cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Liju negn

Ye hawariat lijoch

Show more
Advertising posts
237
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

እውነት ከቶ ማን አሰበ ይህን?? የእግዚአብሔር ታምራት በብዙ ነገር ወደፊት ይቀጥላል ኢሳይያስ 51፥2፦ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤ አንድ ብቻውን በሆነ ጊዜ ጠራሁት፥ ባረክሁትም አበዛሁትም። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH የመወያያ ግሩፕ፦@marantawoch
Show all...
👉የእምነት አባቶቻችን የጌታ ደቀመዛሙርት ህይወታቸው እንዴት አለፈ? 1.❤️ማርቆስ:- እስኪሞት ድረስ በአሌክሳንድርያ ግብፅ ጎዳናዎች በፈረስ ታስሮ እየተጎተተ ህይወቱ አልፋለች 2.❤️ሉቃስ:- በግሪክ ሰቅለውት ህይወቱ አልፋለች 3.❤️ማቲዎስ:-በቆንጨራ ተቆርጦ ሞቷል 4.❤️ዮሐንስ:- በፈላ ዘይት ውስጥ ተቀቅሎ ህይወት አለፏል 5.❤️ጴጥሮስ:-ተዘቅዝቆ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞቷል 6.❤️ቶማስ:- በህንድ በጦር ተወግቶ መስዋእት ሆኗል 7.❤️ጳውሎስ:-በአሰቃቂ ሁኔታ ተገርፎ አንገቱ ተቆርጦ ህይወቱ አልፏል 8.❤️ስምዖን:-ግማሽ ለግማሽ ተቆርጦ ነው የሞተው 9.❤️ማቲያስ:-በድንጋይ ተወግሮና አንገቱ ተቆርጦ 10.❤️እንድርያስ:-በስቅላት ህይወቱ አልፏል 11.❤️ያዕቆብ:-በእየሩሳሎም አደባባይ አንገቱ ተቆርጦ የሞተ 12.❤️በርተለሚዎስ:-በግርፋት ህይወቱ አልፏል ሁሉም መልካሙን ገድል ተጋደሉ ክርስቶስን ካዱ ሲባል አይሆንም ብለው አንገታቸውን ለካራ ሰውነታቸውን በዘይት ለመቀቀል ለግርፋት ለስቅላት አሷልፈው ሰጡ።እርስዎስ በአሁኑ ሰዓት ስለምን እያማረሩ ይሆን?በላይ ያለው ክብር ይበልጣል።ይኸኛው አላፊ ጠፊ ነው። "፤ በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ። " (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9: 23) @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
Show all...
“እነዚያም... እግዚአብሔርን ደስ አያሰኙም...” 1ኛ ተሰ 2፥15       🔘 በእግዚአብሔር  ፊት አምልኮ ማስቀረትን።       🔘 ቤተክርስቲያን አርፍዶ መምጣትን            🔘 አንካሳ መስዋዕት ማቅረብን       🔘 መንፈሳዊ ጉባኤዎችን መተው(መቅረት)       🔘 መጽሐፍ ቅዱስን ሳያነቡ መዋልና ማደርን       🔘 በእግዚአብሔር ቃል ጊዜ ወጣ ገባ              ማለትን       🔘 እኔነትን       🔘 አምልኮ ሳያበቃ መውጣትን       🔘 በወንድሞች መሀል ጠብን መዝራትን       🔘 ከመጠን ያለፈ ኑሮ መፈለግን       🔘 ከማያምን ጋር በማይመች አካሄድ መጠመድን       🔘 የሰውን ምስጢር መግለጥን       🔘 ትዳርን መፍታትና መደረብን       🔘 እግዚአብሔር የቀባውን መዳሰስን       🔘 ከልብ ያልሆነ አገልግሎትን       🔘 ዘረኝነትን      🔘 መንፈሳዊ ያልሆነ ጨዋታን      🔘 ሃሰተኛ ሚዛን (መስፈሪያ )      እኛ ግን  እርሱን ደስ ለማሰኘት እንትጋ!!! @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH Discussion Group👉 @Marantawoch
Show all...
