cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹

إِنَّمَا يَخْشَى اللَّهَ مِنْ عِبَادِهِ الْعُلَمَاءُ ۗ إِنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ غَفُورٌ አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው፡፡ አላህ አሸናፊ መሓሪ ነው፡፡ (📗Al Qura'an 35:28) https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0

Show more
Advertising posts
198Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የመካ ሙሽ -ሪኮች የአላህን ፈጣሪነት አልካዱም! ~ ነቢዩ  የተላኩባቸው እነዚያ ሙሽ -ሪኮች #አብዛኞቹ የሰማይ፣ የምድር ፈጣሪ አላህ እንደሆነ፣ የሁሉ ነገር ስልጣኑ በእጁ እንደሆነ፣ ዝናብ የሚሰጠው አላህ እንደሆነ ያምኑ ነበር። እነዚህ ባዶ ሙግቶች ሳይሆኑ የተረጋገጡ ሐቆች ናቸው። ቁርኣን ውስጥ ከሚገኙ በርካታ መረጃዎች ውስጥ #ጥቂቱን ብቻ ልጥቀስ። 1.  قُل لِّمَنِ ٱلۡأَرۡضُ وَمَن فِيهَآ إِن كُنتُمۡ تَعۡلَمُونَ ٨٤ سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ ٨ټ قُلۡ مَن رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ ٱلسَّبۡعِ وَرَبُّ ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡعَظِيمِ ٨ٌ سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ أَفَلَا تَتَّقُونَ ٨٧ قُلۡ مَنۢ بِيَدِهِۦ مَلَكُوتُ كُلِّ شَيۡءٖ وَهُوَ يُجِيرُ وَلَا يُجَارُ عَلَيۡهِ إِن كُنتُمۡ تَعۡلَمُونَ ٨٨ سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ فَأَنَّىٰ تُسۡحَرُونَ ٨ي {“ምድርና በውስጧ ያለው ሁሉ የማን ነው የምታውቁ ከሆናችሁ?” በላቸው። “በርግጥ የአላህ” ይላሉ። “ታዲያ አትገሰፁምን?” በላቸው። “የሰባቱ ሰማያት ጌታና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን ነው?” በላቸው። “በርግጥ አላህ ነው” ይላሉ። “እንግዲያው አትፈሩትምን?” በላቸው። “የሁሉ ነገር ስልጣኑ በእጁ የሆነው እሱ የሚጠብቅ በሱ ላይ የማይጠበቅ (የሆነው) ማን ነው? የምታውቁስ ከሆናችሁ?” በላቸው። “(ሁሉም) ለአላህ ነው” ይላሉ። “ታዲያ እንዴት ትታለላላችሁ?” በላቸው።} [ሙእሚኑን፡ 84-89] 2.  وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَسَخَّرَ ٱلشَّمۡسَ وَٱلۡقَمَرَ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۖ} ... {وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّن نَّزَّلَ مِنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ فَأَحۡيَا بِهِ ٱلۡأَرۡضَ مِنۢ بَعۡدِ مَوۡتِهَا لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۚ} {ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ፀሐይንና ጨረቃንም የገራ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ “አላህ ነው” ይላሉ።