን እያንዘፋዘፍን እናንተን ስናሳድድ ነበር›› በሚል ንግግር ጥፋታቸውን ቀርቶ ቅጣታቸውን ይቀበላሉ፡፡ እናም እልኻለሁ… ‹‹የተለመደ ድጋፋቸውን ነፈጉኝ›› በሚል ቅሬታ ያፈንካቸው ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች እንዲሁም ፋኖዎች ላይ ለችሎት የማይመጥን ክስ ከምትጽፍ ያሰርካቸውን ወገኖች ወደ መቀሌ ሸኛቸውና አምሥት ሺህ ምርኮኛ መልቀቁን ለነገረህ አካል ‹‹አምሥት ሺህ እሥረኛ ልኬልኻለሁ›› በለው፡፡

‹‹አይደገምም›› የተባለው ሲደገም! አሳዬ ደርቤ ➔ህውሓት የተባለው የቀድሞ ድርጅታችሁ ድክመቱን የሚነግሩትን የተቃውሞ ድምጾችን እያፈነ እንደ ዋልታ፣ ኢቲቪና፣ ፋና ያሉ የገደል ማሚቶዎችን ከፍቶ የእራሱን ድምጽ እያዳመጠ ‹‹ጠንካራ ነኝ›› ይል ነበር፡፡ ➔ከዘጠና ሰባቱ ምርጫ ጋር አብረው የመጡ ጋዜጦችን እና መጽሔቶችን ከሕትመት ውጭ ካደረገ በኋላ የሞደሊስቶችን እና የአርቲስቶችን የምግብ ምርጫ ለሕዝብ የሚያሳዉቁ መናኛ መጽሔቶችን ስፖንሰር ያደርግ ነበር፡፡ ➔የሚተቹትን ጸሐፊዎች እና ጋዜጠኞች ወደ እስር ቤት አስገብቶ በብዕር ሥም እየጻፈ እራሱን በእራሱ ያንቆለጳጵሰው ነበረ፡፡ ➔ከዚህ ባለፈም የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙ እልፍ አእላፍ ወጣቶችን አፍሶ ወደ አዋሽ አርባ የማጎሪያ ካምፕ ካስገባ በኋላ ‹‹መለስ አልሞተም፣ ሕገ-መንግሥቱ አይደፈርም›› የሚል ሥልጠና ሲግታቸውና ‹‹አይደገምም›› የሚል ጽሑፍ ያለበት ቲሸርት አልብሶ ሲያስመርቃቸው ነበረ፡፡ ያ ሁሉ የመብት አፈና ግን እንቢተኛ ወጣትን እና አፈንጋጭ ቡድኖችን ከማፍራት ባለፈ አልጠቀመውም፡፡ በመሆኑም ከእለታት ባንዱ ቀን ወጣቶችን የሚያፍንበትን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግብሮ፣ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎችን የሚያስተላልፉ ዲሾችን የሚነቅል ኮማንድ ፖስት አዋቅሮ እንዲሁም እነ ኢቲቪን የሚከታተል ትውልድ እፈጥራለሁ ብሎ ጣሪያ ላይ ሲንደፈደፍ ከከረመ በኋላ ወደ ምድር ሲወርድ አራት ኪሎ አካባቢ ያስቀመጠው ወንበር ጠፋው፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ከቦሌ ወደ መቀሌ ተሸኝቶ በአየር መንገድ ፈንታ በጋሪ ሲሄድ እራሱን አገኘው፡፡ የሚገርመው ነገር ታዲያ ታሪክ እራሱን ይደግማል›› እንደሚባለው የብልጽግና መንግሥትም ህውሓት በወደቀበት የአፈና መንገድ ሕያው ሆኖ ሊኖርበት