cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሩዋድ የበጎ አድራጎት እና መረዳጃ ማሀበር®

ጉዞ ወደ ከፍታ ☆መረጃ ለማግኘት telegram:- @buki1453 @Esoo_017 @Abunehyan1

Show more
Advertising posts
391
Subscribers
-124 hours
-37 days
No data30 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
° ' ቀብር ውስጥ ያለው ሰውዬ በጣም የሚመኘው ነገር ምንድነው ብላችሁ ታስባላችሁ ' ብለው እኮ ጠየቁ ተከታዮቻቸውን 😔 ~ ' በጣም የሚመኘው ነገር ሁለት ረከዓ መስገድ ነው ብለን እናስባለን ' አሏቸው ። ~ ' እሺ እሱ አልቻለም እናንተ ስገዱ ' አሉን😔 ~ ይሄ ሰውዬ አልቻለም እድል የለውም አይደል እንዴ ? ~ እናንተ እኮ እድል አላችሁ 🥹 << ቀብለ ፈወዋቲል ዐዋን >> ጊዜው ከማለፉ በፊት… በቃ እናንተ ተጠቀሙበት ¡¡
370Loading...
02
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬ ጉዳዮቻችንን ለማስፈፀም ወደ ሰዎች ስንደውል "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም…!" …"የደወሉላቸው ደንበኛ ቴሌፎን ለጊዜው ጥሪ አይቀበልም!"…የሚሉ የኦፕሬተር ድምፆች አሰልችተውናላ? በቃ ለነሱ ብዙም ቦታ አንስጥ... ወደ ጌታችን የምናደርገው ጥሪ ከመሰል መሰናክሎች የጠራ በመሆኑ እንደሰት…መቆራረጥ የሌለው…ፈጣንና ቀልጣፋ ነው…!!🤌🏼 ጌታችን አሁን አልገኝም አይልም..አለሁ….."ለምኑኝ እቀበላችሗለሁ" እንጂ!! መስመሩ በአለም ህዝቦች በጠቅላላ እና በአንድ ሰዓት ጥሪ ቢደረግበት እንኳን ተይዟል አይለንም…!!!..ሁሌም 24 ሰዓት ክፍት ነው በዛ ላይ ወጪ የለውም.......!! . ከእኛ የሚጠበቀው የቂን የተባለውን ሲም ካርድ ተጠቅመን ወደርሱ መደወል ብቻ ነው…🤳🏽ጌታህ የአንተን ጥሪ ሁሌም ይቀበላል…እንደውም ኔትወርኩ የበለጠ ነፃ የሚሆንበትን እና ጥሪህ በፍጥነት ተሰሚነት የሚያገኝባቸውን ተጨማሪ የአየር ሰዓታት አመቻችቶልሃል!!♥♥ለይለቱል ቀድር የእድሉ ተጠቃሚ እንሁን…ታድያ ዱዓ ስታደርጉ እኔንም አትርሱኝ ዱኣ አድርጉልኝ!
500Loading...
03
Media files
380Loading...
04
●▬▬๑۩የኛ ነቢይ ሙሃመድﷺ۩๑▬▬● << የቂያማ እለት የኔን አማላጅነት የማግኘት ቅድሚያ ያለው ሰለዋትን በብዛት ያወረደ ሰው ነው ። >> ብለዋልና ሰለዋት በማብዛት አላህ ሱብሀነ ወተዓላ የነቢዩን ሙሀመድ ﷺ ሸፈዓ እንድናገኝ ያድርገን ። ●▬▬๑۩የኛ ነቢይ ሙሃመድﷺ۩๑▬▬●
380Loading...
05
አሞራው በሰማይ ላይ❤️ ነቢዩላህ ዳውድ በዙፋናቸው ላይ ተቀምጠው ሳለ አንዲት ሴት «ጌታህ ፍትሀዊ ነው ወይስ በዳይ?» የሚል ድንገተኛ ጥያቄን ሰነዘረች ለምን እንደዚህ እንዳለች ምክንያቷን ታብራራ ዘንድ ጠየቋት «አባታቸው የሞተባቸውን ሶስት የቲም ልጆችን አሳድጋለሁ ጉሮሯቸውን የምደፍነውም ጥጥ በመፍተልና በመሸጥ ከማገኘው ገንዘብ ነው። ዛሬ ግን ጥጤን ፈትዬ በጨርቅ ከረጢት ውስጥ አድርጌ ልሸጥ ወደ ሱቅ አመራሁ። በመንገዴ ላይ ሳለሁ አንድ አሞራ ከረጢቴን ይዞብኝ በረረ ለልጆቼ ዳቦ መግዣ አጣሁ በረሀብ እየተንገላቱ ነው ··· » ንግግሯን ሳትጨርስ በሩ ተንኳኳ። ፈቃድ ተሰጣቸውና ወደ ውስጥ ገቡ። አስር ነጋዴዎች ነበሩ። በእጃቸው 1000 ዲናር ይዘዋል ከመሐላቸው አንዱ መናገር ጀመረ «አንቱ የአላህ ነብይ ባህር ላይ እየተጓዝን ሳለ መርከባችን ተቀደደና መስመጥ ጀመረ። ሞታችንን በመጠባበቅ ላይ ሳለን አንድ አሞራ የተፈተለ ጥጥን የያዘ ቀይ የጨርቅ ከረጢት ከላይ ጣለልን። ቀዳዳውን በጨርቁ ደፈንን መርከባችንም ወደ ላይ ተንሳፈፈ ከሞት ዳንን። አላህ ለዋለልን ውለታ ምስጋና ይሆን ዘንድ እያንዳንዳችን መቶ መቶ ዲናር ለመስጠት ቃል ገባን። ይሄው ገንዘባችን እርስዎ ዘንድ ላሉ ሚስኪኖች ሰደቃ ይስጡት » በማለት ብሩን እንዲቀበሏቸው እጃቸውን ዘረጉ። ነቢዩላህ ዳውድም ወደ ሴትዬዋ በመዞር ጌታሽ አንቺን ከድካም አሳርፎ በየብስና በባህር ይነግድልሻል አንቺ ግን በዳይ ትይዋለሽ በይ ገንዘቡን ተቀብለሽ ይዘሽ ሂጂ በማለት አዘዟት።
1213Loading...