የማለዳ ትምህርት /183/ ቀን 20/07/15 ዓ/ም ርዕሽ፦ ቃልኪዳኑን እያሰብን ዘወትር እንፀልይ! ውድ የማራናታ ተለግራም ቤተሰቦች እና የማለዳ ትምህርት ተከታዮች እንደምን አደራችሁ? በጽድቃችን ሳይሆን በምህረቱ በሥራችን ሳይሆን በቸርነቱ ለዛሬ ያደረሰን አምላክ ከልቤ እያመሰገንኩኝ ለዛሬ ትምህርታችን እሻገራለሁ። የዛሬ ትምህርታችን ርዕስ "ቃልክዳኑን እያሰብን ዘወትር እንጸልይ" የሚል ነውና ምናልባት ከዚህ በፊት ሳንጸልይ ያሳለፍናቸውን ቀናቶች ይቅር በለን እያልን እናምብብ የእግዚአብሔር ቃል መፅሐፍ ቅዱስ በዚህ በመጨረሻው ቀን ውስጥ ያለነውን ቅዱሳን ምን ብላችሁ ፀልዩ (ለምኑ) እንደምለን ታውቃላችሁ? በኋለኛው ዝናብ ጊዜ 👉ከእግዚአብሔር ዘንድ #ዝናቡን_ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል፤ እርሱም የበልግ ዝናብን #ለእያንዳንዱም በሜዳ ውስጥ ሣርን ይሰጣል። አሜን ትንቢተ ዘካርያስ 10 : 1 ይህ የኋለኛው ዝናብ ጊዜ ነው። አሁን 👉ከእርሱ ዘንድ #ዝናቡን_እንለምን። እርሱም መብረቅን ያደርጋል። ጌታ በቃሉ ታማኝ ነውና በእርግጥ ያደርገዋል። እንዲህ ያለው:- #በዚያ_ወራት_በወንዶችና_በሴቶች_ባሪያዎች_ላይ_መንፈሴን_አፈስሳለሁ፤ አሜን የእኛ ጌታ በላይ በላይ አፍስስብን! ትንቢተ ኢዮኤል 2 : 29 ከበዓሉም በታላቁ #በኋለኛው_ቀን ኢየሱስ ቆሞ። ማንም የተጠማ ቢኖር 👉ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። 👉በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ። ዮሐ.7:37,38 ይህ ነው ፀሎታችን! የነፍስ ጥማታችን! እኛ👇👇👇👇👇👇👇 👉ከአንዱ በቀር አምላክ እንደሌለ የምናውቅ፣ 1ቆሮ.8:4 👉በልጁም ሞት፣ መቀበርና ትንሣኤ፣ የምናምን ሮሜ 5:8-10 1ቆሮ.15:1-4 👉ከሞተ ስራችን ንሰሐ የገባን፣ ሐዋ.2:38 ዕብ.6:1 👉ለኃጢአታችን ስርየትም በኢየሱስ ስም ተጠምቀን ክርስቶስን የለበስን፣ ሐዋ.2:38 ገላ.3:27 👉በቅድስናው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ የታደስን፣ ትቶ 3:5 👉በሕያው እግዚአብሔር ቤት፣ በቤተክርስቲያን 🕎፣ በአንድ አካል የምንኖር፣ ሐዋርያዊ ትውልድ ነን ( These Days Apostolic Generation) /1ጢሞ.3:15 ሮሜ 12:4,5/ ይህም ጊዜ ለእኛ የምርኮ ጊዜ ነው። የመውረስ ዘመናችን ነው። #ቃልኪዳኑ_ይፈፀማል! እንዲህ ተብሎ የተገባው:- በመጨረሻውም ዘመን የእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ #ጸንቶ ይቆማል፥ ከኮረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፤ አሕዛብም ወደ እርሱ ይጐርፋሉ። ከጽዮን ሕግ፥ ከኢየሩሳሌምም የእግዚአብሔር ቃል #ይወጣልና ብዙዎች አሕዛብ ሄደው። ኑ፥ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፥ ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንውጣ፤ እርሱም መንገዱን #ያስተምረናል፥ #በፍለጋውም_እንሄዳለን ይላሉ። ሃሌሉያህ!!! ትንቢተ ሚክያስ 4 : 1 - 2 ትንቢታዊ ቃሉን እያሰብን ዘወትር እንፀልይ! የእምነት ቃሉን የሰጠው እስከ ፍፃሜው ታማኝ ነው! ተባረኩ የጌታ ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን! 🤷‍♀🤷‍♂በጸሎት ወጥታችሁ በምስጋና ግቡ🤷‍♂🤷‍♀ 🌺 የማለዳ ትምህርት በየማለዳ 🌺 🌸🌼 የውሎአችን ስንቅ ከማራናታ🌸🌼 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH የመወያያ ግሩፕ @marantawoch Comment @Taddyapostolic & @Uwillnverwalkalone
Show all...
