Tutorial education
Open in Telegram
በዚህ Channel የተለያዩ አዝናኝ እና ትምህርታዊ ጥያቄዎችን የምንሰጥ ሲሆን ከ 9-12 teacher guide እና student text book ይለቀቃለል fresh man hand out ጨምሮ ትምህርታዊ video ሚለቀቅበት youtube ቻናል https://youtube.com/channel/UCKgCFVUAn-pO62mit5fD4xQ subscribe በማድረግ ተከታተሉን እናመሰግናለን
Show more297
Subscribers
-324 hours
+17 days
-1430 days
Posts Archive
Repost from 𝖊-𝖘𝖆𝖋𝖊
@esafeSoftwareSolution
⁉️Share this application for your friends! Grade 9 text books android app
#share for your Friend
#ማስታወቂያ
የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።
በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ እንገልፃለን ።
ማሳሰቢያ :-
የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።
የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
Website:
https://placement.ethernet.edu.et
SMS: 9444
ትምህርት ሚኒስቴር
🔔ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇
@tutorial_education
#ማስታወቂያ
በ 2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁና በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ወደ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተመደባችሁ ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችሁ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ
placement.ethernet.edu.et
ላይ በመግባት Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታችሁን እስከ የካቲት 07/2015 ዓ.ም 06፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻም ሆን ቅሬታ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።
የ12ኛ ከ50 ከመቶ በታች ያመጡ የአቅም ማሻሻያ (remedial) ነጥብ ይፋ ተደርጓል።
በምስሉ ላይ ይመልከቱ!
#ትምህርት ሚንስቴር
የአቅም ማሻሻያ (ረሜዲያል) የመቁረጫ ነጥብ ተለቋል፦
-የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 263
- የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 227
- የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 220
- የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 190
- የታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 210
- የታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 210
- የታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 180
- የታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቀረጫ ነጥብ 👉 180
(ከላይ በምስሉ ላይ ይመልከቱ)
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆
📚•• @tutorial_education
📚•• @tutorial_education
#SHARE
☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆
#ማስታወቂያ የዩኒቨርስቲ ምደባን በሚመለከት
በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከየካቲት 05/2015 እኩለ ሌሊት ጀምሮ ይፋ ይደረጋል።
ስለሆነም ተማሪዎች ከታች በተገለጹት አማራጮች የተመደባችሁበትን ተቋም ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ከየካቲት 15/2015 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትቆዩ እናሳስባለን፡፡
የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
Website: https://result.ethernet.edu.et
SMS: 9444
Telegram bot: @moestudentbot
ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችሁ ማንኛውም ጥያቄ
result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Complaint
የሚለውን በመጫን ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ምንም አይነት ጥያቄም ሆነ ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።
በዚሁ አጋጣሚ ተማሪዎች የትምህርት ጥራትን ለማረጋጋጥ የጀመርናቸውን የሪፎርም ሥራዎች እንዲሳኩ የበኩላችሁን እንድትወጡ እያልን በዩኒቨርስቲ ቆይታችሁ ህልማችሁ እንዲሳካና በቀጣይ ጠንካራ አገር ለመገንባት እንደ ህዝብ ለጀመርነው ተግባር ተገቢውን እውቀትና አስተውሎት የምትይዙበት ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
# ማስታወቂያ
የዩኒቨርስቲ ምርጫ ማስተካከያ ቀን እስከ #የካቲት 03/2015 ዓም. መራዘሙን ስለማሳወቅ
በ2014 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ እንዲሁም በመንግስት ተቋማት ገብተው መማር የሚፈልጉ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን እስከ የካቲት 03/2015 ዓ.ም 12፡00 ሰዓት ድረስ እንዲያስተካክሉ ቀኑ የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን በየትምህርትቤቱ በተወከሉ መምህራን በኩል ምርጫችሁን ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማስታወሻ፤
1. ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደማህበራዊ ሳይንስ ቀይራችሁ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች መቀየር የምትችሉት ዩኒቨርስቲ ከገባችሁ በኋላ ዩኒቨርስቲዎቹ ለመቀበል ፈቃደኛ ከሆኑ ብቻ መሆኑን አዉቃችሁ የምርጫ ማስተካከያችሁን በጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳዉቃለን፡፡
2. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት የልህቀት ማዕከል ሆኖ መደራጀቱን ግንዛቤ አንዲወሰድ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ ?
- በ2014 የትምህርት ዘመን ለፈተና የተመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጠቅላላ 985 ሺህ 354 ተማሪዎች ሲሆኑ ለፈተና የቀረቡት 92 ነጥብ 2 % 908 ሺህ 256 ተማሪዎቹ ሲሆኑ 77 ሺህ 98 ተማሪዎች ፈተና አልወሰዱም።
- በደንብ ጥሰት ፣ለመኮራረጅ በመፈለግ እና በሌሎች ምክንያቶች 50 ሺህ 170 ተማሪዎች ሳይፈተኑ ቀርተዋል።
- በ2014 የትምህርት ዘመን 899 ሺህ 520 ተማሪዎች ተፈትነዋል ።
- በፆታ ማዕከልነት የአማካይ ውጤት በወንዶች 30 ነጥብ 2 እንዲሁም ሴቶች 28 ነጥብ 09 % አማካይ ውጤት አስመዝግበዋል።
- በትምህርት ዘርፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ በተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ 31 ነጥብ 63 ከመቶ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ 27 ነጥብ 79 ከመቶ በአማካኝ አስመዝግበዋል።
- በክልል ደረጃ ይህየ ነው የሚባል የውጤት ልዩነት የሌለ ሲሆን አዲስ አበባ ፣ ሐረሪ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የተሻለ ውጤት አስመዝግበዋል።
- ከተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንድ ከ 700፤ 666 ያስመዘገበ ሲሆን 650 ሴት ተማሪ አስመዝግባለች ።
- በማህበራዊ ሳይንስ ከ600 ወንድ 524 አስመዝግቧል።
- ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና እና ሽልማት ይሰጣቸዋል።
Credit : WMCC
@tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
#Update
" ብዙም አይርቅም "
የትምህርት ሚኒስቴር በ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ ይሰጣል።
የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ትላንት ለሊት ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
ከውጤቱ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ መግለጫ ዛሬ ከሰዓት 8:00 በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደሚሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
" የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ውጤታቸው ከ50 በመቶ በላይ የሆኑ ተማሪዎች ከ28 ሺህ እንደማይበልጥ" በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ ይገኛል ፤ ይህን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ጥያቄ አቅርቦ ነበር።
ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች አሐዝ ከ28 ሺህ " #ብዙም_እንደማይርቅ " ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።
እስካሁን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ ይታወቃል።
More : @tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
@tutorial_education
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን ተማሪዎች ከዛሬ ለሊት ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተፈታኞች ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም #ከሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ ፡-
• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ https://t.me/eaesbot
ማየት የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።
ማሳሰቢያ፡-
• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል።
• ተማሪዎች ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አድራሻ ላይ ብቻ እንዲጠቀሙ #ከተመሳሳይ እና #የተዛባ_መረጃ ለማሰራጫት ከሚሞክሩ አካላት እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተላልፏል።
ምንጭ ፦ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
@tutorial_education
#ሰበር_ዜና #Breaking_News
ከ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት (ከ50% በላይ) ያመጡት ሦስት በመቶ ብቻ ናቸው 😳
የፈተና ውጤቱ ከዛሬ እኩለ ሌሊት ጀምሮ በበይነመረብ ይፋ እንደሚደረግ፣ ተማሪዎችም በተሰጣቸው የመለያ ቁጥር ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ማረጋገጧን #አዲስ_ማለዳ ዘግባለች።
ሌላው ውጤት ሲለቀቅ #Network ይጨናነቃል። ስለዚህ በኛ በኩል ፈጥናችሁ ማየት የምትፈልጉ
https://t.me/tutorial_education
አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ በትምህርቱ ዘርፍ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮችን ያካተተ እንደሆነ ተገለፀ
--------------------------------------------------------------------------
ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ረቂቅ ላይ ከምሁራን ጋር ምክክር እያካሄደ ነው ።
የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር) ረቂቅ ፖሊሲው በተለያዩ ጊዜያት ምክክር ሲደረግበት የቆየ መሆኑን እና በትምህርቱ ዘርፍ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣሉ ተብለው የታሰቡ ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑን ገልፀዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የደረሰውን ስብራት ለማከም ፖሊሲ መቅረፅ ብቻውን ለውጥ አያመጣም ያሉት ሚኒስትሩ ያሉ ስብራቶችን በሙሉ ለመቅረፍ በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅም ገልፀዋል።
ፓሊሲው በትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታው የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን በመመልከት በትምህርቱ ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን ሊፈታ በሚችልና አለም አቀፍ ስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ መዘጋጀቱም ተገልጿል።
በቀጣይም የፖሊሲ ማስፈፀሚያ ስትራቴጂዎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና ፕሮግራሞች እንደሚዘጋጁም ነው የተነገረው።
ፓሊሲውን ለመተግበርም የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ተሳትፎ እንደሚጠይቅም በመድረኩ ተነስቷል።
የረቂቅ ፖሊሲው ዋና ዋና ሀሳቦች የትምህርት ሚኒስትር የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ስራ አስፈፃሚ በሆኑት ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይትም ተደርጎበታል።
ሙሉ ዜናው👇
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0G2hDutggSPG9skoNpHHto3PyBvhtqKaKySKeZ3G5x965gpYcspu7rb43ejTkomL1l&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
The area of a rectangle is 8cm2. If one side exceeds the other by 2cm, what the dimensions of the rectangle?
If two straight lines are perpendicular to each other, which one of the following is correct?
Join us @qubeeacademy
Which of is following triples is length of a triangle? The triangle is any type of triangle.
The independent variable in an experiment is the variable that:
