Joseph Math Tutor
Open in Telegram
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
Show more1 855
Subscribers
+124 hours
+87 days
+3430 days
Posts Archive
1 855
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የመምህርነት ሙያን መቀላቀል ለሚፈልጉ የአንድ ዓመት ስልጠና ሊሰጥ ነው፡፡
ስልጠናው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በተመረጡ አምስት ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል፡፡
የምዝገባ መስፈርት፦
በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች እና ተዛማጅነት ባላቸው የትምህርት መስኮች በመምህርነት ሙያ መሰልጠን የሚፈልጉ
የምዝገባ ጊዜ
ከዛሬ ህዳር 16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት
የምዝገባ ቦታ
ከስር በተገለፁ በተመረጡ አምስት ዩኒቨርሲቲዎች በኦንላይን
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጡ የትምህርት አይነቶችና ተዛማጅ የትምህርት መስኮችን ዝርዝር ለማግኘት https://shorturl.at/N8e0s ላይ በመግባት “አማራጭ የመምህራን ስልጠና ትምህርት አይነቶች” የሚለውን በማውረድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የዩኒቨርሲቲ መመዝገቢያ ሊንኮች፦
➫ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፦ https://forms.gle/JZG12devyUvDe3v6
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፦ https://docs.google.com/.../1FAIpQLSfQcnu1ThO.../viewform...
➫ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፦ https://portal.hu.edu.et/Home/AvailablePrograms
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፦ https://portal.ju.edu.et
➫ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፦ https://forms.gle/6t1BNV9S67oXwzBv9
የስልጠና ፕሮግራሙ በአንድ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን፤ በቀን መርሐግብር የሚማሩ ተማሪዎች የትምህርት ወጪያቸው ሙሉ ለሙሉ በመንግሥት እንደሚሸፈን ተገልጿል።
©️ tikvahuniversity
1 855
የማርበርግ ቫይረስ በሳይንስ የተረጋገጠ መድሐኒት ባይኖረውም፣ በሌሎች አገራት ተሞክሮ ጥሩ ውጤት ያሳዩ መድሐኒቶች ሀገር ውስጥ እየገቡ መሆኑ ተገለጸ‼️
የማርበርግ ቫይረስ በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ ከተከሰተበት ጀምሮ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 10 የደረሰ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በዚሁ በሽታ የ5 ሠዎች ህይወት አልፏል።
መናኸሪያ ሬዲዮ ያነጋገራቸው በጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ አማካሪ እንዲሁም የድንገተኛ እና ፅኑ ህክምና ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ወልደሰንበት ዋጋነው፣ በሽታው በቫይረስ የሚዛመት እና ከኢቦላ ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው አስታውቀዋል።
ቫይረሱ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር ግንኙነት እንደሌለው ገልጸው፣ ከሌሎች ቫይረሶች በተለየ መልኩ በፍጥነት ምልክት እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
ቫይረሱ በሽታ የመቋቋም አቅምን የሚያዳክም እንዲሁም ያለ ምክንያት የሰውነት መድማት የሚያስከትል መሆኑን ገልጸው፣ እስካሁን በሳይንስ የተረጋገጠ መድሐኒት ባይኖረውም በአፍሪካ እና በሌሎችም ሀገራት ጥቅም ላይ ውለው ለውጥ ያሳዩ መድሀኒቶች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በሙከራ ላይ ያሉ ክትባቶች መኖራቸውን አስታውቀዋል።
በበሽታው የተያዘ ታማሚ ሙሉ ለሙሉ እገዛ የሚፈልግ በመሆኑ እገዛ ከተደረገለት፣ ከሞት የመትረፍ እድል እንዳለው የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማንሳት ያብራራሉ።
ዶክተር ወልደሰንበት ቫይረሱ በወንድ ዘር ፈሳሽ እና በአይን ውስጥ ብቻ እስከ 1 ዓመት መቆየት እንደሚችል ገልጸዋል። በእነዚህ የሰውነት ክፍሎች በሽታ የመከላከል አቅም ዝቅተኛ በመሆኑ ቫይረሱ የመቆየት እድል እንዳለው ነው ያብራሩት።
በደም እና የአይን ብሌን ልገሳ አማካኝነትም እንደሚተላለፍ አስታውቀዋል።
በአእዋፋት እና በሰዎች እንቅስቃሴ አማካይነት በድንበሮች አካባቢ በስፋት እንደሚሰራጭ ያስታወቁት ባለሙያው፤ በተጠናከረ ሁኔታ ቁጥጥር ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
ከዚህ በኃላም የሚከሰቱ ቫይረሶች ሊኖሩ እንደሚችሉ ስጋታቸውን በመግለጽ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል።
1 855
Repost from JOSEPH MATH TUTORIAL CHANNEL
Course:- Applied Mathematics III
Topic:- Laplace Transform and Its Applications
Prepared By:- Joseph Math Tutorial
ASTU
1 855
Repost from JOSEPH MATH TUTORIAL CHANNEL
+1
Last year Applied Math III worksheet III
(Laplace Transform)
1 855
+1
⚠️WARNING⚠️
Please don't click these links
People's telegram accounts are being hacked. The hackers are spamming with fake links to every contact and groups and they're messing wit their personal informations like bank accounts so please be aware and share this to your friends and families!!!
1 855
እኔ ካወጣሁላችሁ ፈተና 2 ጥያቄ direct መጥቷል ብዙ ጥያቄ በተዘዋዋሪ መጥቷል።
በደንብ እንደሰራችሁት ተስፋ አለኝ በርቱ።👍
1 855
⚠️ Security Alert
Enhance the security of your account: Many Telegram accounts have been compromised. Ensure that you enable two-step verification for added protection.
1 855
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ በ2019 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
ለመምህራን የሚቀርበው ጥቅማጥቅምና ደመወዝ በቂ አለመሆን ለመምህራን እጥራት ምክንያት እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ይህም አዲስ መምህራንን በበቂ ሁኔታ ለማፍራት አስቸጋሪ እንዳረገው ገልፀዋል።
የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ግለሰቦች የአንድ ዓመት የማስተማር ዘዴ (Pedagogy) ኮርስ በመውሰድ ለመምህርነት ብቁ መሆን እንደሚችሉ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በዚህም የመምህራንን ቁጥር ለማሳደግ ይቻላል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ሲሰጡ፣ የበለጠ የመምህነነት ሙያ ፍቅር ሊያጎለብቱ እንደሚችሉም ገልፀዋል።
ባለፈው ዓመት ከቅድመ-መዋዕለ ህጻናት እስከ 12ኛ ክፍል በሀገሪቱ አጠቃላይ የመምህራን ቁጥር 625,000 የነበረ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ቁጥሩን ወደ 700,000 ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። #Fortune
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