የማለዳ ትምህርት /184/ , ቀን 21/07/15 ዓ/ም (ሐሙስ) ....እንግዲህ እንንቃ!! በጌታችንና በመድኀንታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተወደዳችሁ ውድ ቅዱሳን ወንድሞችና እህቶችእንዲሁም የማራናታ ተለግራም ቻናል ቤተሰቦች እና የማለዳ ትምህርት ተከታዮች በሙሉ እንደምን አደራችሁ እያልኩኝ ለዛሬ ቀን ስንቃችን ይሆናል ብሎ እግዚአብሔር በልቤ ያመጣውን #የማንቂያ_ደውል_ትምህርት ላካፍላችሁ ወደድኩኝ። ከላይ በርዕሱ ላይ እንዳያችሁት ..... እንግድህ እንንቃ ማለት የማነቂያ ደውል ትምህርት እንደምሆን እንገምታለን። እያየን ካለመመልከት፤ እየሰማን ካለማዳመጥ፤ እያወቅን ካለማስተዋል፤ እንቆጠብ የጌታ መምጫ ቀርባለች። ብዙ ጊዜ በቤተክርስቲያን ውስጥ #ኢየሱስ_ሊመጣ_ነው_እንዘጋጅ በሚል ትምህርት ብዙ የእግዚአብሔር ሰወች፤ መስካሪዎች አስተምሮንና መክሮን ይሆናል። ነገር ግን ከእኔም ጭምር፦ ☞ ስንቶቻችን ተዘጋጅተናል? ☞ በመቅረዛችን ውስጥ ዛይት ለስንቶቻችን ሞልቷል? ☞ ኢየሱስ ዛሬ ብመጣስ የት ነን? እስክ እናስብ....... ወገን እንንቃ ሙሽራው ሲመጣ ሙሽሪት አንቀላፍታ ብትጠብቅ ሙሽራው መሄዱ ግድ ስለሆነበት አንቀላፍታ የጠበቀች ሙሽሪት ስለማትጠቅመው ጥሎአት ይሄዳል። ሰይረፍድ እንመለስ ጌታ በደጃችን ነውና ለመሄድ እንዘጋጅ። ይሄ ማንቂያ ደውል ለሁላችሁም ነው ምን አልባት ጌታ ስለዘገየ መምጣቱ ይቀራል ማለት አይደለም ቢዘገይም መምጣቱ አይቀርም። ስለዚህ በንቃት ጌታን መጠበቅ አለብን። በአሁን ግዜ ጌታን በንቃት መጠበቅ ያለፈ ፋሽን ይመስል ክርስቲያን ሆነን የምናስበው የምናልመው የምንጠብቀው የአለም ነገር ብቻ ሆኖአል አብዛኞቻችን ስለ ጌታ መምጫ ማሰብ አቁመናል ብናስተውል እንደውም ስለ ጌታ መምጣት ማሰብ ያለብን አሁን ነው ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በመጨረሻው ግዜ ይፈጸማሉ ወይም ይሆናሉ ካላቸው ነገሮች የቀረ ምንም የለም። (ወደ ዕብራውያን ምዕ. 10) - 35፤ እንግዲህ ታላቅ ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ። 36፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና። 37፤ ገና በጣም ጥቂት ጊዜ ነው፥ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም፤ 38፤ ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም። 39፤ እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም። ደግሞም፦ 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት ምዕ. 3) 8፤ እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ። 9፤ ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። 10፤ የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል፤ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፥ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይቀልጣል፥ ምድርም በእርስዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል። ብንመለከት ብናዳምጥ እና ብናስተውል አሁን ይሆናል ከተባለው ትንቢት የቀረ የምለው የጌታ መምጫ ብቻ ነው ስለዚህ: ወጣት ሆይ የስም ብቻ ክርስትና ይብቃ ከዚህ ሰዓት አንስቶ እስከ መምጫው ድረስ ክርስትናን መኖር ጀምር አራዳ ምናምን ይሄ ዘመን በመጣው ቋንቋ አትሸወድ ለአንተም ለኔም ላንቺም ከአሁን ቦኃላ የሚበጀው ለእግዚአብሔር እንደሚገባ በመኖር የሙሽራውን መምጫ መጠበቅ ነው። ይህን ቃል ሁሌም አስብ " ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።" (የማቴዎስ ወንጌል 24:42) 🤷‍♂🤷‍♀በጸሎት ወጥታችሁ በምስጋና ግቡ🤷‍♂🤷‍♀ 🌼የማለዳ ትምህርት በየማለዳ🌼 🌻የውሎአችን ስንቅ ከማራናታ🌻 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH Discussion group @marantawoch በinbox ማናገር ከፈለጉ @Taddyapostolic &
Show all...