06
●የነብዩ ሙሃመድ ﷺ ታሪክ●                   ክፍል 5       ዝግጅት:- አብዱ  ሙሰማ ሀሰን ነብዩ صلى الله عليه وسلم በዚያ በጃሂሊያው ዘመን ራሱ ከወንጀል የተቆጠቡ ነበሩ።  በየትኛውም አስፀያፊ ስነምግባር አልተዘፈቁም። ክህደትና ውሸት አልፈፀሙም፤ ሙዚቃ አላዳመጡም። ቁማር አልተጫወቱም። ዝሙት ላይ አልወደቁም። እርቃናቸውን አልታዩም። ዐረፋን በመተው ሙዝደሊፋ ላይ አልቆሙም። ጣኦትን አልተሳለሙም። ለጣኦት የታረደንም ይሁን የአላህ ስም ያልተጠቀሰበትን እርድ አልበሉም። ከዕባ በጎርፍ በመጎዳቱ ምክንያት ሙሽሪኮቹ ከዕባውን አፍርሰው በሚገነቡበት ወቅት የ35 አመቱ ሙሀመድصلى الله عليه وسلم  ድንጋይ እየተሸከመ ያቀርብ ነበር። ሙሽሪኮቹም ከዕባውን ገንብተው ሲያጠናቅቁ ሀጀረል አስወድን የትኛው ጎሳ ከቦታው ላይ ያስቀምጠው በሚል በመካከላቸው ጭቅጭቅ ተፈጠረ። መጀመሪያ የደረሰ ሰው ይፍረድልን ብለው ተስማሙ። ድንገት ሙሀመድ ከውጭ ከተፍ አለ። ታማኙ ሰው መጣ ብለው ጮሁ። ሙሀመድም ጋቢ መሳይ ልብስ አምጡ አላቸውና ሀጀረል አስወድን ከጋቢው ላይ አስቀምጦ ሁሉም ጎሳ የጋቢውን ጫፍ በመያዝ ወደከዕባው እንድወስዱት ካስደረገ በኋላ ከልብሱ ላይ አንስቶ ቦታው ላይ አስቀመጠው። በዚህም ከፀብ ታደጋቸው። እነሱም የነብዩን ብልህነት ተገነዘቡ። ሀጀረል አስወድ ከጀነት ነጭ ሆኖ እንደወረደና በሰው ልጆች ወንጀል ተፅእኖ ምክንያት እንደጠቆረ የሚጠቁም ሀዲስ አለ። ነብዩ صلى الله عليه وسلم  ከመላካቸው በፊት ዐረቡ ዐለም እጅግ በጣም በከፋ የአሰተሳሰብ ኋላቀርነት ተዘፍቆ ነበር።በዚያ በጃሂሊያው ዘመን ድንጋይ እየተመረጠ ይመለካል። ዝሙት እንደክብር መገለጫ በይፋ ይፈፀማል። አራጣ በሰፊው ተንሰራፍቷል። ጎረቤት ይበደላል። በክት (የሞተ እንስሳ) ይበላል። ዝምድና መቁረጥ የተለመደ ባህል ነው።ጠንካራው የደካማውን ይቀማል። ሴት መውለድ ያስኮንናል። ከተወለዱም ከነህይወታቸው ይቀበራሉ። ድህነት ተፈርቶ ልጅ ይገደላል። አስካሪ መጠጥ የህዝቡ መለያ ነው። ባል ሚስቱን ሂጂና ከእከሌ  አርግዘሽልኝ ነይ ብሎ ይልካል። ባጭሩ ዐብደላህ ቢን ዐባስ  رضي الله عنه እንደገለፀው የዐረቦችን መሀይምነት ለማወቅ የፈለገ በ አንዓም ምእራፍ ውስጥ ከአንቀፅ 130 ጀምሮ የተጠቀሰውን ታሪካቸውን ማስተዋሉ በቂ ነው። ነብያቶች ባጠቃላይ  በህይወት ባሉበት ጊዜ የሙሀመድ ነብይነት ካጋጠማቸው የእሱ ተከታይ እና አጋዥ  ሊሆኑ ቃል ገብተዋል። እያንዳንዱ ነብይም ለተከታዮቹ ስለ ሙሀመድ ሳይናገር አላለፈም።  በትክክለኛው ተውራትና ኢንጅል ውስጥ ሙሀመድ በመገለጫዎቹም ብቻ ሳይሆን በስሙም  መጠቀሱ ለዚህ ግልፅ ማሳያ ነው።እንደ ወረቃ፣በሂራ፣ አቡ ተይሃን፣ ዐብደላህ ቢን ሰላም፣ ከዕቡ አልአህባር ፣ዐብደላህ ቢን ዐምር፣ የዐሙሪያው መነኩሴ እንድሁም የሩሙ ንጉስ ( ሂረቅል)  አይነት የመፅሀፉ ባለቤቶች ስለሙሀመድ ምስክርነት መስጠታቸው  ይሄንኑ አረጋጋጭ ነው። ሊላኩ አካባቢ ደግሞ የሙሀመድ መምጣት ወሬ በሰፊው ተሰራጨ። ጠንቋዮች ሳይቀሩ ስለሙሀመድ صلى الله عليه وسلم መተንበይ ጀምረው ነበር። ታዲያ የዚህ ወሬ መሠራጨት አንዳንዶች ሙሀመድን ዝግጁ ሆነው እንድጠብቁ ጥሩ እድል ፈጥሮላቸዋል። አንሷሮች እስልምናን እንድቀበሉ ፈር የቀደደላቸውም ይሄው ወሬ ነበር። ሰልማንም رضي الله عنه የመነኩሴውን ጥቆማ ተከታትሎ ሰለመ። ነብይ ከመሆናቸው በፊት ድንጋይ ሰላምታ እንደሚያቀርብላቸው፣ በህልም የሚያዩት ነገር  በተመሳሳይ መልኩ በእውን እንደሚከሰት፣ የሆነ ወጣ ያለ ድምፅ እንደሚሰሙ እና ያልተለመደ ብርሃን እንደሚመለከቱ ተናግረዋል። ኋላ ላይ ደግሞ ከሰዎች ራቅ ማለትን ወደዱና ለቀናቶች የሚሆንን ስንቅ በመያዝ ወደ ሂራእ ዋሻ እየሄዱ ያመልኩ ጀመር። ከእለታት በአንዱ  ሰኞ በዋሻው ውስጥ እንዳሉ መላኢካው ጂብሪል በልብስ ጠቅልሎ ከጨመቃቸው በኋላ አንብብ አላቸው። ማንበብ አልችልም ብለው መለሱ። ከሶስተኛው ምልልስ በኋላ ከመጀመሪያዋ የቁርአን ምእራፍ (የ ዐለቅ ምእራፍ) አምስቱን አንቀፆች አነበበላቸው። በአብዛኛዎቹ ቀደምቶችና ተከታዮቻቸው አቋም መሠረት መጀመሪያ የወረደው የቁርአን ምእራፍ የዐለቅ/ቀለም ምእራፍ ሲሆን ከእሷም ውስጥ የመጀመሪያዎቹ 5 አንቀፆቸ ናቸው። ነብዩም صلى الله عليه وسلم በክስተቱ ተደናግጠው እየተንቀጠቀጡ ኸዲጃ  رضي الله عنها ዘንድ ደረሱ። ሸፍኑኝ ሸፍኑኝ አሉ። በልብስ ሸፈነቻቸው። ቀጥለውም አሁንኳ ለነፍሴም ስጋት እያደረብኝ ነው። እብደትም እንዳያጋጥመኝ እየሰጋሁ ነው አሏት። ኸዲጃ رضي الله عنها ግን ኧረ ፍፁም! አንተ ለዚህ የምትገባ ሰው አይደለህም ብላ መልካም ጎኖቹን ከጠቃቀሰች በኋላ ለማንኛውም እስኪ ወደ አጎቴ ልጅ ወረቃ ጋር ልውሰድህ ብላ አስመከረቻቸው። ወረቃም ሙሀመድን ያጋጠመው ሙሳን ያጋጠመው አይነት እንደሆነ፣ ከሀገር እንደሚባረርም ጠቁሞ በሚሰደድበት ወቅት በህይወት ካለ ጠንከር ያለ እገዛ እንደሚያደርግለትም ነገረው። ወረቃ ቢን ነውፈል رضي الله عنه ሙሀመድ صلى الله عليه وسلم   መልእክተኛ ከመሆናቸው በፊትም ቢሞት በነብይነታቸው ግን አምኖ ነበር። ሸይኽ አልባኒ ትክክለኛ ባሏቸው  ሀዲሶችም ወረቃ የጀነት መሆኑ ተጠቁመዋል። ከቀደምቶች ኢማሙ ጦበሪ ፣በገውይ፣ ኢብኑ ቃኒዕ እንድሁም ከዘመናችን መሻይኾች ሸይኽ ዑሰይሚንና ሸይኽ ፈውዛን ከወንዶች የመጀመሪያው አማኝ ወረቃ እንደሆነና እና ከሶሃቦችም እንደሚመደብ ይጠቅሳሉ። በመጀመሪያው የቁርአን ምእራፍ ነብይነታቸው ከታወጀ በኋላ ለተወሰኑ ጊዜያቶች ራእዩ ተቋረጠ። ነብዩም صلى الله عليه وسلم  በመቋረጡ ምክንያት ከባድ ሀሳብ ገባቸው። ከእለታት አንድ ቀን ቆመው በነበሩበት ሰአት የሆነ ድምፅ ሰሙ። ቀጥ ብለው  ሲመለከቱ ያኔ በሂራእ ዋሻ የታገላቸውን መላኢካ በሰማይና በመሬት መካከል በኩርሲይ ላይ ተቀምጦ አዩት። በመጀመሪያው ቀን የደረሰባቸውን ትግል (ጭንቀት) አስታወሱና በድንጋጤ  ቤት ገብተው ሸፍኑኝ ሸፍኑኝ አሉ። እንደተሸፋፈኑም የሙድደሲር ምእራፍ ወረደላቸው። አንተ ተሸፋፋኙ ሆይ። ተነስና አስጠንቀቅ.... የሚል ትእዛዝ ደረሳቸው። ይቀጥላል....... ቀጣይ ይትሉ ❤️           ©Hisnul_Muslim99
860Loading...
07
Media files
1110Loading...