አስቦ እየዳከረ መሆኑ ነው፡፡ በህውሓት ጊዜ በባሕር ዳር ወጣቶች ላይ የተፈጸመው እልቂት በብልጽግና ዘመን ሲፈጸም ትክክል ሆኖ የሚገኝ ይመስል በረከት ስምዖንን ለእስራት የዳረገውን ጥፋት የአማራ ክልል ፕሬዝዳንትና ባለሥልጣናት እየደገሙት ነው፡፡ ሆኖም ግን ከመከላከያ ጋር ለመሞት የተዘጋጁ ፋኖዎችን ባፈኑበት መዳፍ ሰሜን እዝን ከወጉ አሸባሪዎች ጋር መተቃቀፍ ቢቻልም ይህ አይነቱ የኃይል አሰላለፍ ግን የኋላ ኋላ ውድቀትን እንጂ የዙፋን መርጋትን አያመጣም፡፡ ጥጋባችሁን የሚናገሩ አንደበቶችን ወደ እስር ቤት በመወርወርም መራባቸውን እና እጦታቸውን መናገር የጀመሩትን በሚሊዮን የሚቆጠሩ አፎች ዝም መሰኘት አይቻልም፡፡ ችግር ፈጣሪን ታቅፎ ‹‹ሕግ ማስከበር›› በሚል ሥም ‹‹ሕግ ይከበር›› የሚሉ ዜጎችን በማፈን ብሎም ‹‹ሕልውናችን ይጠበቅ›› የሚሉ ፋኖዎችን በማሳደድም ሕገ ወጦችን ማስፋፋት እንጂ የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ የሚቻል አይሆንም፡፡

ወገኖቻችን እየታፈኑ ወደ እስር ቤት የተጋዙት በወንጀል በመጠርጠራቸው ሳይሆን በብልጽግና እና በህውሓት መሀከል በመካሄድ ላይ የሚገኘውን የጋብቻ ሥነ ሥርዓት ያደናቅፋሉ ተብለው በመጠርጠራቸው ነው››
ወገኖቻችን እየታፈኑ ወደ እስር ቤት የተጋዙት በወንጀል በመጠርጠራቸው ሳይሆን በብልጽግና እና በህውሓት መሀከል በመካሄድ ላይ የሚገኘውን የጋብቻ ሥነ ሥርዓት ያደናቅፋሉ ተብለው በመጠርጠራቸው ነው›› ብለን በተናገርነው መሠረት ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ አምርተዋል፡፡ ነገ ደግሞ ኦቦሳንጆ በተቀመጡበት ሦፋ ላይ የብልጽግና መሪዎች ተቀምጠው ደብረ ጽዮን ጋር ሲተሻሹ ማየታችን አይቀርም፡፡ ያን ጊዜ ታዲያ ብ/ ጄኔራል ተፈራ ማሞን እና ምክትላቸውን ‹‹የወያኔ ተልዕኮ አስፈጻሚዎች›› ብለው የወነጀሏቸው የብአዴን አመራሮች ‹‹ተዋረድን›› ብለው በመደበቅ ፈንታ ጌታቸው ረዳን በፍቅር ዐይን እየተመለከቱ ሲሽኮረመሙ ይታያሉ፡፡ ብልጽግና ላይ ትችት ሲሰነዝር ያዩትን ጋዜጠኛና አክቲቪስት ሁሉ ‹‹በወያኔ ተላላኪነት›› እያጥላሉ ሆዳቸውን ሲሞሉ የከረሙ የገደል ማሚቶዎችም… አካውንታቸውን ዲአክቲቬት አድርገው በመሰወር ፈንታ ‹‹በወልቃይት ማንነት ላይ ከህውሓት ጋር መዳራት ልክ አይደለም›› የሚሉ ድምጾችን ‹‹የኤርትራ ተላላኪዎች›› በሚል ፍረጃ እያጥላሉ ጅራታቸውን ሲቆሉ ይገኛሉ፡፡

ማርክ ማይ ወርድ! አሳዬ ደርቤ የአራት ኪሎው መንግሥት ወደ ፈላጭ ቆራጭነት ለመሸጋገርና በወልቃይት መሬት ላይ ለመደራደር ሲያስብ አብን እና ብአዴን የእቅዱ ተገዢ ሆነው ደስ አሰኙት፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በሶሻል ሚዲያው መድረክ ሕዝባቸውን የሚያነቁ ጦማሪዎችና በጦር ሜዳ ላይ የሚዋደቁ ወጣቶች እንቅፋት ሆነው ታዩት፡፡ እርሱም አለ… ‹‹በወልቃይት ማንነት ዙሪያ ለመደራደርም ሆነ አማራን ለማስገበር የጌታቸው ረዳን ሐሳብ መተግበር ግድ ይላል፡፡ ይሄውም የአማራን ልሳኖችን እና ክንዶች የመስበር ዘመቻ 'ሕግ ማስከበር' ይባል፤›› ከዚህም ውሳኔ በኋላ ከላይ የተዘረዘሩትን ኃይሎች ጠርቶ ወረቀትና ገንዘብ ካቀበላቸው በኋላ "ሕግ አስከብሩ›› አላቸው። እነርሱም ቦርጫቸውን እንደ ጠረጴዛ በመጠቀም የተሰጣቸውን ወረቀት ካስደገፉበት በኋላ ‹‹ጽንፈኛ›› በሚል ርዕስ ‹‹እንቢተኛ እና ሐቀኛ›› የአማራ ልጆችን ሥም መጻፍ ጀመሩ፡፡ እናም አሁን ላይ ፦ ➔አንዳንድ የአብን አመራሮች በብአዴን የሚታፈኑ የአማራ ልጆችን እየጠቆሙ ነው፡፡ ➔አንዳንድ ተከፋይ የአማራ ወመኔዎች ‹‹ወገኔ›› የሚሉትን ሕዝብ ለአፈና ዳርገው ‹‹ወያኔ›› የሚሉትን ጠላት እየጠበቁ ነው፡፡ ➔አብዛኛው የአማራ ሙሕራን እና ፖለቲከኞች ‹‹ተደራጅ›› ብለው ሲቀሰቅሱት የኖሩት ፋኖ ሲሳደድ እያዩ ‹‹ሕግ እንዲከበር እንፈልጋለን፡፡ በወልቃይት ላይ ለመደራደር ያሰባችሁ ቀን ግን እንጣላለን›› እያሉ ነው፡፡ ይሄውም የመጀመሪያ ምዕራፍ ‹‹የሕግ ማስከበር›› ዘመቻ በስኬት መጠናቀቅ ከቻለ ሁለተኛው ምዕራፍ ‹‹ሕግ አስከባሪ›› የሚል ይሆናል፡፡ እናም ‹‹በአንዳንድ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነት ጥያቄዎች መልስ እስኪያገኙ ድረስ በፌደራል መንግሥትና በኮማንድ ፖስት ሊተዳደሩ ይገባል›› መባል ይጀመራል፡፡ ያን ጊዜም ከላይ የተጠቀሱት ተላላኪ ኃይሎች ስምምነታቸውን ገልጸው ከወጡ በኋላ ለይምሰል ያህል ከሕዝብ ጎን ቆመው ቁጣቸውንና ተቃውሟቸውን እንዲገልጹ ይፈቀድላቸዋል፡፡ የሕዝብ ጠበቃና ጠባቂ የሆኑ ወጣቶች ወንጀለኛ እና ጽንፈኛ ተብለው እየተመረጡ ሲታፈኑ በዝምታው አማካኝነት ለዘብተኛ መሆኑን ሲገልጽ የከረመው የአማራ ሙሕርም በብልጽግና ውሳኔ የመናደድ መብቱ ይከበርለታል። ከወልቃይት ምድርም ‹‹ማንነቴን የምትወስን አንተ ማን ነህ›› የሚል ትግል ይቀጣጠላል፡፡ ‹‹የወገን ያለህ›› የሚል ቃልም ይሰማል፡፡ ሆኖም ግን ያ ጊዜ እንደሚመጣ አውቀው በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ሲደራጁ የከረሙ ፋኖዎች ለአፋና እና ለብተና የተዳረጉ በመሆናቸው ፈጥኖ የሚደርስ ኃይል አይኖርም፡፡ ከዚያ በማስከተል በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የታፈኑ ሁሉ ያለምንም ፍርድ በነጻ ይለቀቃሉ፡፡ ከእነዚህ መሃከል አብዛኞቹ ትግላቸውን ሲቀጥሉ አንዳንዶቹም ዝምታን ተምረው ይወጣሉ፡፡ አሳሪዎቹ ደግሞ የሚታሠሩበት ቀን እስኪመጣ ድረስ የእነሱ ሕልውና በብልጽግና እድሜ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ተረድተው የህውሓትና የመንግሥት ጋብቻ ሲፈጸም እልልታቸውን ያቀልጣሉ። ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› በሚል አቋምም ዛሬ ላይ የንቁ ዜጎች ማሸማቀቂያ ካደረጉት ጠላት ጎን ተሰልፈው ሕዝባቸው ላይ ይዘምታሉ፡፡ ይህ ቀን እንዳይመጣ የሚሹ ወገኖች ግን አሁን ላይ እንቅልፍ በተጫጫነው ክልል ውስጥ ቆመው ቀን እና ሌሊት በመታገል ላይ ይገኛሉ። "አፈናው ይቁም" ይላሉ።

በጥቅም ተገዝቼ ድምጽ ሳልሆናችሁ ብቀር ምላሴ ከትናጋዬ ትጣበቅ!! እስርን ፈርቼ በአረመኔ መዳፎች መታፈናችሁን ብክድ የአምላክ ጥበቃ ከእኔ ይራቅ!! ጥፋታችሁ አገር አጥፊን ማውገዛችሁ ብቻ ነው። ወን
+2
በጥቅም ተገዝቼ ድምጽ ሳልሆናችሁ ብቀር ምላሴ ከትናጋዬ ትጣበቅ!! እስርን ፈርቼ በአረመኔ መዳፎች መታፈናችሁን ብክድ የአምላክ ጥበቃ ከእኔ ይራቅ!! ጥፋታችሁ አገር አጥፊን ማውገዛችሁ ብቻ ነው። ወንጀላችሁም ወንጀለኛን መክሰሳችሁና የፍትሕ ድምጽ መሆናችሁ ብቻ ነው።

ታፋኞቹን ስናስባቸው አሳዬ ደርቤ ከቤታቸው እና ከሥራ ቦታቸው ታፍነው የተወሰዱ ጋዜጠኞችና የሕዝብ ድምጾች ለጋዜጣዊ መግለጫ የተጠሩ ይመስል ዘና ባለ መንፈስ ውስጥ ሆነው እንዲሁም መታሠራቸውን ዘንግተው ከእስር ቤት ቅጽር ግቢ ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡ መስኪ ግን ለሰባት ቀናት ያህል መታሰሯን ሳይሆን የሰባት ወር ልጇን መርሳት ተስኗታል፡፡ ከእነዚህም ታፋኞች መሀከል አንዱ የሆነው ጋዜጠኛ ሰሎሞን ሹምዬ ‹‹ዛሬ ቀኑ ማን ነው›› በማለት ሲጠይቅ ‹‹ባግባቡ አልተከበረም እንጂ ግንቦት ሃያ ነው›› በማለት ያየሰው ሽመልስ መለሰለት፡፡ ይሄንንም መልስ መስኪ ስትሰማ ‹‹‹‹የግንቦት ሃያ ቀንን በደማቁ ለማክበር ጋዜጠኞችን እና የመብት ጥያቄ ያነሱ ዜጎችን አሰልፎ ወደ እስር ቤት ማስገባት እንጂ ሕዝብን አሰልፎ ወደ አደባባይ ማውጣት አይጠይቅም›› በሚል መልስ ከወትሮው በላቀ መልኩ ግንቦት ሃያ መከበሩን ታስረዳው ጀመር፡፡ አቦይን በምሕረት በፈታው መንግሥት የታሰሩት አቶ ታዲዮስ ታንቱም ‹‹እዚህ እስር ቤት የተገኘነው እኮ አጥፍተን ሳይሆን የግንቦት ሃያ በዓልን አክብሩ ተብለን ነው›› በማለት በመስኪ ሐሳብ መስማማታቸውን ገለጹ፡፡ በወሬው መሀከልም ከፊት ለፊታቸው ካለ ግድግዳ ላይ የተሰቀለው ቴሌቪዥን ‹‹ከአፍታ በኋላ ልዩ ልዩ ዜናዎች ስለሚኖሩን ባሉበት ይጠብቁን›› የሚል መልዕክት አስተላለፈ። ያን ጊዜም በወያኔ ዘመን ወደ እስር ቤት ከገባ በኋላ የታሰረበትን ጥፋት ከተመስገን በየነ አንደበት ሲያዳምጥ የኖረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ‹‹ከመኮነን መንትያ ልጆች አንዱ ወንጀሌን ቢነግረኝ…›› ከሚል ንግግር ጋር ሪሞቱን አንስቶ ቻናል ይቀያይር ጀመር፡፡ ‹‹የመኮነን መንትያ ልጆች እነማን ናቸው›› ተብሎ ሲጠየቅም ‹‹መሳይ መኮነን እና ናትናኤል መኮነን ይባላሉ›› የሚል መልስ ሰጥቶ በየቻናሉ ሲፈልጋቸው ከቆየ በኋላ ከአቶ ደመቀ መኮነን ውጭ ማንንም ማግኘት ስላልቻለ ቻናሉን ፋና ላይ አድርጎ ሪሞቱን አስቀመጠው፡፡ በዚህም ቻናል ‹‹በሕግ ማስከበር ዘመቻው በዝርፊያ፣ በሕገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር፣ የሕብረተሰቡን ሰላም በማወክና በኮንትሮባንድ ንግድ… የተጠረጠሩ ከአምሥት ሺህ በላይ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ›› የሚል ዜና ሲከታተል ከቆየ በኋላ የኮንትሮባንድ ዜናው እሱን የሚወክል ሆኖ ስላላገኘው ቻናሉን አሚኮ ላይ አድርጎ ‹‹ሕገ መንግሥቱን በመናድ የተጠረጠሩ…›› የሚል ዜና ይጠብቅ ያዘ፡፡ በዚህ መሀከልም ወደ ታፋኞቹ የመጣ አንድ የፖሊስ አዛዥ ‹‹በአንዳንድ ነገሮች ላይ ላነጋግራችሁ ስለምፈልግ ሰብሰብ ብላችሁ ተቀመጡ›› የሚል ትዕዛዝ ከሰጣቸው በኋላ ማስታወሻ ደብተሩን ገልጦ ከፊታቸው ተቀመጠ፡፡ ከደርዘን በላይ ከሚሆኑ ታዋቂ ጋዜጠኞች መሀከል እራሱን ያገኘው የፖሊስ አዛዥም ‹‹መቅረጸ ድምጽና ካሜራ ሳትይዙ የመጣችሁት ለምንድን ነው?›› ብሎ ሊቆጣቸው ካሰበ በኋላ ከፊቱ የተገኙት ታስረው እንጂ ለጋዜጣዊ መግለጫ ተጠርተው አለመሆኑ ትዝ ሲለው ‹‹የእስረኛ አያያዛችን እንዴት አገኛችሁት? ጤንነታችሁስ እንዴት ነው?›› በማለት ጠየቀ፡፡ ለዚህም ጥያቄ አቶ ታዲዮስ ታንቱ የሰጡት መልስ እንዲህ የሚል ነበረ፡፡ ‹‹የታፈንበት መንገድ ከኮቪድ ጋር የሚመሳሰል ቢሆንም ኤካ ሆስፒታል ሳንገባ አብዛኞቻችን አገግመናል››