en
Feedback
CUSTOMS COMMISSION JIGJIGA BRANCH/በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

CUSTOMS COMMISSION JIGJIGA BRANCH/በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

Open in Telegram

ራዕይ፡- "በ2022 በአገራችን ደረጃዉን የጠበቀ ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳደር ተገንብቶ ማየት ስ/ቁ-025-775-72-77

Show more
3 409
Subscribers
+324 hours
+107 days
+12030 days
Posts Archive
የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ማህበራዊ ኃላፊነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ጅግጅጋ፣ ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በሶማሌ ክልል በፋፋን ዞን በሀደው ወረዳ ለሚገኘው ሀደው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚማሩ 100 ያህል የወገንን እርዳታ ለሚሹ ተማሪዎች የ125,020 ብር ዋጋ ያላቸው የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ። ድጋፉ በቅ/ጽ/ቤቱ አመራሮችና ሠራተኞች፣ በሀደው ወረዳ አመራሮች፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት የተደረገ ሲሆን፣ የተማሪዎቹን የትምህርት ሂደት ለማገዝ ቦርሳ፣ ደብተርና እስክሪብቶ ተበርክቷል። የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ አዲስ ጌታቸው እንዳሉት፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ገቢ ከመሰብሰብና ኮንትሮባንድን ከመከላከል ባሻገር የሀገራዊ ማህበራዊ ኃላፊነቱንም በተገቢው መንገድ እየተወጣ መሆኑን ገልጿል። የዛሬ ታዳጊ ተማሪዎች ነገ ክልሉን፣ ዞኑንና ወረዳውን የሚመሩ እንዲሁም ወደ ተለያዩ ተቋማት የሚቀላቀሉ ዜጎች በመሆናቸው፣ በእነሱ ላይ መሥራት የነገን ሀገር መሠረት መገንባት መሆኑንም አቶ አዲስ ጌታቸው ገልጸዋል። በሀገራችን እየተሠሩ ያሉ ፕሮጀክቶች በተለያዩ የቀረጥና የታክስ ገቢዎች የሚሸፈኑ በመሆናቸው፣ ከክልሉ የፀጥታ ዘርፍና ከክልል መስተዳድር ጋር በቅንጅት በመሥራት የተሻለ ውጤት መመዝገብ እንደሚቻልም አንስተዋል። የሀደው ወረዳ የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዲ በበኩላቸው፣ የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች ያደረገውን ድጋፍ አድንቀው፣ የተማሪዎችን ትምህርት ለማገዝ የተደረገው ተግባር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የተደረገው ድጋፍ የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ከመደበኛ የጉምሩክ ሥራው በተጨማሪ ለማህበረሰቡ ያለውን ኃላፊነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል። በደንበኞች ትምህርት ቡድን ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ

የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት መጪውን 2019 አዲስ ዓመት አቀባበል በደማቅ ሁኔታ አከበረ ጅግጅጋ፣ ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም በሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቡድን አስተባባሪነት የተዘጋጀው የእንኳን አደረሳችሁና የመልካም ምኞት ፕሮግራም በቅ/ጽ/ቤቱ ቅጥር ግቢ ተከብሯል። በፕሮግራሙም የቅ/ጽ/ቤቱ ሰራተኞችና አመራሮች በመገኘት የአዲሱን ዓመት መልካም ምኞት ተለዋውጠዋል። በፕሮግራሙ ላይ የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ አዲስ ጌታቸው፣ መጪው አዲስ ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት ዓመት እንዲሆን ተመኝተዋል። በ2018 በጀት ዓመት የተገኘውን ውጤት በአዲስ ዓመት ለመድገም በትብብርና በአንድነት መስራት እንደሚገባም በማንሳት፣ የመልካም አዲስ ዓመት ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። እንዲሁም ከደረጃ አንድ እስከ አምስት ለሚገኙ ሰራተኞች በዓሉን ምክንያት በማድረግ የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል። የዕለቱን መርሃ ግብር የአበባዮሁሽ ባህላዊ ጭፈራ ያደመቀ ሲሆን፣ በባህላዊ ጭፈራው የበዓሉ ድባብ ይበልጥ ደምቆ ተሳታፊዎችም በደስታ የአዲሱን ዓመት አቀባበል አድርገዋል። ቅ/ጽ/ቤቱ አዲሱ ዓመት የአብሮነትና የመተባበር ዓመት ሆኖ፣ ዕቅዶችን በጋራ የሚያሳካበትና የተሻለ ውጤት የሚመዘገብበት እንዲሆን እየተመኘ ለሰራተኞች፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለሁሉም መልካም በዓልና መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን ይገልጻል። መልካም አዲስ ዓመት!!!

የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የ2019 ዕቅድ ትውውቅ አካሄደ ጅግጅጋ፣ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም በመርሃ-ግብሩ የቅ/ጽ/ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስራ ሂደቶች፣ የመቆጣጠሪያ ጣቢያ አስተባባሪዎች፣ ሰራተኞች ፣ የፌደራል ፖሊስ አመራሮች፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች፣ የክልሉ ሚሊሻ አመራሮች፣ አምራቾች፣ አስመጪ፣ ላኪዎች፣ የጉምሩክ አስተላላፊዎች እንዲሁም የምግብና መድኃኒት፣ የደረጃ እና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሀላፊዎች ተሳትፈዋል። የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ አዲስ ጌታቸው በመክፈቻ ንግግራቸው በ2018 በጀት አመት የተመዘገበውን ስኬት በ2019 በጀት ዓመት ለማስቀጠልና የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በትጋት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። አቶ አዲስ አክለውም ከባለፈው በጀት ዓመት ልምድ በመውሰድ ክፍተቶችን በማረም፣ የገቢ አሰባሰብን በማሻሻልና የኮንትሮባንድ ቁጥጥርን በማጠናከር የተሻለ የስራ አፈጻጸም ማስመዝገብ እንደሚገባ ገልጸዋል። በ2018 በጀት አመት የተለያዩ የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለመንግስት ገቢ ከማስገኘት ባለፈ፣ በተሰራው ውጤታማ ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሽልማትና እውቅና መገኘቱን አቶ አዲስ ገልጸዋል። የቅ/ጽ/ቤቱ የዕቅድና ልውጥ ስራዎች ቡድን ተወካይ አቶ አብዱረሂም አምረዲን በበኩላቸው፣ ቅ/ጽ/ቤቱ በ2019 በጀት አመት 5.39 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ያቀደ መሆኑን ገልጸው፣ የገቢ ዕቅዱን ለማሳካት የተቀመጡ የስራ አቅጣጫዎችን ለተሳታፊዎች አስተዋውቀዋል። የ2018 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ውጤቶችና ተግዳሮቶች በመገምገም፣ በ2019 በጀት አመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በተቀመጡ የስራ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ አዲስ ጌታቸው ሰፊ ማብራሪያ በመስጠት በ2019 በጀት ዓመት ለቅ/ጽ/ቤቱ የተቀመጠውን ዕቅድ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላትና ከጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር በቅንጅትና በትብብር በመስራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ አቅጣጫ ተሰጥተዋል። በደንበኞች ትምህርት ቡድን ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