በዘንድሮ ዋራ ቤቴል ጉባኤ በሁላችን ልብ የማይረሳ ትዝታ የጣለልን አምልኮ መዝሙር ተጋበዙልን! ታ ታኔ ታራቲ... "አሁን የእኔ ተራ ነው" 1, ሔሬ ቃራማያ ላንሻዋ እኬ ሔራያ ማንቹ አንጋ ዮራን ዶጎቴ ኬሻያ ሔሽ ዬ ሔራያ ጣቴ እክቴወኤ አኔን ቶዋንታይት ያናያ ዳጌወኤ 4* ጣቴ አኔ ታራት 2* ድዌ ታጋ ጋራት ጣቴ አኔ ታራት 2* ካአቴ ያናያት ጣቴ አኔ ታራት 2* ድዌ ታጋ ጋራት ጣቴ አኔ ታራት 2* ፋርሳቴ ያናያት 2, ጣቴ ኮን ካአ ኡንፋና ድሔሬሞ ባርያ እሌና ወማ ማንቾ እኮሞ ዶጎቴ ቃጨራ ቃራማ ጋቴወኤ ላላቴይ ሻኖክሁ አኔን ቶዋቴወኤ 4* 3, ሳአወሐ ህጋወሐ ሳንተ ሁጭራ ጋቴወ ህንድዶ ሁርባጣይ ሔራያ ጣ እክተወ ባሩ ባኤወኤሁራ የሱስ ዳዬ እሌወኤ ሔጦ ሙ'ዶሞሐ ሔሬና ቶዋቴወኤ 4* 4, ቃሩ አናያ ኬሽሁ ድርያ ዳ ጌያት ማኑይ ማኔ እኩሞሁ ጮዬያ ላና ጌያት ድርያ ዳይ ባራ ቃራያ ሀውሞ ራባያ ህጋና እሌያይ ላኡሞ 4* 5, ሀዳ ባሩ ዳይሮ ሀንሴ ወሽናይዌ ሾሌ ሔራወሁራ አይርኜ ኡይናይዌ ጣቴ እክቴወኤ ቶዋኞ ሆጉሞ ሳቴ አይኖ ድሆላወኤ ያናያ ቶዋኞይቴ 4* @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH የመወያያ ግሩፕ፦@Marantawoch
Show all...
👄አንደበት ✍✍አንደበታችንን እንጠብቅ 🗣ያዕቆብ 3:5 እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል። 🗣6፤ አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል 🗣34፤ እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ክፉዎች ስትሆኑ መልካም ለመናገር እንዴት ትችላላችሁ? በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና። 🗣35፤ መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል። " አንደበትህ ኃጢአትን ያስባል፤ እንደ ተሳለ ምላጭ ሽንገላን አደረግህ።" 🗣መዝሙረ ዳዊት 52:2 " አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።" ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤"የያዕቆብ መልእክት 1:19) " 👉👉👉ስለዚ ስንዋደድ ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና 🗣በአንደበት አንዋደድ።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3:18) @MARANATHAWOCH D..G @marantawoch
Show all...
ከአድሱ አልበም የተወሰደ ከወንድም ዳዊት ያቼስ Kiristoos hunda (Qolass. 3:11) Kiristoosi hundaa inni waaqa guddaa Hidhaansa cubbu’uu isatti xare nurraa 2x Abbaalleen kiristoos keessa jiraa Hafuurrilleen kiristoos keessa jiraa Fayyinnilleen kiristoos keessa jiraa Nageennilleen kirsitoos keessa jiraa 2x 1.Nama uumee waaqi addee dansaa kaayee Diinni dogoggorsee achi keessaa baasee Karaa isaan deebisuun waaqi itti yaadee Jechafii foon godhee cubbuu haaloo baasee Inni waaqaa kiristoos waaqa guddaa Gooftaa,waaqaa inni ta’aa woma hundaa Uffate wayaa haaloo ka cubbuu namaa ittiin shigiduu Isa malee waaqi nama uume hin jiruu 2x 2.Waaqa yoo barbaadde iyyesuus waaqii Jecha waaqaa keessaa hubantiin ilaalii Durii fi ammallee isa qofa waaqii Icciitiin fayyinaa ifte warra isaatii Namaaf yaadee ka mataa ifii salphisee Inni waaqaa ka saba ifii fayyisee Maqaasaatiin cuuphante jennaan fayyitee Du’a keessaa gara jireennaa darbitee 2x 3.Si’iin hin jalqabnee cuuphami isaanii Ka biraa hin barbaadiin iyyesuus waaqii Kaayyoon cuuphansaatuu fayyina lubbuutii Kiristoos uffattaa cuuphami hagaanii Dafii koottu cuuphami yesuus jedhaa Itti hin beellamin hin beettu waan bor te’aa Lafaan gubbatti samaayii tanaan jalatti Maqaan fayyinaa hin jiru yesuusiin achii @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH የመወያያ ግሩፕ፦@marantawoch
Show all...
Repost from Truth Media
ለማመስገን በቂ ነው መዳኔ! እህታችን ጌታ ኢየሱስ ጸጋ ላይ ጸጋን ይደርብልሽ! May God bless you!!
Show all...