08
✅እግዚአብሄር :– እኔ ሰው አይደለሁም።( ሆሴዕ 11:9 ) ✅ኢየሱስ :– እኔ ሰው ነኝ።(ዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ( ትንቢተ ሆሴዕ 11:9 ) እኔ እግዚአብሔር አምላክ ነኝ እንጂ #ሰው_አይደለሁምና፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ሰው ነኝ ይላል (የዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ነገር ግን አሁን ከእግዚአብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን #ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ:: ነገር ግን ነገር ግን........ ኢየሱስ ሰው ነኝ አምላክ አይደለሁም እያለ እየተማፀናቹ እናንተ ግን አይ  ኢየሱስ አምላክ ነህ፣ ጌታ ነህ፣ ፈጣሪ ነህ ወዘተ..... ብላችሁ የምታመልኩት ከሆነ ይህን መልዕክት በአንደበቱና በግልፅ  አስቀምጦላቹሃል፣ የማቴዎስ ወንጌል 7 ፣ 21 በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ #ጌታ_ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥#የሚለኝ_ሁሉ_መንግሥተ_ሰማያት_የሚገባ_አይደለም። 22 በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። 23 የዚያን ጊዜም። #ከቶ_አላወቅኋችሁም፤ #እናንተ_ዓመፀኞች፥  #ከእኔ_ራቁ_ብዬ_እመሰክርባቸዋለሁ። ስለዚህ ኢየሱስን ምትወዱት ከሆነ ቃሉንና ምክሩን ስሙ! ከፊቴ ጥፉ አላውቃችሁም እላቹሃለው እያላቹ ነው። በወንጌል ካላፈሩ እስኪ ሼር አድርጉት ይህ 100% ከመፅሀፍ ቅዱስ ከ (ወንጌል) ስለወጣ ሁሉም #ክርስቲያን  #ሼር ያድርገው። 📱 “እየሱስ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የፈጣሪ መልእክተኛ”  ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ 💥1• “የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የኣብ ነው እንጂ የኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 14:24) ✋ የማን ነው ኣለ? ••••• የላከኝ የኣብ√ በዚህ ጥቅስ መሰረት ወልድ( እየሱስ) የኣብ መልእክተኛ ነው። 💥 2• “እኔ ከራሴ ኣንዳች ላደርግ ኣይቻለኝም እንደሰማሁ እፈርዳሎ ፍርዴም ቅን ነው የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን ኣልሻምና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:30) ✋ የማን ፈቃድ ኣለ? ••••• የላከኝን√ ማነው የላከው? እየሱስ ኣምላክ ከሆነ, ኣምላክን የሚልክ ደግሞ ማነው? ኣምላክ ይልካል ወይስ ይላካል? 💥 3• “ቃሌን የሚሰማ የላከኝም የሚያምን የዘላለም ሂወት ኣለው”( የዬሐንስ ወንጌል 5:24) ✋ ማንን የሚያምን ኣለ? ••••••• የላከኝን√ ማነው የላከው? 💥 4• “ኢየሱስም ጮኸ እንዲህም ኣለ በኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 12:44) ✋ በኢየሱስ ማመን በማን ማመን ነው? •••••• በላከው√ ማነው የላከው? 💥 5• “እኔ ከራሴ ኣልተናገርሁምና ነገር ግን የላከኝ ኣብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 12:49) ✋ እዚህ ላይ ደግሞ ” የላከኝ ኣብ” በማለት የኣብ መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ተናግርዋል። 💥6• “የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 8:26) ✋ ኢየሱስን የላከ እውነተኛው ማነው? 💥 7• “የላከኝም ኣብ ሰለኔ ይመሰክራል”( የዬሐንስ ወንጌል 8:18) ✋ማን ኣለ? ••••• የላከኝ ኣብ√ 💥8• “ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም ኣላቸው ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ 7:16) ✋ ትምህርቱ ከማን ነው?•••••ከላከው√ ማነው የላከው? 💥 9• “እኔም በራሴ ኣልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 7:28) ✋ ኢየሱስን የላከ የማይታወቅ እውነተኛው ማነው? 💥 10• “እኔንም የጣለ የላከኝም ይጥላል”( ሉቃስ ወንጌል 10:16) ✋የላከኝን? ማነው የላከው? 💥11• “ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር ኣልተላክሁም ኣለ”( ማቴዎስ 15:34) ✋ወደ እስራኤል መልእክተኛ ኣድርጎ የላከው ማነው? 💥12• “ኣንተም እንደላክኸኝ ኣመኑ”( የዬሐንስ ወንጌል 17:8) ✋ማነው የላከው? 💥13• “ይህ የማደርገው ስራ ኣብ እንደላከኝ ስለኔ ይመሰክራልና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:36) ✋ኣብ እንደላከኝ በማለት መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ይናገራል። 💥14• “የላከኝ ኣብም እርሱ ስለኔ መስክሮዋል”( የዬሐንስ ወንጌል 5:37) ✋ምን ያደረገኝ ኣብ? •••••••• የላከኝ√ 💥15• “እኔ ከእግዚኣብሄር ወጥቼ መጥቻለሁና እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ ኣልመጣሁም”( የዬሐንስ ወንጌል 8:42) ✋ከእግዚኣብሄር የተላከ መልእክተኛ መሆኑን ይነግረናል። 💥16• “ባሪያ ከጌታው ኣይበልጥም መልእክተኛም ከላከው ኣይበልጥም” ( የዬሐንስ ወንጌል 13:16) መልእክተኛው ማነው? ላኪውስ ማነው? 💥17• “ኣብ እንደላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኃለሁኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 20:21) ✋ኣብ እንደላከኝ በማለት የኣብ መልእክተኛ እንደሆነ በግልፅ ነግሮናል።
1350Loading...
09
( ﺍللَّهُمَّ ﺻَﻞِّ ﻋَﻠَﻰ ﺳَﻴِّﺪِﻧَﺎ مُحَمَّدٍ ﻋَﺒْﺪِﻙَ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻚَ ﺍلنَّبِيِّ ﺍﻷُﻣِّﻲ ﻭَﻋَﻠَﻰ ﺁﻟِﻪِ ﻭَﺻَﺤْﺒِﻪِ وَسَلِّمْ تَسْلِيماً ) Selewat to be said 80 or 100 times on Friday after asr. ጁሙዐ ከአስር ቡሀላ 80 ወይም 100 ጊዜ የሚደረግ ሰለዋት
1250Loading...
10
ክብር ለሴቶች . 1⃣. ባል በሚስቱ ላይ ከወሰለተ ቅጣቱ እስኪሞት ድረስ በድንጋይ መወገር ነው፡፡ 2⃣. 2ኛ ሚስት አግብቶ እኩል ካላስተዳደር የትንሳኤ ቀን ወደ ጎን ተጣሞ ይቀሰቀሳል፡፡ 3⃣.ጥሎሽ ይህን ያህል እሠጣታለሁ ብሎ ቃል ገብቶ ካልሠጠ እሱ ሌባ ነው፡፡ 4⃣. የፈታት አንደሆነ ከሠጣት ነገር ዉስጥ አንዳችም ነገር መውሰድ የለበትም፡፡ አሳፋሪ ነው አትውሰዱ ይላል ቁርኣን፡፡ 5⃣. የዉርስ መብቷን የማይሠጣት ከሆነ የአላህን ድንበር ተላለፈ፡፡ የአላህን ድንበር የሚተላለፍ ራሱን ምንኛ በደለ!፡፡ 6⃣ ሴትን ልጅ በመምታት ይሁን በሌላ ነገር ያዋረዳትና ዝቅ ያደረጋት እሱ የተዋረደ ነው፡፡ 7⃣. ከአራትወር በላይ ጥሏት የጠፋ እንደሆነ የመለያየት መብት አላት፡፡ 8⃣. እንደ እናቱ ሊያያት አይገባም፤ ጀርባውን መስጠትና ፍራሹን መለየትም የለበትም፡፡ 9⃣. ‹አልቀርብሽም አንቺ ለኔ እንደ እናቴ ነሽ› ካላት በኋላ ቃሉን ማጠፍ ከሳበ ለቅጣቱ ስልሳ ቀናትን መፆም ይኖርበታል፡፡ 🔟. የጠላት እንደሆነም ይታገስ፡፡ በጠሉት ነገር ዉስጥ ብዙ መልካም ነገር ሊኖር ይችላልና ይላል ቁርአን ፡፡ 1⃣1⃣. አንደኛውን ባህሪዋን ቢጠላ ሌላውን ይውደድላት፡፡ ሰው ሆኖ ሙሉ የለምና፡፡ 1⃣2⃣ የፈታት እንደሆነም መልካምነቷን አይርሳ፡፡ ትዝታ አያረጅም፡፡ ምንም እንኳ የሆነ ጊዜ ጥሩ ትንፋሽ ተለዋውጠዋልና፡፡ 1⃣3⃣. በፍቺ ከተለያዩ ልጆቿን አይከልክላት፡፡ ቀለባቸውንም በትክክል ይስጣት ፡፡ 1⃣4⃣. ሴት ልጅ በሀብት ንብረቷ ሙሉ ባለመብት ናት፡፡ መፀወተች፣ ነገደችበት መብቷ ነው፡፡ በሷ ገንዘብ ባሏ አያገባውም፡፡ 1⃣5⃣ ድንበር ያለፈባት ሰው በተመሳሳይ መልኩ መቀጣት ይኖርበታል፡፡ 1⃣6⃣. ባሏን የምትታዘዘው በመልካም ነገር ያዘዛት እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ፈጣሪን በማመፅ ፍጡርን መታዘዝ የለም፡፡ 1⃣7⃣ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) የበኑ ቀይኑቃዕ ጎሣዎች ላይ የዘመቱት በሴት ልጅ ክብር ምክንያት ነው፡፡ 1⃣8⃣. ከሷ መከላከል የመስዋእትነት ደረጃ አለው፡፡ 1⃣9⃣. ኸሊፋ አል-ሙዕተሲም ዐሙሪያ ድረስ ጦራቸውን ያዘመቱት ስለሷ መነካት እልህ ብለህ ነው፡፡ (ይህን ታሪክ ፈልጋችሁ አንብቡ፡፡) 2⃣0⃣. በዉሸት በዝሙት የወነጀላት የሰማኒያ ጅራፍ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡ 2⃣1⃣. እሷን ማስተማር ግዴታ ነው፡፡ በመልካም ሁኔታ ማሳድግ የጀነት መግቢያ መንገድ ነው፡፡ 2⃣2⃣ ከእናቶች እግር ሥር አትነሱ፡፡ ጀነት በእግራቸው ሥር ነውና፡፡ 2⃣3⃣. እናት ከአባት በሦስት ደረጃዎች የበለጠች ናት፡፡ አል-ዐሪፊ እንደፃፉት… ራሳችሁ በድላችሁ፣ መብቶቻቸውን ሰርቃችሁ እስልምና ሴቶችን ይበድላል አትበሉ።💞💞💞
1401Loading...
