✞✟ ኦርቶዶክሳዉያን ✞✟
እንኳን ወደ ቻናላችን በሰላም መጣቹ ይህ ቻናል የተከፈተው ለኦርቶዶክሳውያን እና ማወቅ ለሚፈልግ ለማንኛውም ሰው ነው ✞መዝሙር ✟ግጥም ✞ኦርቶዶክሳዊ ፎቶ ያገኙበታል
Show more529
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1630 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
†
🕊 💖 ሰ ላ ም ታ 💖 🕊
'' ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰይጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ''
🕊
'' ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ''
† † †
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኤርምያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† 🕊 ቅዱስ ኤርምያስ 🕊 †
† ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ከዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በስድስት መቶ አካባቢ የነበረ ነቢይ ነው:: አባቱ ኬልቅዩ ይባላል:: ከካህናተ እስራኤል አንዱ ነበር::
እግዚአብሔር ኤርምያስን የጠራው ገና በሕፃንነቱ ነበር:: "ከእናትህ ማኅጸን ሳትወጣ መርጬሃለሁ: ቀድሼሃለሁ" ሲልም በገሃድ መስክሮለታል:: [ኤር.፩፥፭] (1:5)
ከቅዱሳን ነቢያት እንደ ኤርምያስ የተሰቃየና ያለቀሰ የለም:: ከሰባ ዘመናት በላይ ስለ ወገኖቹ አልቅሷልና ሊቃውንት "ነቢየ ብካይ" [ባለ እንባው ነቢይ] ይሉታል::
ዘመኑ ዘመነ-ኃጢአት [ዘመነ ዐጸባ] ነበር:: እሥራኤላውያን ከመሪዎቻቸው ከነ ሴዴቅያስ ጋር በክፋት ተባብረውም ነበርና ኤርምያስን አልሰሙትም:: ይልቁኑ ክፉ ቦታ ውስጥ አስረው አሰቃዩት:: እግዚአብሔር ግን በኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አማካኝነት ከመከራው አዳነው::
የተሰበከላቸውን የንስሐ ጥሪ አልሰሙምና ስልምናሦር የሚባል የአሕዛብ ንጉሥ መጥቶ አሥሩን ነገድ ማርኮ በ፯፻፳፪ [722] አሦር [ነነዌ] አወረዳቸው:: በኋላ ደግሞ በኃይለኝነቱ የታወቀው የባቢሎን ንጉሥ ይማርካቸው ዘንድ ወደ ሁለቱ ነገድ ኢየሩሳሌም ደረሰ:: ኤርምያስ ወደ ከተማዋ ዳር ወጥቶ ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አለቀሰ::
ከቤተ መቅደስ ንዋያት እኩሉን ለምድር አደራ ሰጣትና ሸሸገችው:: ነቢዩ የተናገረው አይቀርምና ንጉሡ ናቡከደነጾር እኩሉን ገድሎ: እኩሉንም ማርኮ: ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ: የአሕዛብ መዘባበቻ አድርጐ በ፭፻፹፮ [586] ባቢሎን አወረዳቸው::
ቅዱስ ኤርምያስን ግን ትሩፋን [ከመከራው የተረፉት] ይዘውት ወደ ግብጽ ወረዱ እንጂ አልተማረከም:: በዚያም ተአምራትን አድርጐ አራዊትን አጥፍቷቸዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን እውነተኛ አባት : ነቢይ : መምሕርም ነውና ወደ ሕዝቡ [ወደ ባቢሎን] ወረደ:: በዚያም ትንቢትን እየተናገረ : ሕዝቡን ከሰባ ዓመታት በኋላ ወደ ሐገራቸው እንደሚመለሱ እያስተማራቸው በባቢሎን ቆይቷል:: ያለ በደሉም በመከራቸው ተካፋይ ሆኗል::
ሰባው ዘመን ሲፈጸም እግዚአብሔር እንደ ቃል ኪዳኑ በኤርምያስ መሪነት እሥራኤል ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: አሁንም ግን ክፋታቸውን ይተው ዘንድ ፈቃደኞች አልነበሩምና ኤርምያስ ገሠጻቸው::
በዚህ ተበሳጭተው ሊወግሩት ሲሉ ጸጋ በዝቶለት : ምሥጢርም ሰፍቶለት ስለ ነገረ ሥጋዌ [ስለ ክርስቶስ የማዳን ሥራ] አምልቶና አጉልቶ ትንቢት ተናገረ:: አንዴ ልቡናቸው ታውሮ ኤርምያስ ነው ብለው ድንጋዩን በድንጋይ ሲወግሩት ውለዋል:: ዘግይቶ ግን ኤርምያስ ራሱን ገለጠላቸው:: ስለ እነርሱ ሲል ሰባ ዘመን ያለቀሰውንና ምትክ የሌለውን አባታቸውን ወግረው ገደሉት::
ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ሃምሳ ሁለት ምዕራፎች ያሉት ሐረገ ትንቢት ተናግሯል / ጽፏል:: ዜና ሕይወቱ ከራሱ የትንቢት መጽሐፍ በተጨማሪ በተረፈ ኤርምያስ : በመጽሐፈ ባሮክ : በገድለ ኤርምያስ : በዜና ብጹዐን : በመጽሐፈ ስንክሳርም ተጽፏል::
† ቸር እግዚአብሔር በኤርምያስ ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿን ከስደትና ከመቅሰፍት ይሰውርልን::
🕊
[ † ግንቦት ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ [ከታላላቆቹ ነቢያት አንዱ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ
፫. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ
፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
† " ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል : ወደ እርሷ የተላኩትንም የምትወግር : ዶሮ ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም:: እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል:: እላችሁአለሁና : በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም :: " [ማቴ. ፳፫፥፴፯-፴፱]
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
†
[ 🕊 ዳግሚያ ትንሳኤ ! 🕊 ]
እንኩዋን ለዳግሚያ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ !
💖
✞ እሁድ - ዳግም ትንሣኤ ይባላል ፦
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
---------------------------------------------
"ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ:: በመካከላቸውም ቆሞ 'ሰላም ለእናንተ ይሁን' አላቸው:: ከዚያም በሁዋላ ቶማስን 'ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ:: እጅህንም አምጣና በጐኔ አግባው:: ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን' አለው:: ቶማስም 'ጌታዬ አምላኬም' ብሎ መለሰለት:: ኢየሱስም 'ስላየኸኝ አምነሃል:: ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን ናቸው' አለው::" [ዮሐ.፳፥፳፮-፳፱]
† † †
💖 🕊 💖
†
🕊 💖 ዕለተ ሰንበት 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
† 🕊 ዳግሚያ ትንሳኤ ! 🕊 †
እንኩዋን ለዳግሚያ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ።
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይድረሰውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ትንሳኤው በሁዋላ ለደቀ መዛሙርቱ በጉባኤ ፫ [3] ጊዜ ተገልጦላቸዋል :-
፩. በዕለተ ትንሳኤ ምሽት በፍርሃት ሳሉ
፪. ያላመነ ቶማስን ለማሳመን በተነሳ በ ፰ [ 8 ]ኛው ቀን [ ማለትም ዛሬ ]
፫. ከተነሳ ከ ፳፫ [ 23 ] ቀናት በሁዋላ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻ ላይ ነው::
ጌታ አርባውን ቀን ለአንዱም: ለሁለቱም በግል ይገለጥላቸው ነበር:: እመቤታችንን ግን ፈጽሞ አይለያትም ነበር::
ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለሳምንት ተለይቷቸው ስለ ነበር በቤተ ክርስቲያን ውዳሴ ማርያም እንጂ መልክዐ ኢየሱስ በማሕበር አይደገምም::
በዚሕች ዕለት ደቀ መዛሙርቱ በጽርሐ ጽዮን ሳሉ ጌታችን "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ብሏቸዋል:: ቶማስንም "ና ዳስሰኝ" ብሎታል:: ሐዋርያው እጁን ከተወጋ ጐኑ ላይ ቢያሳርፍ በመቃጠሉ "ጌታየ አምላኬም" ሲል ጮሆ ምስጢረ ተዋሕዶውን መስክሯል::
ጌታም ቶማስን "እስመ ርኢከኒሁ አመንከኒ" [ማለትም ስላየኸኝ አመንከኝ] ! "ብጹዐንሰ እለ እንዘ ኢይሬእዩኒ የአምኑኒ" [ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብጹዐን (ማለትም ንዑዳን ክቡራን) ናቸው ብሎታል:: [ዮሐ.፳፥፳፬] (20:24)
ከጌታችን ከትንሳኤው: ከቅዱሱም ሐዋርያ በረከት አይለየን::
❝ ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ:: በመካከላቸውም ቆሞ 'ሰላም ለእናንተ ይሁን' አላቸው:: ከዚያም በሁዋላ ቶማስን 'ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ:: እጅህንም አምጣና በጐኔ አግባው:: ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን' አለው:: ቶማስም 'ጌታዬ አምላኬም' ብሎ መለሰለት:: ኢየሱስም 'ስላየኸኝ አምነሃል:: ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን ናቸው' አለው:: ❞ [ዮሐ.፳፥፳፮-፳፱] (20:26-29)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
💖 🕊 💖
†
🕊 💖 ሰ ላ ም ታ 💖 🕊
'' ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰይጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ''
🕊
'' ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ''
💖
[ † 🕊 ክብርት ሰንበት 🕊 † ]
" ንጉሥ ከእርሱ ርቀን የነበርን እኛ ቤዛችን በሚሆን በልጁ ሕማም ከእርሱ ምን ያህል ክብር እንዳገኘን ዐወቅህን? ሞት ጠፋ ፣ ዲያብሎስም ድል ተነሣ ፣ ሲዖል ታወከ ፣ በኃጢአት የተፈረደው ፍርድ ተፋቀ ፣ ሰይጣን ያመጣው ስሕተት ጠፋ። እንዳልነበረም ሆነ ገነት ተከፈተ ትንሣኤ ተገለጠ"
[ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ ]
---------------------------------------------
" ለክርስቶስ ፡ ይደሉ ፡ ስብሐት ፤ ለዘአብጽሐነ ፡ እስከ፡ ዛቲ ፡ ሰዓት ፤ እግዚኣ ፡ ለሰንበት ፤ አኰቴተ ፡ ነዓርግ ለመንግሥትከ ፡ ወመኑ ፡ መሐሪ ፡ ዘከማከ።
ትርጉም ፦
[ እስከዚኽች ሰዓት ለአደረሰን ለክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባል፡፡ የሰንበት ጌታዋ ነው፡፡ ለጌትነትህ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ ማነው ? ]
[ ቅዱስ ያሬድ ]
† † †
💖 🕊 💖