} {ከሰማይም ውሃን ያወረደና በሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ህያው ያደረጋት ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በርግጥም “አላህ ነው” ይላሉ።} [ዐንከቡት፡ 61፣ 63] 3.   {وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ لَيَقُولُنَّ خَلَقَهُنَّ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡعَلِيمُ} {ሰማያትንና ምድርን ማን እንደፈጠረ ብትጠይቃቸውም በእርግጥ “አሸናፊውና አዋቂው (አላህ) ነው የፈጠራቸው” ይላሉ።} [ዙኽሩፍ፡ 9] 4.   {وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَهُمۡ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۖ } {ማን እንደፈጠራቸው ብትጠይቃቸውም “በእርግጥ አላህ ነው” ይላሉ።} [ዙኽሩፍ፡ 87] እንዲያውም የመካ ጣኦታውያን ለአላህ አምልኮትም ይፈፅሙ ነበር። እርድና ሐጅን በምሳሌነት መውሰድ ይቻላል። ከዚህም አልፎ ጣኦታውያኑ ጣኦቶቻቸው ከአላህ በታች እንደሆኑ ያውቁ ነበር። በማስረጃ ነው የማወራው። 1.  {وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ} {እነዚያም ከርሱ ሌላ ረዳቶችን የያዙት “ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቀርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቸውም” (ይላሉ።)} [ዙመር፡ 3] 2.  {وَيَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمۡ وَلَا يَنفَعُهُمۡ وَيَقُولُونَ هَٰٓؤُلَآءِ شُفَعَٰٓؤُنَا عِندَ ٱللَّهِۚ} {ከአላህም ሌላ የማይጎዳቸውን እና የማይጠቅማቸውን ያመልካሉ። “እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው” ይላሉም።} [ዩኑስ፡ 18] ልብ በሉ! ወደ አላህ ለመቃረብ ነው ጣኦቶችን የሚያመልኩት እያለን ነው። ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ እንዲህ ይላሉ፡- كَانَ الْمُشْرِكُونَ يَقُولُونَ: لَبَّيْكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، قَالَ: فَيَقُولُ رَسُولُ اللهِ : «وَيْلَكُمْ، قَدْ قَدْ» فَيَقُولُونَ: إِلَّا شَرِيكًا هُوَ لَكَ، تَمْلِكُهُ وَمَا مَلَكَ، يَقُولُونَ هَذَا وَهُمْ يَطُوفُونَ بِالْبَيْتِ “አጋሪዎቹ 'ለበይከ ለአንተ ተጋሪ የለህም' ይሉ ነበር። ይህን ሲሉ የአላህ መልእክተኛ  {ወዮላችሁ በቃ በቃ!} ይሏቸው ነበር። እነሱ ግን 'የምትቆጣጠረው የማይቆጣጠርህ ላንተ የሆነ ተጋሪ ቢሆን እንጂ' ይላሉ። ይህን የሚሉት ከዕባን እየዞሩ (ጠዋፍ ሲያደርጉ) ነው።” [ሙስሊም፡ 1185] እንደምታዩት ሰዎቹ በአላህ ፈጣሪነት ያምኑ ነበር። ዒባዳም ለሹ ይፈፅሙ ነበር። እንዲያውም ጣኦቶቻቸው አላህ የሚቆጣጠራቸው ከሱ በታች የሆኑ እንደሆኑ በግልፅ እየተናገሩ ነው። ይሄ ሁሉ መረጃ እያለም “የለም! የመካ አጋሪዎች ከነ ጭራሹ በአላህ አያምኑም ነበር” የሚል አለ። ቢገባችሁ ችግራችሁ ከቁርኣን ጋር ነው። “እና የአላህን ፈጣሪነት የሚያምኑ ከነበሩ እንደ ከሃዲ፣ አጋሪ ያስቆጠራቸው ምን ነበር?” ከተባለ ከምክንያቶቹ ውስጥ #አንዱ ሺርክ ነው። #ሙሽሪኮች ነበሩ። አላህን እንደሚያመልኩት ጣኦቶቻቸውን ያመልካሉ። ለአላህ ሐጅ እንደሚያደርጉት በሐጁ ላይ ጣኦቶቻቸውን ይጠራሉ። “የአላህ ባሪያ” ብለው ስም እንደሚያወጡት “የዑዛ ባሪያ” ብለው ስም ያወጣሉ። በአላህ እንደሚምሉት በጣኦቶቻቸው ይምላሉ። ለአላህ እንደሚያርዱት ለጣኦቶቻቸው ያርዳሉ። አላህን እንደሚወዱት ጣኦቶቻቸውን ይወዳሉ። ... ይሄ ተግባራቸው ነው ከነብዩ  ጋር ያፋጠጣቸው። ይሄ ተግባራቸው ነው ለአላህ ባላንጣ ማድረግ ተብሎ የተወገዘው። {ከሰዎችም ከአላህ ሌላ ባላንጣዎችን የሚይዝ አለ። ልክ አላህን እንደሚወዱት ይወዷቸዋል} የሚለው የጌታችን ቃል ይህን ሀሳብ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። በተመሳሳይ ዛሬም ዒባዳዎችን ለአላህ እንደሚሰጠው ለፍጡሮች የሚሰጥና የሚማፀን ከሆነ የነዚያን ሙሽሪኮች ተግባር ነው የፈፀመው። የዒባዳ ተውሒድ ከሌለ በአላህ ፈጣሪነትና ጌትነት ማመን ብቻውን ሙስሊም አያሰኝም፣ ከእሳትም አያድንም። በመቅሪዚይ (845 ሂ.) ንግግር ፅሁፌን ልቋጭ፡- “ተውሒደ ሩቡቢያ እነዚያ አጋሪዎች ያልካዱበት ለመሆኑ ጥርጥር የለም። ይልቁንም ጥራት ይገባውና እሱ (አላህ) ብቻ የነሱም የሰማያትና የምድርም ፈጣሪ፣ ለአለማቱ ጥቅም ባጠቃላይ የቆመ እንደሆነ ያምኑ ነበር። ይልቅ የተቃወሙት የአምልኮትና የውዴታን ተውሒድ ነው።” [ተጅሪዱ ተውሒዲል ሙፊድ፡ 8] ይሄ እንግዲህ የብዙሃኑ ሙሽሪኮች እምነት ነው። በጊዜው ከነበሩ ከሃዲዎች ውስጥ የተወሰኑ ደህሪዮች ነበሩ፣ በፈጣሪ የማያምኑ። እነዚያን የሚመለከቱ መረጃዎችን ብቻ እየመዘዙ ሌሎችን አንቀፆችን መግፋት እራስን መሸወድ ነው። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ልብ በሉ! እንዲህ የሚንደፋደፉት ለጀይላኒይ ያላቸው የተጋነነ ቦታ እና የጀይላኒይ ብርቱ ፀረ አሽዐሪያ አቋም አልጣጣም ብሎ ስላስቸገራቸው ነው። ከቅርቃሩ መውጫ መንገድ እውነቱን መቀበል ብቻ ነበር። ግን በራሱ ላይ ቆልፎ ስለ ተቀመጠ አካል ምን ማለት ይቻላል?! = (ኢብኑ ሙነወር፣ ሸዋል 16/1444 (ሚያዚያ 28/2015)) የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

አሕ ^ባሽ እና ዐብዱል ቃዲር አልጀይላኒይ (561 ሂ.) ~ ተስፈንጣሪው የአሕ ^ ባሽ አንጃ "አላህ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ነው" የሚሉ ሙስሊሞችን ከኢስላም በማስወጣት (በማ^ ክ^ ፈ^ር) የታወቀ ነው። የቡድኑ ቁንጮዎች በዚህ ፅንፈኛ አቋማቸው የተነሳ እነ ኢማሙ ዳሪሚይን፣ እነ ኢብኑ ኹዘይማን፣ እነ ኢብኑ መንደህን እስከማብጠልጠል ደርሰዋል። ይሄ አጉል የሆነ አካሄዳቸው ግን ሳያስቡት ቅርቃር ውስጥ ሲከታቸው ይታያል። "እናከብራቸዋለን" ከሚሏቸው ዑለማዎች ውስጥ የአላህን ከፍጡራን በላይ መሆን የሚያፀድቁ ያጋጥሟቸዋልና። ጀይላኒይ ረሒመሁላህ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ መሆን ይችላሉ። የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን አንዴ ሳይሆን ደግመው ደጋግመው አስረግጠው ገልፀዋል። ይህንን እውነት የማይቀበሉትን ኮንነዋል። ከዚህም አልፈው