11
💛ያ አላህ እኔ በጣም ታምሜያለሁ ስልህ”ከአላህ እዝነት ተስፋን አትቁረጡ” አልከኝ 💛ልቤ ውስጥ ጭንቀት አለ ስልህ” አላህን በማስታወስ ትረጋጋለች” አልከኝ» 💛ሰዎች አዛ ያድርጉኛል / ያሰቃዪኛል / ስልህ” አላህ እነዛ በዳዬችን በሚሰሩት ስራ ዘንጊ አይደለም” አለከኝ 💛ብቸኝነት ይሰማኛል ስልህ” እኛ ከደምሰሮቻቸው የበለጥ ቅርብ ነን” አልከኝ 💛 እኔ ወንጀለኛ ነኝ ተሳስቻለሁ ስልህ” ከአላህውጭ ወንጀልን የሚምር ማን አለና? “አለከኝ 💛ጌታየ አትተወኝ ስልህ” አስታውሱኝ አስታውሳቹሀለሁ » አልከኝ 💛 ህይወቴ በጭንቀት ተሞልቷል ስልህ “አላህን የሚፈራ መውጫውን የበጅለታለ “አልከኝ 💛ብዙ ነገር እፈልጋለሁ ስልህ” ለምኑኝ እቀበላቹሀለሁ”አልከኝ። -------------------------------- አዎ አላህ ካንተ ውጭ ማንም የለንም ጌታችን ሆይ እባክህን ዱአችንን ተቀበለን ወንጀላችንን ማረን
1491Loading...
12
ትንሽ ፈገግ በሉ‼ ============ ✍ «… ወሎ ውስጥ ነው አሉ። አንድ ቆለኛ ሙስሊምና አንድ ደገኛ ክርስቲያን ጓደኛሞች ይሆናሉ። ክርስቲያኑ ሙስሊሙን ግብዣ ጠራው። የገና በአል ነበር። ሙስሊሙ ሲመጣ  ምግቡ፣ መጠጡ፣ ሁሉ ነገር ተትረፍርፏል። ሰዎቹ ፌሽታ በፌሽታ፣ ፈንጠዝያ በፈንጠዝያ ሆነዋል። * ሙስሊሙ:– "ድግሱ ምንን ምክንያት በማድረግ ነው?" ብሎ ጠየቀ። "ጌታ ተወልዶ ነው" አሉት። ለሙስሊሙ ይሄ አስደንጋጭ ነበር። ጌታ ይወለዳል?! ግን ከሰው ቤት ነው ያለው ምን ይላል? "ህምምም" ብሎ የሆዱብ በሆዱ አድርጎ ዝም ይላል። ይህን ጉድ አይቶ ተመለሰ። ሌላ ጊዜ ተጠራ። ጥምቀት ነበር። ሲመጣ ድግሱ አሁንም እንደባለፈው የደመቀ ነው። ሰዎቹም ደስታ በደስታ ናቸው። "ይሄስ በአል ምንድን ነው ምክንያቱ?" ብሎ ጠየቀ። "ጌታ ተጠምቆ ነው" አሉት። ዘንድሮ ጉድ ተአምር እያየ ነው። እንዲያም ነው፤ እንዲህም ነው ሳይል ወደ ቤቱ ተመለሰ። አሁንም ተጠራ። ስቅለት ነበር። ሲመጣ ከወትሮው የተለየ ነገር አየ። ሰዎቹ የባለፈው አይነት ደስታ አይታይባቸውም። አዝነዋል። በባዶ እግር ይሄዳሉ። የሚበሉት ንፍሮ ነው። ግንባራቸውን በሳር መሳይ ነገር አስረዋል። ምን ጉድ ነው?! ቆለኛው ግራ ገብቶታል። * "ምንድን ነው የሆናችሁት?" አላቸው። "ጌታ ሞቶ ነው" አሉት። * "ያ ባለፈው የተወለደው?" ሲል ጠየቀ። "አዎ" አሉት። · ከዚያ ምን ቢል ጥሩ ነው:– "እኔኮ ቀድሞም ፌሽታ ስታበዙ እንደማያድግ አውቄያለሁ!" ©: የታሪኩ ምንጭ አንድ የደሴ ክርስቲያን ነው።
2393Loading...
13
( ﺍللَّهُمَّ ﺻَﻞِّ ﻋَﻠَﻰ ﺳَﻴِّﺪِﻧَﺎ مُحَمَّدٍ ﻋَﺒْﺪِﻙَ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻚَ ﺍلنَّبِيِّ ﺍﻷُﻣِّﻲ ﻭَﻋَﻠَﻰ ﺁﻟِﻪِ ﻭَﺻَﺤْﺒِﻪِ وَسَلِّمْ تَسْلِيماً ) Selewat to be said 80 or 100 times on Friday after asr. ጁሙዐ ከአስር ቡሀላ 80 ወይም 100 ጊዜ የሚደረግ ሰለዋት
1600Loading...
14
አቡ ነዎስ ማነዉ ? - አቡ ነዋስ ማለት በኢማም አሽ'ሻፊዒይ ዘመን የነበረ ሰዉ ሲሆን በጣም በመጥፎነት እና ኸምር (አስካሪ መጠጥ) በመጠጣት የታወቀ ነበረ። ከእለታት አንድ ቀንም ወደ መስጅድ እንሂድ ሲባል እንዲህ በማለት ግጥም እየገጠመ መልስ ሰጠ: ”مَاقالَ ربُكَ ويلٌ لِلذِينَ سَكِرُوا ولَكِن قالَ ويلٌ لِلمُصَلينَ“ ”دَعِ الْمَسَاجِدَ لِلعُبَادِ تَسْكُنُهَا وَطِفْ بِنَا حَولَ خَماّرٍ ليَسقِيناَ“ “መስጅዶችን ለአምላኪዎች ተዉላቸዉ ይቆዩበት  መጠጥ አጠጪ ቤት ዉሰደን እኛን ያጠጣበት” “ጌታህኮ ለሚሰክሩት ሰዎች ወየዉላቸሁ አላለም ነገር ግን እኮ ለሰላት ሰጋጆች ብሏል ወየዉላቸዉ” ከዛም ይህንን መጥፎ እና አፀያፊ ግጥም የሰማዉ የዘመኑ ኸሊፋ ሀሩን አራ'ሺድ በመቆጣት የአቡ'ነዋስን አንገት መምታት ፈለገ። አንድ ግለሰብም ገጣሚዎች እኮ የማይተገብሩትን ነዉ የሚናገሩት በማለት ኸሊፋዉን አረጋጋና ይቅርታ ተደረገለትበስተ መጨረሻም አቡ ነዋስ ሞተ፣ ጀናዛዉ ሲታጠብም በልብሱ ዉስጥ እንዲህ የሚል ግጥም ተፅፎ አገኙ : ”يَاربِ وإِن عَظُمَتْ ذُنوبِي كثْرةً فَلقَد علِمتُ بأن عَفوَك أعْظَمٌ إنْ كانَ لاَ يرْجُوكَ إِلاَّ مُحسِنٌ فَبِمنْ يَلوذُ ويَستَجيرُ المُجرِمُ“ “ጌታዬ ሆይ ወንጀሎቼ ቢሆኑ በብዛታቸዉ ግዙፍ በእርግጥም አወኩ ያንተ መሀርታ መሆኑን ግዙፍ አንተን ደግ እንጂ ሌላ ማንም የማይከጅል ከሆነ ታዲያ በዳዩ በማን ይጠበቃል በማን ይማራል” ”أَدعوكَ رَبِّ كَما أَمَرتَ تَضَرُّعاً فَإِذا رَدَدتَ يَدي فَمَن ذا يَرحَمُ ما لي إِلَيكَ وَسيلَةٌ إِلا الرَجا وَجَميلُ عَفوِكَ ثُمَّ أَنّي مُسلِمُ“ “ጌታዬ ሆይ በፍራቻ እጣራሀለዉ እንደዘዝከኝ እጄን በከንቱ ከመለስከዉ ታዲያ ማን ይማረኝ ወዳንተ ለመቃረብ ከመመፀን ዉጪ ምን አለኝ ይቅርባይነትህ ሲቀር ቀጥሎም ሙስሊም ነኝ” ይህንን ግጥምም ኢማም አሽ'ሻፊዒይ ካነበቡት በኋላ እሳቸዉ ከሙስሊሞች ጋር ሆነዉ ሰላተል ጀናዛን በአቡ ነዋስ ላይ ሰገዱት። 𝐓𝐞 ▸  https://t.me/Halal_post ♡ㅤ   ❍ㅤ     ⎙ㅤ     ⌲  ˡᶦᵏᵉ  ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ
1700Loading...
