✟ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የንጽጽር ቻናል
ይህ የተከፈተው ገጽ በአንድ ሀጢያተኛ ባርያ ሲሆን ባለችን አጭር ጊዜ እንኳን ሰው ወደ እግዚአብሔር በንስሀ እንዲመለስ ለማድረግ ነው።በዚህ ገጽ የሚቀርቡት➤ ➤የኢ/አ/ብርሀን መልእክቶች ። ➤>>>>>>>>>ቤተሰብ ምስክርነት ። ➤>>>>>>>>>ትምህርቶች ። ➤አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች መልእክቶች ናቸው።
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት 5 ገፅ 17
ጸሎተ አባ ጊዮርጊስ ዘሰብዐቱ ጊዜያት _ የሰባቱ(፯ቱ) ጊዜያት የአባ ጊዮርጊስ ጸሎት በጠዋት የሚጸለይ የእመቤታችን ሰላምታ (ሰላመ ማርያም ዘነግህ) የአፍሽ መዐዛ እንኮይ የሆነ በበረሃና በዱር የምትሸቺ ድንግል ማርያም ሆይ ሰላምታ ይገባሻል ፣ በመከራዬ ጊዜ ረዳቴና ጋሻዬ ነሽና ሰላም እልሻለሁ። መመኪያዬ እመቤቴ ሆይ ያለአንች ሌላ ተስፋ የማደርገው ዘመድ የለኝምና ባለመናቅ "በገንዘቤ የገዛሁህ አገልጋዬ ወዳጄ" ትይኝ ዘንድ ሰላም እልሻለሁ። ለሐና ዕንቋ የምትሆኚ የሰሎሞን ዙፋኑ እመቤቴ ሆይ ሰማንያ ዕቁባትና ስልሳ ነገሥታት እያገለገሉ አመስግነዉሻልና ሰላምታ ይገባሻል። በኋላ ዘመን እናት የወለደቻትን ልጅ በማታድንበት የፋዳና የበቀል ዕለት በሚሆንበት ጊዜ ከሞት ዕዳ ታድኚኝ ዘንድ ሰላም እልሻለሁ። እንደልማድሽ ሁሉን ወደሚችለዉ ልጅሽ እንዲህ በይ፦ "የማትበቀይ ርኅሩኅ ሆይ፡ ሣይ የሳለዉን ሥዕል…