አሻዒራን በስም ጠቅሰው አብጠልጥለዋል። ይሄ ለአ^ ሕ^ባሾች ከባድ ራስ ምታት ነው። አይቀበሏቸው እነሱ ዘንድ የማይሆን ነገር ነው። ሌሎችን እንደ - ሚያ* ከ^ ፍሩ እንዳያከ * ፍ- ሯ ^ቸው በሱፊያው ዓለም ያላቸው ቦታ እጅግ የገዘፈ ነው። ሌሎችን በሚያ* ከ^ ፍሩበት ጉዳይ እሳቸውን ሲያልፉ ደግሞ አጭ በርባሪነታቸው ገሃድ ይወጣል። ምን ይሻላል? ሽምጥጥ አድርገው መዋሸትን እንደ ዘዴ መርጠው ነበር። ችግሩ ግን ውሸቱም የነሱን ዝቅጠት ከማጋለጥ ባለፈ የሚፈይድ አለመሆኑ ነው። ቀጥሎ ጀይላኒይ የአላህን ከ0ርሹ በላይ መሆን ያፀደቁባቸውን ንግግሮች እጠቅሳለሁ፦ [1ኛ]:- وأن الله تعالى خلق سموات بعضها فوق بعض، وسبع أرضين بعضها أسفل من بعض، ومن الأرض العليا إلى السماء الدنيا مسيرة خمسمائة عام، وبين كل سماء وسماء مسيرة خمسمائة عم، والماء فوق السماء السابعة، وعرش الرحمن فوق الماء، والله تعالى على العرش “የላቀው አላህ ሰማያትን ከፊሎቹን ከከፊሎቹ በላይ፣ ሰባት ምድሮችን ደግሞ ከፊሎቹን ከከፊሎቹ በታች አድርጎ ፈጥሯል። ከላይኛዋ ምድር እስከ ታችኛዋ ሰማይ ድረስ አምስት መቶ አመት የሚያስኬድ ርቀት አለ። ከእያንዳንዱ ሰማይ እስከ ቀጣዩ ሰማይ ድረስ እንዲሁ የአምስት መቶ አመት ጉዞ ርቀት አለ። ውሃው ከሰባተኛው ሰማይ በላይ ሲሆን የአረሕማን ዐርሽ ከውሃው በላይ ነው። ከፍ ያለው አላህ በዐርሹ ላይ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/123] [2ኛ]:- وَهُوَ بِجِهَةِ العُلُوِّ، مُسْتَو عَلَى العَرْشِ، ... واللهُ تَعَالَى عَلَى العَرْشِ وَلاَ يَخْلُو منْ عِلْمِهِ مكانٌ، وَلاَ يجوزُ وصفهُ بأنَّهُ فِي كلِّ مكانٍ، بلْ يقالُ: إنَّهُ فِي السَّمَاءِ عَلَى العَرْشِ “እርሱ በላይ አቅጣጫ ከዐርሹ በላይ ከፍ ብሎ ነው። … የላቀው አላህ በዐርሹ ላይ ነው። ከእውቀቱ የሚራቆት ቦታ የለም። ‘እርሱ ሁሉም ቦታ ነው’ ብሎ መግለፅ አይፈቀድም። ይልቁንም እርሱ በሰማይ በዐርሹ ላይ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/121] [3ኛ]:- وهو باين من خلقه، لا يخلو من علمه مكان، ولا يجوز وصفه بأنه في كل مكان، بل يقال: إنه في السماء على العرش “እርሱ ከፍጡሩ ተለይቶ ነው ያለው። ከእውቀቱ የቱም ቦታ አይራቆትም። ‘በሁሉም ቦታ ነው’ ብሎ እሱን መግለፅ አይፈቀድም። ይልቁንም በሰማይ በዐርሹ ላይ ነው ይባላል።” ይህን ካሉ በኋላ የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎችን ዘርዝረዋል። አለፍ ብለውም “የኢስቲዋእን መገለጫ ያለ ‘ተእዊል’ (ቁልመማ) በዐርሹ ላይ ከፍ ማለት ነው ብሎ ያለ ገደብ መረዳት ይገባል” ካሉ በኋላ ከርራሚያ፣ #አሽዐሪያና ሙዕተዚላን ከነ ተሳሳተው ትርጓሜያቸው ጋር በስም ጠቅሰው አውግዘዋል። [አልጉንያ፡ 1/124] [4ኛ]:- كَوْنُهُ عزَّ وجلَّ عَلَى العَرْشِ مذكورٌ فِي كلِّ كتابٍ أُنزلَ عَلَى كلِّ نبيٍّ أُرسلَ بلا كَيْفٍ “አሸናፊውና የላቀው - ያለ አኳኋን - በዐርሹ ላይ መሆኑ በሁሉም የተላከ ነብይ ላይ በተወረደ መፅሐፍ ውስጥ ሁሉ ተጠቅሷል።” [አልጉንያ፡ 1/125] [5ኛ]:- وأنه تعالى ينزل في كل ليلة إلى سماء الدنيا، كيف شاء وكما شاء، فيغفر لمن أذنب وأخطأ وأجرم وعصى لمن يختار من عباده ويشاء، ... لا بمعنى نزول رحمته وثوابه على ما ادعته المعتزلة والأشعرية “የላቀው (አላህ) በየሌሊቱ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ በሚሻው ሁኔታ፣ እንደ መሻቱ ይወርዳል። ሃጢአት ለፈፀመ፣ ለተሳሳተ፣ ለወነጀለ፣ ላመፀ ይምራል፤ ከባሮቹ ለመረጠውና ለፈለገው። እንጂ ሙዕተዚላና #አሽዐሪያ እንደሞገቱት የእዝነቱና የምንዳው መውረድ አይደለም።” [አልጉንያ፡ 1/125] በጀይላኒይ ላይ ወሰን በማለፍ ለሚታወቁት በርካታ ሱፊዮች ይሄ እጅግ አስደንጋጭ ነገር ነው። በቁርኣንና በሐዲሥ ላይ እንደለመዱት አይቆለምሙት፣ አይመችም። ጭራሽ “አሽዐሪያ” እያሉ በስም ጠርተው ነው ደጋግመው ያብጠለጠሏቸው። ምን ይሻላል? ቢጨንቃቸው ሁለት ዓይነት ማምለጫዎችን ዘይደዋል። [ማምለጫ አንድ]፦ አንዳንዶቹ: “ሌሎች ሰዎች በኪታባቸው ውስጥ አስገብተውባቸው እንጂ እሳቸው ይህን አላሉም” በማለት አይናቸውን በጨው አጥበው የተከራከሩ አሉ። ለምሳሌ ሀይተሚይ (974 ሂ.)። [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 145] ግና ከሀይተሚይ በፊት ያለፉ ታላላቅ ዑለማዎች - ሱፊዮች ጭምር - ያረጋገጡት ሐቅ በእንዲህ አይነት ድንጋጤ በወለደው ባዶ ሙግት አይፈርስም። ሲጀመር ሀይተሚይ በመሰል ጉዳዮች ላይ ሚዛናዊነት የለውም። እንደ ኢብኑ ዐረቢይ ላሉ አፈንጋጮች እየተሟገተ እነ ኢብኑ ተይሚያን በሃሰት የሚወነጅል ነው። [ማምለጫ ሁለት]፦ "ኋላ ቶብተዋል" የሚል ነጭ ውሸት ነው። ይህንን ካሉት ውስጥ ያፊዒይ (768 ሂ.) ተጠቃሽ ነው። ያፊዒይ ከላይ የተዘረዘሩትን ንግግሮች የጀይላኒይ መሆናቸውን ይመሰክራል። ይሄ ለሀይተሚይ ምላሽ ይሁንልን። ነገር ግን በህይወታቸው መጨረሻ ላይ “ዐቂዳቸውን ቀይረዋል ይላል። “ማስረጃው” አስቂኝ ነው። የጀይላኒይ “አላህ ከዐርሽ በላይ ነው” ብሎ ማመን ለኢብኑ ደቂቀል ዒድ ሲደርስ በጀይላኒይ “አፈንጋጭነት” ይገረማሉ። ጀይላኒይም ይሄ ነገር ሲደርሳቸው በህይታቸው ፍፃሜ ላይ ዐቂዳቸውን ቀየሩ ይላል። ያፊዒይ ይቀጥልና ታሪኩን የነገረኝን ነጅሙዲን አልአስፈሃኒይን አልጠረጥረውም። ምክንያቱም እሱ የከሽፍ (መገለጥ) ባለቤት ነውና ይላል። [ሚርኣቱል ጂናን፡ 3/272] ሱፊያ ሰፈር እንዲህ አይነት በሬ ወለደ ወሬ ብርቅ አይደለም። ያፊዒይም በዚህ የታወቀ ነው። ለማንኛውም ጀይላኒይና ኢብኑ ደቂቀል ዒድ ዘመናቸው አይገናኝም። ኢብኑ ደቂቅ የተወለዱት ጀይላኒይ ከሞቱ ከ64 በኋላ ነው። ምኑን ከምኑ እንደሚያገናኝ ተመልከቱ። ባለ ከሽፉ እንዲህ አይነት መክሹፍ (የተጋለጠ) ውሸት ነው የዋሸው። ታሪኩ ቅጥፈት እንደሆነ ሌሎች ነጥቦችን መጨመር ቢቻልም በዚህ ደረጃ ላለ ቅጥፈት ደክሜ ማድከም አልፈለግኩም።
Show all...
ሙሓደራ 183 ክፍል አንድ (001) ★ ረድ በ አሕባሹ አቡበከር ላይ ★ 👉በ ሸይኹል ኢስላም ላይ ለቀጠፈው ቅጥፈት የተሰጠ ምላሽ እናም ሌሎች 🎙በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ(አቡ ሓቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed https://t.me/UstazKedirAhmed https://t.me/UstazKedirAhmed
Show all...
ከዚያም ቁርኣናዊ ማስረጃዎችን የዘረዘረ ሲሆን ቀጥሎም ኢስቲዋእን በኢስተውላ (ተቆጣጠረ) በመተርጎም በሚታወቁት ሙዕተዚላ ላይ የሰላ ትችት ሰንዝሯል። [ተእዊሉል አሓዲሢል ሙሽኪላ፣ ኢብኑ መህዲ፡ 24ኛ ወረቀት] [አልአስማእ፣ በይሀቂ፡ 2/307] “ኢስቲዋእ በዐረብ ቋንቋ መቆጣጠር ማለት አይደለም” በማለትም ለአክባሪዎቹ አሽዐሪያዎች ምቾት የማይሰጥ ምስክርነት ሰጥቷል። [ተእዊል፡ 25ኛ ወረቀት] ልብ በሉ! ዐሊይ ብኑ መህዲ አላህ ከሁሉ ነገር በላይ በዐርሹ በላይ መሆኑን ያፀድቅ እንደነበር በይሀቂይም መስክረዋል። [አልአስማእ፡ ቁ. 870] አሽዐሪዮች “ኢስተዋ” የሚለውን “ኢስተውላ” እያሉ ለመቆልመም (ተእዊል ለማድረግ) የሚጠቀሙትን ስንኝ አስመልክቶም እንዲህ ብሏል፡- “በዐርሹ ላይ ኢስቲዋእ የማድረጉ ትርጓሜም ገጣሚው … እንዳለው እሱን መቆጣጠር ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም መቆጣጠር ማለት ችሎታና ሃይል ነው። የላቀው አላህ ደግሞ ቻይ፣ ሃያልና አሸናፊ ከመሆን ተወግዶ አያውቅም። {ከዚያም በዐርሹ ላይ ከፍ አለ} ሲል ግን ይህ መገለጫ ካልነበረ በኋላ መምጣቱን ስለሚያሳይ እነሱ የሚሉት ውድቅ ይሆናል።” [አተምሂድ፡ 262] በአሕ - ባሽ የጥመት ስብከት የተሸወዳችሁ ወገኖቻችን ሆይ! አላህን ፈርታችሁ፣ አኺራችሁን አስባችሁ፣ ህሊናችሁን ከነዚህ አካላት ጫና ነፃ አድርጋችሁ እውነቱን መርምሩ። አላህ ልባችሁን ለሐቅ ክፍት ያድርግላችሁ። = (ኢብኑ ሙነወር፣ ሸዋል 10/1444 (ሚያዚያ 22/2015)) የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

አንድ እውነት በአሕ ^ባሽ ስብከት ለተሸወዳችሁ ሁሉ ~ ቀደምት የአሽዐሪያ መሪዎች የአላህን ከፍጡራን በላይ መሆን ያምኑ ነበር። "አላህ ከዐርሹ በላይ ነው" የሚሉ ሰዎችን ከኢስላም በማስወጣት ለሚታወቁት አሕ - ባሾች ይህንን መቀበል ከባድ ነው። መረጃው ይሄውና፡- 1. ኢብኑ ኩላብ (240 ሂ.)፡- አሽዐሪዮች ዘንድ የተከበረ “የኛ” የሚሉት ሸይኽ ነው። የዛሬ አሽዐሪዮች ከዚህ ሰውየ የቀዱት መሰረታዊ ዐቂዳ ስላላቸው እውነተኛው የአሽዐሪያ መዝሀብ መስራች ኢብኑ ኩላብ ነው እስከሚባል ተደርሷል። አሽዐርዮቹ አቡ መንሱር አልበግዳዲይና ሸህረስታኒም ሸይኻቸው እንደሆነ መስክረዋል። [ኡሱሉዲን፣ በግዳዲይ፡ 104] [ኒሃየቱል ኢቅዳም፡ 303] ከመሆኑም ጋር በያዝነው ጉዳይ ላይ ያለው ዐቂዳ ግን ከነሱ የተለየ ነው። ይሄውና ቃሉ፡- ولو لم يشهد لصحة مذهب الجماعة في هذا الفن خاصة إلا ماذكرنا من هذه الأمور لكان فيه ما يكفي، كيف وقد غرس في بنيه الفطرة ومعارف الآدميين من ذلك مالا شيء أبين منه ولا أوكد؟ لأنك لا تسأل أحدا من الناس عنه، عربيا ولا عجميا، ولا مؤمنا ولا كافرا فتقول: أين ربك؟ إلا قال: في السماء إن أفصح، أو أومأ بيده أو أشار بطرفه إن كان لا يفصح “ለ(አህሉ ሱና) ወልጀማዐ መዝሀብ ትክክለኝነት በዚህ ዘርፍ ላይ የጠቀስናቸው ነገሮች እንጂ ሌላ ምስክር ባይኖር እንኳ በዚህ ውስጥ የሚበቃ ነገር አለ። በንፁህ ተፈጥሮና በሰው ዘር እዝነ ልቦና ላይ የተተከለ ነገር እንዴትስ ብሩህና የፀና አይሆን? ምክንያቱም ዐረብም ይሁን ሌላው አማኝም ይሁን ከሃዲ ማንንም ሰው ‘ጌታህ የት ነው?’ ብለህ ስለሱ አትጠይቅም መግለፅ ከቻለ ‘በሰማይ’ የሚልህ፣ መግለፅ ካልቻለ በእጁ ወይም በአይኑ የሚያመላክትህ ቢሆን እንጂ።” [ደርእ፡ 6/194] [አልጁዩሽ፡ 1/435] "የተጠቀምካቸው ምንጮች የኢብኑ ተይሚያ ኪታቦች ናቸው" የሚል ተቃውሞ የሚያነሳ ካለ ኢብኑ ኩላብ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን በሚገባ ያፀድቅ እንደነበር አቡል ሐሰን አልአሽዐሪይና አቡ መንሱር አልበግዳዲይም አረጋግጠዋል። [መቃላቱል ኢስላሚዪን፡ 299] [ኡሱሉዲን፡ 113] ኢብኑ ኩላብ ዛሬ አሕባሾች የሚያራምዱትን አቋም እንዲህ ሲል ኮንኖታል፡- “ከአእምሯዊ ምልከታም ከቁርኣንና ሐዲሥም የመጨረሻ ያፈነገጠው ደግሞ ‘አለም ውስጥም አይደለም፣ ከሱ ውጭም አይደለም’ በማለት እኩል ያራቆተው ነው። ምክንያቱም ‘እስኪ ባለመኖር ግለፀው’ ቢባል ከዚህ በበዛ ስለሱ ምንም ሊል አይችልምና። ቀጥተኛ የሆኑ የአላህን ዘገባዎች ነው የመለሰው። ከማስረጃም ከአመክንዮም አንፃር የማይሆን ነገር ነው በዚህ ላይ የተናገረው። የጠራው ተውሒድ ይሄ እደሆነ ሞግቷል። ጥርት ያለው ማራቆት እነሱ ዘንድ ጥርት ያለው ማፅደቅ ሆኗል።” [ደርእ፡ 6/119] [በያኑ ተልቢሲል ጀህሚያ፡ 1/44] 2. ሓሪሥ አልሙሓሲቢይ (243 ሂ.)፡- አሽዐሪዮች እንደ ሸይኻቸው የሚወስዱት ነው። [ኡሱሉዲን፡ 208-209] የአላህን ከፍጡራን በላይ መሆን በሚገባ ያፀድቃል። ለምሳሌ ይህን የሚያመላክቱ ማስረጃዎችን ከዘረዘረ በኋላ እንዲህ ብሏል፡- فهذا مَقْطَعٌ يوجبُ أنَّهُ فوقَ العرشِ، فوقَ الأشياءِ، منزَّهٌ عَنِ الدُّخولِ في خلقهِ، لا يخفى عليهِ منهم خافية، لأنَّهُ أبانَ في هذهِ الآياتِ أنَّ ذاتَهُ بنفسهِ فوقَ عبادهِ “ይሄ እርሱ ከዐርሹ በላይ፣ ከነገሮች በላይ እንደሆነ በፍጡሮቹ ውስጥ ከመግባት የጠራ እንደሆነና ከነሱ የትኛዋም ስውር ነገር እንደማትሰወረው የሚያስረግጥ ክፍል ነው። ምክንያቱም በነዚህ አንቀፆች ውስጥ እሱ ዛቱ በራሱ ከባሮቹ በላይ እንደሆነ ግልፅ አድርጓልና። …” ቀጥሎም ማስረጃዎችንና ዘለግ ያሉ ትንታኔዎችን ይሰጣል። [ፈህሙል ቁርኣን፡ 349 - 352] በሌላ ቦታም ስለ ቁርኣን ሲያወራ እንዲህ ብሏል፡- وَقد تكلم بِهِ بِنَفسِهِ من فَوق عَرْشه وأنزله مَعَ الْأمين من ملايكته إِلَى أَمِين أهل الأَرْض “በርግጥም በሱ (በቁርኣኑ) ከዐርሹ በላይ ሲሆን በራሱ ተናግሯል። ከመላእክት ውስጥ ከታማኙ (ጂብሪል) ጋር ከምድራውያን ውስጥ ታማኝ ወደሆነው (ሙሐመድ) አውርዶታል።” [ፈህሙል ቁርኣን፡ 309] 3. አቡል ዐባስ አልቀላንሲይ፡- ከአቡል ሐሰን አልአሽዐሪይ ጋር አንድ ዘመን ከመሆኑ በስተቀር የውልደቱም የህልፈቱም አመት በውል አይታወቅም። ከአሽዐሪያ ኢማሞች እንደሆነ ግን እራሳቸው መስክረዋል። [ኡሱሉዲን፡ 310] አቡ መንሱር አልበግዳዲይ በኢስቲዋእ ዙሪያ አሽዐሪዮች ያንፀባረቋቸውን የተለያዩ ሀሳቦች ሲዘረዝር እንዲህ ብሏል፡- ومنهم من قال: إن استواءه على العرش كونه فوق العرش بلا مماسة، وهذا قول القلانسي وعبد الله بن سعيد “ከነሱም ውስጥ ‘ኢስቲዋኡ ያለ መነካካት ከዐርሹ በላይ መሆኑ ነው’ ያለ አለ። ይህ #የቀላንሲይ እና የዐብደላህ ብኑ ሰዒድ (ኢብኑ ኩላብ) አቋም ነው።” [ኡሱሉዲን፡ 113] ከኢብኑ ዐሳኪርም እንዲህ የሚል ማረጋገጫ እናገኛለን፡- وَهُوَ من جملَة الْعلمَاء الْكِبَار الْأَثْبَات واعتقاده مُوَافق لاعْتِقَاده فِي الْإِثْبَات “እርሱ (ቀላንሲይ) ከታላላቅና ታማኝ ዑለማዎች ውስጥ ሲሆን እምነቱም ከሱ (ከአቡል ሐሰን) የማፅደቅ እምነት ጋር ተመሳሳይ ነው።“ [ተብዪን፡ 398] ኢብኑ በዚዛም (662 ሂ.) እንዲህ ብሏል፡- “ከአሽዐሪያ መሻይኽ ውስጥ የሆነው አልቀላንሲይ በሸሪዐ የተዘገቡ ጉልህ ማስረጃዎችን በመንተራስ ‘የላቀው አላህ በሁሉም ቦታ ሳይሆን በአንድ ቦታ ነው፤ እርሱ በሰማይ ነው’ ወደሚል አቋም ተጉዟል።” [አልኢስዓድ ፊ ሸርሒል ኢርሻድ፣ ኢብኑ በዚዛ፡ 225] 4. አቡል ሐሰን አልአሽዐሪይ (324 ሂ.)፡- አህሉ ሱና “የላቀው አላህ በምድሩ ሳይሆን ከሰማያቱ በላይ በዐርሹ ላይ እንደሆነም ኢጅማዕ አድርገዋል። ... የኢስቲዋኡ ፍቺ ቀደሪያዎች (ሙዕተዚላዎች) እንደሚሉት መቆጣጠር ማለት አይደለም” ብሏል። [ሪሳላ ኢላ አህሊ ሠግር፡ 130-131] ስለ አቡል ሐሰን ዐቂዳ ዝርዝር የፈለገ ከዚህ በፊት የፃፍኩትን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይችላል፦ https://tinyurl.com/5y8k639h 5. ዐሊይ ብኑ መህዲ አጦበሪይ (380 ሂ.)፡- የአቡል ሐሰን አልአሽዐሪ ተማሪ ነው። እንዲህ ብሏል፡- اعلمْ - عصمنا الله وإيَّاكَ مِنَ الزيغِ برحمته - أنَّ الله سبحانه في السَّمَاء فوقَ كلِّ شيءٍ، مستوٍ على عرشهِ، بمعنى أنَّه عَالٍ عليه “እኛንም አንተንም አላህ በእዝነቱ ከጥመት ይጠብቀንና - የጠራው አላህ - ከሁሉም ነገር በላይ በሰማይ እንደሆነ፣ በዐርሹ ላይ ከፍ ያለ ነው በሚል ፍቺ ኢስቲዋእ ያደረገ እንደሆነ እወቅ።”
Show all...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.