15
ቀይ ቀለም ያለዉ ወተት ¡ አቡ ጃዕፈር ሀሩን አር'ረሺድ የምዕመናን መሪ፣ እንዲሁም አምስተኛዉ የዓባሲዬች ኸሊፋ፣ ከረሱል ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም በኋላም 24ኛ ኸሊፋ ነበረ። አቡ ነዎስ ማለት ደግሞ በመጠጥ የታወቀ ነገር ግን ወደ አኺራ ሳይሄድ በፊት ተዉበት ያደረገ ሰዉ ነበረ። ከዕለታት አንድ ቀንም አቡ ነዋስ የተባለዉን ሰዉ መካ ከተማ ዉስጥ ኸምር (አስካሪ መጠጥ) ይዞ ተመለከተዉ፣ ኸሊፋዉ ሀሩን እንዲ ሲል ጠየቀ : ያ አቡ ነዎስ በእጅክ ምንድን የያዝከዉ? አለ አቡ ነዋስ : ወተት ነዉ አለ ኸሊፋዉ ሀሩን  : ወተት ቀይ ነዉ እንዴ ? አለ አቡ ነዋስም : "አንቱ አሚረል-ሙዕሚኒን ሆይ እርሶን ሲመለከት ነዉ ከእፍረቱ የተነሳ ወተቱ ቀይ የሆነዉ" አላቸዉ👌 (💣BOOM) 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥 https://t.me/Halal_post ♡ㅤ   ❍ㅤ     ⎙ㅤ     ⌲  ˡᶦᵏᵉ  ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ
1310Loading...
16
❤️‍🩹❤️‍🩹
1220Loading...
17
📖      በቁርኣን ታሪኮች ለምን ይወሱልናል??!! ከብዙ ጥበቦቹ ውስጥ አንዱ……    ታሪኮቹ በምታነብ ጊዜ ከምታውቀው ጠባቡ ዐለም ወደ የረሳኸው ሰፊው ዐለም ይዘውህ ይሻገራሉ። ያ………    የረሳኸው ሰፊው ዐለም ላይ የአንተው ዐይነት ሰዎች ነበሩ; እንደቆሰልከው የቆሰሉ; እንደታመምከው የታመሙ; እንደተበደልከው የተበደሉ።    ታግሰው; ተሸክመው; ችለው… አልፈዋል!! 🧿ብትዋሽ………     ከአንተ በፊት ኑሕ ተዋሽቷል። 🧿ብትታመጽ………      ከአንተ በፊት ሙሳ ታምጿል። 🧿ብትበደል………      ከአንተ በፊት ዩሱፍ ተበድሏል። 🧿ብትቸገር………      ከአንተ በፊት ዒሳ ተቸጋግሯል። 🧿ብትባረር………     ከአንተ በፊት ሙሐመድ ተባሯል። 🧿እምቢተኛ ልጅ ቢኖርብህ………     የኑሕ ልጅ ከአንተ ልጅ ቀድሞ እምቢ ብሏል። 🧿አመጸኛ ሚስት ብትኖርብህ………      የሉጥ ሚስት ከአንተዋ ቀድማ አምጻለች። 🧿አመጸኛ ባል ቢኖርብሽ………     የዐሲያ ባል ከአንቺ ባል ቀድሞ አምጿል። 🧿አጓጉል ዘመዶች ቢገጥሙህ………     የሙሐመድ ዘመዶች በዚህ ተግባር ቀድመዋል። ብቻህን አይደለህምና <> ቀለል አርገው!! እነርዚህ ታላላቆች መከራውን ለማለፍ በተሳፈሩበት መርከብ ከተሳፈርክ;    የደረሱበት ደረጃ ትደርሳለህ!! ታገስ……ታገስ……ታገስ ወንድሜ!! ✏️          ከፉርቃን ሰማይ ስር!!
2842Loading...
18
❤️‍🩹❤️‍🩹
1280Loading...
19
الدعاء الليل اللهُمَّ إني أمسيت منك في نعمةٍ وعافيةٍ وستر فــأتمم نعمتك عليَّ وعافيتك وسترك في الدنيا والآخرة3⃣ مرات ✨اللهُمَّ إني أمسيت أشهدك وأشهد حملة عرشك وملائكتـَك وجميع خلقك أنـَّك أنت الله لا إله إلا أنت وحدك لا شريك لك وأنَّ سيدنا محمداً عبدك ورسولك 4⃣مرات رضيت بالله ربـّاً وبالإسلام ديناً وبسيدنا محمدٍ صلى الله عليه وآله وسلم نبيـاً ورسولاً 3⃣مرات ✨ (حسبي الله لا إله إلا هو عليه توكلت وهو ربُّ العرش العظيم) 7⃣ مرات ✨ اللهُمَّ صلِّ على سيدنا محمدٍ وآله وصحبه وسلم 🔟مرات ✨ اللهُمَّ إني أسألك من فـُجـَاءَةِ الخير وأعوذ بك من فـُجـَاءَةِ الشرِّ ✨ اللهُمَّ أنت ربي لا إله إلا أنت خلقتني، وأنا عبدك وأنا على عهدك ووعدك ما استطعت، أعوذ بك من شرِّ ما صنعت، أبوء لك بنعمتك علي وأبوء بذنبي فاغفر لي فـإنـَّه لا يغفر الذنوب إلا أنت
1350Loading...
° ' ቀብር ውስጥ ያለው ሰውዬ በጣም የሚመኘው ነገር ምንድነው ብላችሁ ታስባላችሁ ' ብለው እኮ ጠየቁ ተከታዮቻቸውን 😔 ~ ' በጣም የሚመኘው ነገር ሁለት ረከዓ መስገድ ነው ብለን እናስባለን ' አሏቸው ። ~ ' እሺ እሱ አልቻለም እናንተ ስገዱ ' አሉን😔 ~ ይሄ ሰውዬ አልቻለም እድል የለውም አይደል እንዴ ? ~ እናንተ እኮ እድል አላችሁ 🥹 << ቀብለ ፈወዋቲል ዐዋን >> ጊዜው ከማለፉ በፊት… በቃ እናንተ ተጠቀሙበት ¡¡
Show all...
