For Students EI Tutor Centre (Sebe)
Open in Telegram
211
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Posts Archive
"አንድ ባለሱቅ፣ ልጁ ደስተኛ የመሆንን ሚስጥር እንዲያውቅ በዓለም ካሉ ጠቢባን ሁሉ በላይ ጥበበኛ ወደ ሆነ ሰው ላከው። ወጣቱ ለአርባ ቀናት በበረሃ ላይ ተጓዘ፤ በመጨረሻም ተራራ ጫፍ ላይ የተገነባ የሚያምር ሕንጻ አገኘ። ጥበበኛውም የሚኖረው እዛ ነበር።
ቅጽሩንም አልፎ ሲገባ፣ ግርግር ተመለከተ። ነጋዴዎች ይመጣሉ ይሄዳሉ፣ ሰዎች በየጥጋጥጉ ያውካካሉ፣ ሙዚቀኞች ