✥❖ተዋህዶ ሀይማኖቴ❖✥
አይነ ስዉር ባያያትም ፀሀይ ትወጣልች ምናፍቃን ባይገባችዉም ድንግል ማርያም ታማልዳልች https://t.me/joinchat/n3YAKpHXZN5kNzQ0
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
189
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
መስቀል አበባ | ዘማሪ በሱፍቃድ አንዳርጋቸው
መስቀል አበባ ነህ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
አዝ____
መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር
አደይ አበባ ስነ ስቅለቱ
መስቀል አበባ ዕሌኒ አገኘች
አደይ አበባ ደገኛይቱ
አዝ____
መስቀል አበባ ጥራጊ ሞልተው
አደይ አበባ አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ ጢሱ ሰገደ
አደይ አበባ መስቀል ካለበት
አዝ____
መስቀል አበባ ወንዙ ጅረቱ
አደይ አበባ ሸለቆ ዱሩ
መስቀል አበባ አሸብርቀው ደምቀው
አደይ አበባ ላንተ መሰከሩ
@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All
መስቀል አበባ.mp33.04 MB
4110
ባለውለታዬ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ባለውለታዬ /2/ ከአመድ ያነሳኸኝ
ከትብያ ተጥዬ ተመስገን ጌታዬ
አዝ____
በሩን ቢዘጋብኝ ስምኦን ጨክኖ
ዝቅ አድርጎ ቢያየኝ ከአይሁድ ጋር ሆኖ
እንድቀርብ ወደ እርሱ አዘዘ ጌታዬ
እግሩን አጥበዋለሁ ወድቄ በእንባዬ
አዝ____
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
መዓረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በየሱስ ክርስቶስ
አዝ____
ድንጋይ የጨበጡ ፈራጆች ከበዉኝ
ነውሬን ዘርዝረው ጌታ ፊት አቆሙኝ
ፈረደችባቸው ሃጢያትም በነርሱ
በሰላም ሂድ ብሎ ምሮኛል ጉሱ
አዝ____
የማምነውን አምላክ አውቀዋለሁ እኔ
በሰራልኝ ስራ በእድሜ በዘመኔ
ፍቅሩን ተሸክሟል የልቤ ትከሻ
ልለየው አልችልም እስከመጨረሻ
አዝ____
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
መዓረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በየሱስ ክርስቶስ
@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All
ባለውለታዬ_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ.mp34.66 MB
በዙሪያችን_ካሉ_ድንቅ_ምስክሮች_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ.mp35.63 MB
ምስጋና_በመቅደስህ_ዘማሪ_ገብረዮሐንስ_ገብረፃድቅ_.mp33.97 MB
ምልክቴ ነሽ ዘማሪ አቤል መክብብ.mp33.85 MB
አብሠራ_ገብርኤል_ዘማሪ_ዲያቆን_ፍሬዘር_ደሳለኝ.mp310.73 MB
ድንግል_ፈጣሪዋን_ወለደችው_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ.mp36.16 MB
3600
++ሰው እንጂ እግዚአብሔር አልረሳኝም+++
በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ፅኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደኃ ፣የሚበላውን የሚቸገር ረሃብተኛ ፣ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርብ ሆኖ ይታዘብ የነበረው ወዳጁ እንዲህ አለው ‹ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማስገኘት ካልቻለ የመጸለይህ ትርጉም ምንድር ነው? በቃ ፈጣሪህ አልሰማህም ማለት ነው!› ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያሃ ምስኪን ክርስቲያን ግን እንዲህ ሲል መለሰለት ‹እግዚአብሔርማ አልረሳኝም! ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ ነግሮት ነበር፡፡ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን ይህ ሰው ረስቶኛል!!!›
ክርስቲያኖች ለምን አንዳንዶች ከዕለት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፤ አንዳንዶች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ እንጀራ ያጣሉ ? መቼም ‹ለሰው ፊት የማያዳላ› እግዚአብሔር አድልዎ ኖሮበት ነው አትሉም?! ይህስ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙት ምንም የሌላቸውን በመርዳት እና በመመገብ በባሕርይው መግቦትን ገንዘብ ያደረገውን አምላክ በጸጋ እንዲመስሉትና በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡
ስለዚህ ‹የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ› ብለን የለመንነው አምላክ ከዕለት እንጀራችን አትርፎ የሚሰጠን ይህን አምላካዊ አደራ እንድንወጣም ስለሚፈልግ እንደሆነ ብንረዳው እንዴት መታደል ነበር!!!ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
4110
Repost from ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
🌼 "የዕንቁጣጣሽ" ሥያሜ አመጣጥ?
ዓመታት ተፈጽመው አዲስ ዓመት ስንጀምር ቅዱስ ዮሐንስ፣ ዓውደ ዓመት፣ አዲስ ዓመት ፣ ዕንቁጣጣሽ እየተባለ ይጠራል፡፡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንደሚያስረዱት ዕንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይም ጥንተ ታሪክ በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪቃ ለካም ደረሰችው፡፡
በአፍሪቃ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኃ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት «ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ» ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡
ሁለተኛው ደግሞ የሀገራችን ንግሥት ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ዜና ጥበብ እየሰማች ስታደንቅ ትኖር ነበር፡፡ በጆሮዋ የሰማችውን በዓይኗ ዓይታ ለመረዳት ስለፈለገች በግመሎች ላይ ሽቱና እጅግ ብዙ ወርቅ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኝ በኢየሩሳሌም የማይገኝ ልዩ ልዩ ገጸ በረከት አስጭና ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ገባች፡፡
ከንጉሡ ሰሎሞንም ጋር ተገናኝታ የያዘችውን ገጸ በረከት ከሰጠችው በኋላ ብዙ ነገሮችን ጠየቀችው፡፡ እርሱም አንድ ነገር ላይ ሰውሮ ሁሉንም ገለጸላት፡፡ ቤተ መንግሥቱንም፣ በቤተ መንግሥቱ የሚገኙ እጅግ በጣም የከበሩ ዕቃዎችን ሁሉ አስጎበኛት፡፡
ሲያበቃ «ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንልሽ» ሲል እጅግ በጣም የከበረ ዕንቁ አበረከተላት/ሰጣት/፡፡ ወሩም ወረኃ መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው መጥቷል፡፡ አሁን ከሚፈጸመው ሥነ ሥርዓት ደርሶ በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ የሚከበረውም መስከረም አንድ ቀን ነው፡፡
አንድም «ዕንቁ ዕፅ አወጣሸ» ብሎ የአበባውን መፈንዳትን ያስረዳናል፡፡
መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይህ በሺዎች የሚቆጠሩ ባለማሕተቦች የተቀላቀሉት የዝማሬ ዳዊት ቻናል ዩቲዩብ ነው ሊንኩን ተጭነው subscribe በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ!
https://www.youtube.com/channel/UC8iS8VUpEphoIVnfhsC2WdQ
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
2500
Show all...
✥❖ተዋህዶ ሀይማኖቴ❖✥
አይነ ስዉር ባያያትም ፀሀይ ትወጣልች ምናፍቃን ባይገባችዉም ድንግል ማርያም ታማልዳልች
https://t.me/joinchat/n3YAKpHXZN5kNzQ04510
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.