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬ ጉዳዮቻችንን ለማስፈፀም ወደ ሰዎች ስንደውል "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም…!" …"የደወሉላቸው ደንበኛ ቴሌፎን ለጊዜው ጥሪ አይቀበልም!"…የሚሉ የኦፕሬተር ድምፆች አሰልችተውናላ? በቃ ለነሱ ብዙም ቦታ አንስጥ... ወደ ጌታችን የምናደርገው ጥሪ ከመሰል መሰናክሎች የጠራ በመሆኑ እንደሰት…መቆራረጥ የሌለው…ፈጣንና ቀልጣፋ ነው…!!🤌🏼 ጌታችን አሁን አልገኝም አይልም..አለሁ….."ለምኑኝ እቀበላችሗለሁ" እንጂ!! መስመሩ በአለም ህዝቦች በጠቅላላ እና በአንድ ሰዓት ጥሪ ቢደረግበት እንኳን ተይዟል አይለንም…!!!..ሁሌም 24 ሰዓት ክፍት ነው በዛ ላይ ወጪ የለውም.......!! . ከእኛ የሚጠበቀው የቂን የተባለውን ሲም ካርድ ተጠቅመን ወደርሱ መደወል ብቻ ነው…🤳🏽ጌታህ የአንተን ጥሪ ሁሌም ይቀበላል…እንደውም ኔትወርኩ የበለጠ ነፃ የሚሆንበትን እና ጥሪህ በፍጥነት ተሰሚነት የሚያገኝባቸውን ተጨማሪ የአየር ሰዓታት አመቻችቶልሃል!!♥♥ለይለቱል ቀድር የእድሉ ተጠቃሚ እንሁን…ታድያ ዱዓ ስታደርጉ እኔንም አትርሱኝ ዱኣ አድርጉልኝ!
Show all...
●▬▬๑۩የኛ ነቢይ ሙሃመድﷺ۩๑▬▬● << የቂያማ እለት የኔን አማላጅነት የማግኘት ቅድሚያ ያለው ሰለዋትን በብዛት ያወረደ ሰው ነው ። >> ብለዋልና ሰለዋት በማብዛት አላህ ሱብሀነ ወተዓላ የነቢዩን ሙሀመድ ﷺ ሸፈዓ እንድናገኝ ያድርገን ። ●▬▬๑۩የኛ ነቢይ ሙሃመድﷺ۩๑▬▬●
Show all...
አሞራው በሰማይ ላይ❤️ ነቢዩላህ ዳውድ በዙፋናቸው ላይ ተቀምጠው ሳለ አንዲት ሴት «ጌታህ ፍትሀዊ ነው ወይስ በዳይ?» የሚል ድንገተኛ ጥያቄን ሰነዘረች ለምን እንደዚህ እንዳለች ምክንያቷን ታብራራ ዘንድ ጠየቋት «አባታቸው የሞተባቸውን ሶስት የቲም ልጆችን አሳድጋለሁ ጉሮሯቸውን የምደፍነውም ጥጥ በመፍተልና በመሸጥ ከማገኘው ገንዘብ ነው። ዛሬ ግን ጥጤን ፈትዬ በጨርቅ ከረጢት ውስጥ አድርጌ ልሸጥ ወደ ሱቅ አመራሁ። በመንገዴ ላይ ሳለሁ አንድ አሞራ ከረጢቴን ይዞብኝ በረረ ለልጆቼ ዳቦ መግዣ አጣሁ በረሀብ እየተንገላቱ ነው ··· » ንግግሯን ሳትጨርስ በሩ ተንኳኳ። ፈቃድ ተሰጣቸውና ወደ ውስጥ ገቡ። አስር ነጋዴዎች ነበሩ። በእጃቸው 1000 ዲናር ይዘዋል ከመሐላቸው አንዱ መናገር ጀመረ «አንቱ የአላህ ነብይ ባህር ላይ እየተጓዝን ሳለ መርከባችን ተቀደደና መስመጥ ጀመረ። ሞታችንን በመጠባበቅ ላይ ሳለን አንድ አሞራ የተፈተለ ጥጥን የያዘ ቀይ የጨርቅ ከረጢት ከላይ ጣለልን። ቀዳዳውን በጨርቁ ደፈንን መርከባችንም ወደ ላይ ተንሳፈፈ ከሞት ዳንን። አላህ ለዋለልን ውለታ ምስጋና ይሆን ዘንድ እያንዳንዳችን መቶ መቶ ዲናር ለመስጠት ቃል ገባን። ይሄው ገንዘባችን እርስዎ ዘንድ ላሉ ሚስኪኖች ሰደቃ ይስጡት » በማለት ብሩን እንዲቀበሏቸው እጃቸውን ዘረጉ። ነቢዩላህ ዳውድም ወደ ሴትዬዋ በመዞር ጌታሽ አንቺን ከድካም አሳርፎ በየብስና በባህር ይነግድልሻል አንቺ ግን በዳይ ትይዋለሽ በይ ገንዘቡን ተቀብለሽ ይዘሽ ሂጂ በማለት አዘዟት።
Show all...
የነብዩ ሙሃመድ ﷺ ታሪክ●                   ክፍል 5       ዝግጅት:- አብዱ  ሙሰማ ሀሰን ነብዩ صلى الله عليه وسلم በዚያ በጃሂሊያው ዘመን ራሱ ከወንጀል የተቆጠቡ ነበሩ።  በየትኛውም አስፀያፊ ስነምግባር አልተዘፈቁም። ክህደትና ውሸት አልፈፀሙም፤ ሙዚቃ አላዳመጡም። ቁማር አልተጫወቱም። ዝሙት ላይ አልወደቁም። እርቃናቸውን አልታዩም። ዐረፋን በመተው ሙዝደሊፋ ላይ አልቆሙም። ጣኦትን አልተሳለሙም። ለጣኦት የታረደንም ይሁን የአላህ ስም ያልተጠቀሰበትን እርድ አልበሉም። ከዕባ በጎርፍ በመጎዳቱ ምክንያት ሙሽሪኮቹ ከዕባውን አፍርሰው በሚገነቡበት ወቅት የ35 አመቱ ሙሀመድصلى الله عليه وسلم  ድንጋይ እየተሸከመ ያቀርብ ነበር። ሙሽሪኮቹም ከዕባውን ገንብተው ሲያጠናቅቁ ሀጀረል አስወድን የትኛው ጎሳ ከቦታው ላይ ያስቀምጠው በሚል በመካከላቸው ጭቅጭቅ ተፈጠረ። መጀመሪያ የደረሰ ሰው ይፍረድልን ብለው ተስማሙ። ድንገት ሙሀመድ ከውጭ ከተፍ አለ። ታማኙ ሰው መጣ ብለው ጮሁ። ሙሀመድም ጋቢ መሳይ ልብስ አምጡ አላቸውና ሀጀረል አስወድን ከጋቢው ላይ አስቀምጦ ሁሉም ጎሳ የጋቢውን ጫፍ በመያዝ ወደከዕባው እንድወስዱት ካስደረገ በኋላ ከልብሱ ላይ አንስቶ ቦታው ላይ አስቀመጠው። በዚህም ከፀብ ታደጋቸው። እነሱም የነብዩን ብልህነት ተገነዘቡ። ሀጀረል አስወድ ከጀነት ነጭ ሆኖ እንደወረደና በሰው ልጆች ወንጀል ተፅእኖ ምክንያት እንደጠቆረ የሚጠቁም ሀዲስ አለ። ነብዩ صلى الله عليه وسلم  ከመላካቸው በፊት ዐረቡ ዐለም እጅግ በጣም በከፋ የአሰተሳሰብ ኋላቀርነት ተዘፍቆ ነበር።በዚያ በጃሂሊያው ዘመን ድንጋይ እየተመረጠ ይመለካል። ዝሙት እንደክብር መገለጫ በይፋ ይፈፀማል። አራጣ በሰፊው ተንሰራፍቷል። ጎረቤት ይበደላል። በክት (የሞተ እንስሳ) ይበላል። ዝምድና መቁረጥ የተለመደ ባህል ነው።ጠንካራው የደካማውን ይቀማል። ሴት መውለድ ያስኮንናል። ከተወለዱም ከነህይወታቸው ይቀበራሉ። ድህነት ተፈርቶ ልጅ ይገደላል። አስካሪ መጠጥ የህዝቡ መለያ ነው። ባል ሚስቱን ሂጂና ከእከሌ  አርግዘሽልኝ ነይ ብሎ ይልካል። ባጭሩ ዐብደላህ ቢን ዐባስ  رضي الله عنه እንደገለፀው የዐረቦችን መሀይምነት ለማወቅ የፈለገ በ አንዓም ምእራፍ ውስጥ ከአንቀፅ 130 ጀምሮ የተጠቀሰውን ታሪካቸውን ማስተዋሉ በቂ ነው። ነብያቶች ባጠቃላይ  በህይወት ባሉበት ጊዜ የሙሀመድ ነብይነት ካጋጠማቸው የእሱ ተከታይ እና አጋዥ  ሊሆኑ ቃል ገብተዋል። እያንዳንዱ ነብይም ለተከታዮቹ ስለ ሙሀመድ ሳይናገር አላለፈም።  በትክክለኛው ተውራትና ኢንጅል ውስጥ ሙሀመድ በመገለጫዎቹም ብቻ ሳይሆን በስሙም  መጠቀሱ ለዚህ ግልፅ ማሳያ ነው።እንደ ወረቃ፣በሂራ፣ አቡ ተይሃን፣ ዐብደላህ ቢን ሰላም፣ ከዕቡ አልአህባር ፣ዐብደላህ ቢን ዐምር፣ የዐሙሪያው መነኩሴ እንድሁም የሩሙ ንጉስ ( ሂረቅል)  አይነት የመፅሀፉ ባለቤቶች ስለሙሀመድ ምስክርነት መስጠታቸው  ይሄንኑ አረጋጋጭ ነው። ሊላኩ አካባቢ ደግሞ የሙሀመድ መምጣት ወሬ በሰፊው ተሰራጨ። ጠንቋዮች ሳይቀሩ ስለሙሀመድ صلى الله عليه وسلم መተንበይ ጀምረው ነበር። ታዲያ የዚህ ወሬ መሠራጨት አንዳንዶች ሙሀመድን ዝግጁ ሆነው እንድጠብቁ ጥሩ እድል ፈጥሮላቸዋል። አንሷሮች እስልምናን እንድቀበሉ ፈር የቀደደላቸውም ይሄው ወሬ ነበር። ሰልማንም رضي الله عنه የመነኩሴውን ጥቆማ ተከታትሎ ሰለመ። ነብይ ከመሆናቸው በፊት ድንጋይ ሰላምታ እንደሚያቀርብላቸው፣ በህልም የሚያዩት ነገር  በተመሳሳይ መልኩ በእውን እንደሚከሰት፣ የሆነ ወጣ ያለ ድምፅ እንደሚሰሙ እና ያልተለመደ ብርሃን እንደሚመለከቱ ተናግረዋል። ኋላ ላይ ደግሞ ከሰዎች ራቅ ማለትን ወደዱና ለቀናቶች የሚሆንን ስንቅ በመያዝ ወደ ሂራእ ዋሻ እየሄዱ ያመልኩ ጀመር። ከእለታት በአንዱ  ሰኞ በዋሻው ውስጥ እንዳሉ መላኢካው ጂብሪል በልብስ ጠቅልሎ ከጨመቃቸው በኋላ አንብብ አላቸው። ማንበብ አልችልም ብለው መለሱ። ከሶስተኛው ምልልስ በኋላ ከመጀመሪያዋ የቁርአን ምእራፍ (የ ዐለቅ ምእራፍ) አምስቱን አንቀፆች አነበበላቸው። በአብዛኛዎቹ ቀደምቶችና ተከታዮቻቸው አቋም መሠረት መጀመሪያ የወረደው የቁርአን ምእራፍ የዐለቅ/ቀለም ምእራፍ ሲሆን ከእሷም ውስጥ የመጀመሪያዎቹ 5 አንቀፆቸ ናቸው። ነብዩም صلى الله عليه وسلم በክስተቱ ተደናግጠው እየተንቀጠቀጡ ኸዲጃ  رضي الله عنها ዘንድ ደረሱ። ሸፍኑኝ ሸፍኑኝ አሉ። በልብስ ሸፈነቻቸው። ቀጥለውም አሁንኳ ለነፍሴም ስጋት እያደረብኝ ነው። እብደትም እንዳያጋጥመኝ እየሰጋሁ ነው አሏት። ኸዲጃ رضي الله عنها ግን ኧረ ፍፁም! አንተ ለዚህ የምትገባ ሰው አይደለህም ብላ መልካም ጎኖቹን ከጠቃቀሰች በኋላ ለማንኛውም እስኪ ወደ አጎቴ ልጅ ወረቃ ጋር ልውሰድህ ብላ አስመከረቻቸው። ወረቃም ሙሀመድን ያጋጠመው ሙሳን ያጋጠመው አይነት እንደሆነ፣ ከሀገር እንደሚባረርም ጠቁሞ በሚሰደድበት ወቅት በህይወት ካለ ጠንከር ያለ እገዛ እንደሚያደርግለትም ነገረው። ወረቃ ቢን ነውፈል رضي الله عنه ሙሀመድ صلى الله عليه وسلم   መልእክተኛ ከመሆናቸው በፊትም ቢሞት በነብይነታቸው ግን አምኖ ነበር። ሸይኽ አልባኒ ትክክለኛ ባሏቸው  ሀዲሶችም ወረቃ የጀነት መሆኑ ተጠቁመዋል። ከቀደምቶች ኢማሙ ጦበሪ ፣በገውይ፣ ኢብኑ ቃኒዕ እንድሁም ከዘመናችን መሻይኾች ሸይኽ ዑሰይሚንና ሸይኽ ፈውዛን ከወንዶች የመጀመሪያው አማኝ ወረቃ እንደሆነና እና ከሶሃቦችም እንደሚመደብ ይጠቅሳሉ። በመጀመሪያው የቁርአን ምእራፍ ነብይነታቸው ከታወጀ በኋላ ለተወሰኑ ጊዜያቶች ራእዩ ተቋረጠ። ነብዩም صلى الله عليه وسلم  በመቋረጡ ምክንያት ከባድ ሀሳብ ገባቸው። ከእለታት አንድ ቀን ቆመው በነበሩበት ሰአት የሆነ ድምፅ ሰሙ። ቀጥ ብለው  ሲመለከቱ ያኔ በሂራእ ዋሻ የታገላቸውን መላኢካ በሰማይና በመሬት መካከል በኩርሲይ ላይ ተቀምጦ አዩት። በመጀመሪያው ቀን የደረሰባቸውን ትግል (ጭንቀት) አስታወሱና በድንጋጤ  ቤት ገብተው ሸፍኑኝ ሸፍኑኝ አሉ። እንደተሸፋፈኑም የሙድደሲር ምእራፍ ወረደላቸው። አንተ ተሸፋፋኙ ሆይ። ተነስና አስጠንቀቅ.... የሚል ትእዛዝ ደረሳቸው። ይቀጥላል....... ቀጣይ ይትሉ ❤️           ©Hisnul_Muslim99
Show all...
✅እግዚአብሄር :– እኔ ሰው አይደለሁም።( ሆሴዕ 11:9 ) ✅ኢየሱስ :– እኔ ሰው ነኝ።(ዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ( ትንቢተ ሆሴዕ 11:9 ) እኔ እግዚአብሔር አምላክ ነኝ እንጂ #ሰው_አይደለሁምና፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ሰው ነኝ ይላል (የዮሐንስ ወንጌል 8:40 ) ነገር ግን አሁን ከእግዚአብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን #ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ:: ነገር ግን ነገር ግን........ ኢየሱስ ሰው ነኝ አምላክ አይደለሁም እያለ እየተማፀናቹ እናንተ ግን አይ  ኢየሱስ አምላክ ነህ፣ ጌታ ነህ፣ ፈጣሪ ነህ ወዘተ..... ብላችሁ የምታመልኩት ከሆነ ይህን መልዕክት በአንደበቱና በግልፅ  አስቀምጦላቹሃል፣ የማቴዎስ ወንጌል 7 ፣ 21 በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ #ጌታ_ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥#የሚለኝ_ሁሉ_መንግሥተ_ሰማያት_የሚገባ_አይደለም። 22 በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። 23 የዚያን ጊዜም። #ከቶ_አላወቅኋችሁም፤ #እናንተ_ዓመፀኞች፥  #ከእኔ_ራቁ_ብዬ_እመሰክርባቸዋለሁ። ስለዚህ ኢየሱስን ምትወዱት ከሆነ ቃሉንና ምክሩን ስሙ! ከፊቴ ጥፉ አላውቃችሁም እላቹሃለው እያላቹ ነው። በወንጌል ካላፈሩ እስኪ ሼር አድርጉት ይህ 100% ከመፅሀፍ ቅዱስ ከ (ወንጌል) ስለወጣ ሁሉም #ክርስቲያን  #ሼር ያድርገው። 📱 “እየሱስ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የፈጣሪ መልእክተኛ”  ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ ̄ 💥1• “የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የኣብ ነው እንጂ የኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 14:24) ✋ የማን ነው ኣለ? ••••• የላከኝ የኣብ√ በዚህ ጥቅስ መሰረት ወልድ( እየሱስ) የኣብ መልእክተኛ ነው። 💥 2• “እኔ ከራሴ ኣንዳች ላደርግ ኣይቻለኝም እንደሰማሁ እፈርዳሎ ፍርዴም ቅን ነው የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን ኣልሻምና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:30) ✋ የማን ፈቃድ ኣለ? ••••• የላከኝን√ ማነው የላከው? እየሱስ ኣምላክ ከሆነ, ኣምላክን የሚልክ ደግሞ ማነው? ኣምላክ ይልካል ወይስ ይላካል? 💥 3• “ቃሌን የሚሰማ የላከኝም የሚያምን የዘላለም ሂወት ኣለው”( የዬሐንስ ወንጌል 5:24) ✋ ማንን የሚያምን ኣለ? ••••••• የላከኝን√ ማነው የላከው? 💥 4• “ኢየሱስም ጮኸ እንዲህም ኣለ በኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ ወንጌል 12:44) ✋ በኢየሱስ ማመን በማን ማመን ነው? •••••• በላከው√ ማነው የላከው? 💥 5• “እኔ ከራሴ ኣልተናገርሁምና ነገር ግን የላከኝ ኣብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 12:49) ✋ እዚህ ላይ ደግሞ ” የላከኝ ኣብ” በማለት የኣብ መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ተናግርዋል። 💥6• “የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 8:26) ✋ ኢየሱስን የላከ እውነተኛው ማነው? 💥 7• “የላከኝም ኣብ ሰለኔ ይመሰክራል”( የዬሐንስ ወንጌል 8:18) ✋ማን ኣለ? ••••• የላከኝ ኣብ√ 💥8• “ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም ኣላቸው ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከኔ ኣይደለም”( የዬሐንስ 7:16) ✋ ትምህርቱ ከማን ነው?•••••ከላከው√ ማነው የላከው? 💥 9• “እኔም በራሴ ኣልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው”( የዬሐንስ ወንጌል 7:28) ✋ ኢየሱስን የላከ የማይታወቅ እውነተኛው ማነው? 💥 10• “እኔንም የጣለ የላከኝም ይጥላል”( ሉቃስ ወንጌል 10:16) ✋የላከኝን? ማነው የላከው? 💥11• “ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር ኣልተላክሁም ኣለ”( ማቴዎስ 15:34) ✋ወደ እስራኤል መልእክተኛ ኣድርጎ የላከው ማነው? 💥12• “ኣንተም እንደላክኸኝ ኣመኑ”( የዬሐንስ ወንጌል 17:8) ✋ማነው የላከው? 💥13• “ይህ የማደርገው ስራ ኣብ እንደላከኝ ስለኔ ይመሰክራልና”( የዬሐንስ ወንጌል 5:36) ✋ኣብ እንደላከኝ በማለት መልእክተኛ መሆኑን በግልፅ ይናገራል። 💥14• “የላከኝ ኣብም እርሱ ስለኔ መስክሮዋል”( የዬሐንስ ወንጌል 5:37) ✋ምን ያደረገኝ ኣብ? •••••••• የላከኝ√ 💥15• “እኔ ከእግዚኣብሄር ወጥቼ መጥቻለሁና እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ ኣልመጣሁም”( የዬሐንስ ወንጌል 8:42) ✋ከእግዚኣብሄር የተላከ መልእክተኛ መሆኑን ይነግረናል። 💥16• “ባሪያ ከጌታው ኣይበልጥም መልእክተኛም ከላከው ኣይበልጥም” ( የዬሐንስ ወንጌል 13:16) መልእክተኛው ማነው? ላኪውስ ማነው? 💥17• “ኣብ እንደላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኃለሁኝ”( የዬሐንስ ወንጌል 20:21) ✋ኣብ እንደላከኝ በማለት የኣብ መልእክተኛ እንደሆነ በግልፅ ነግሮናል።
Show all...
👍 2
( ﺍللَّهُمَّ ﺻَﻞِّ ﻋَﻠَﻰ ﺳَﻴِّﺪِﻧَﺎ مُحَمَّدٍ ﻋَﺒْﺪِﻙَ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻚَ ﺍلنَّبِيِّ ﺍﻷُﻣِّﻲ ﻭَﻋَﻠَﻰ ﺁﻟِﻪِ ﻭَﺻَﺤْﺒِﻪِ وَسَلِّمْ تَسْلِيماً ) Selewat to be said 80 or 100 times on Friday after asr. ጁሙዐ ከአስር ቡሀላ 80 ወይም 100 ጊዜ የሚደረግ ሰለዋት
Show all...
ክብር ለሴቶች . 1⃣. ባል በሚስቱ ላይ ከወሰለተ ቅጣቱ እስኪሞት ድረስ በድንጋይ መወገር ነው፡፡ 2⃣. 2ኛ ሚስት አግብቶ እኩል ካላስተዳደር የትንሳኤ ቀን ወደ ጎን ተጣሞ ይቀሰቀሳል፡፡ 3⃣.ጥሎሽ ይህን ያህል እሠጣታለሁ ብሎ ቃል ገብቶ ካልሠጠ እሱ ሌባ ነው፡፡ 4⃣. የፈታት አንደሆነ ከሠጣት ነገር ዉስጥ አንዳችም ነገር መውሰድ የለበትም፡፡ አሳፋሪ ነው አትውሰዱ ይላል ቁርኣን፡፡ 5⃣. የዉርስ መብቷን የማይሠጣት ከሆነ የአላህን ድንበር ተላለፈ፡፡ የአላህን ድንበር የሚተላለፍ ራሱን ምንኛ በደለ!፡፡ 6⃣ ሴትን ልጅ በመምታት ይሁን በሌላ ነገር ያዋረዳትና ዝቅ ያደረጋት እሱ የተዋረደ ነው፡፡ 7⃣. ከአራትወር በላይ ጥሏት የጠፋ እንደሆነ የመለያየት መብት አላት፡፡ 8⃣. እንደ እናቱ ሊያያት አይገባም፤ ጀርባውን መስጠትና ፍራሹን መለየትም የለበትም፡፡ 9⃣. ‹አልቀርብሽም አንቺ ለኔ እንደ እናቴ ነሽ› ካላት በኋላ ቃሉን ማጠፍ ከሳበ ለቅጣቱ ስልሳ ቀናትን መፆም ይኖርበታል፡፡ 🔟. የጠላት እንደሆነም ይታገስ፡፡ በጠሉት ነገር ዉስጥ ብዙ መልካም ነገር ሊኖር ይችላልና ይላል ቁርአን ፡፡ 1⃣1⃣. አንደኛውን ባህሪዋን ቢጠላ ሌላውን ይውደድላት፡፡ ሰው ሆኖ ሙሉ የለምና፡፡ 1⃣2⃣ የፈታት እንደሆነም መልካምነቷን አይርሳ፡፡ ትዝታ አያረጅም፡፡ ምንም እንኳ የሆነ ጊዜ ጥሩ ትንፋሽ ተለዋውጠዋልና፡፡ 1⃣3⃣. በፍቺ ከተለያዩ ልጆቿን አይከልክላት፡፡ ቀለባቸውንም በትክክል ይስጣት ፡፡ 1⃣4⃣. ሴት ልጅ በሀብት ንብረቷ ሙሉ ባለመብት ናት፡፡ መፀወተች፣ ነገደችበት መብቷ ነው፡፡ በሷ ገንዘብ ባሏ አያገባውም፡፡ 1⃣5⃣ ድንበር ያለፈባት ሰው በተመሳሳይ መልኩ መቀጣት ይኖርበታል፡፡ 1⃣6⃣. ባሏን የምትታዘዘው በመልካም ነገር ያዘዛት እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ፈጣሪን በማመፅ ፍጡርን መታዘዝ የለም፡፡ 1⃣7⃣ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) የበኑ ቀይኑቃዕ ጎሣዎች ላይ የዘመቱት በሴት ልጅ ክብር ምክንያት ነው፡፡ 1⃣8⃣. ከሷ መከላከል የመስዋእትነት ደረጃ አለው፡፡ 1⃣9⃣. ኸሊፋ አል-ሙዕተሲም ዐሙሪያ ድረስ ጦራቸውን ያዘመቱት ስለሷ መነካት እልህ ብለህ ነው፡፡ (ይህን ታሪክ ፈልጋችሁ አንብቡ፡፡) 2⃣0⃣. በዉሸት በዝሙት የወነጀላት የሰማኒያ ጅራፍ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡ 2⃣1⃣. እሷን ማስተማር ግዴታ ነው፡፡ በመልካም ሁኔታ ማሳድግ የጀነት መግቢያ መንገድ ነው፡፡ 2⃣2⃣ ከእናቶች እግር ሥር አትነሱ፡፡ ጀነት በእግራቸው ሥር ነውና፡፡ 2⃣3⃣. እናት ከአባት በሦስት ደረጃዎች የበለጠች ናት፡፡ አል-ዐሪፊ እንደፃፉት… ራሳችሁ በድላችሁ፣ መብቶቻቸውን ሰርቃችሁ እስልምና ሴቶችን ይበድላል አትበሉ።💞💞💞
Show all...
👍 1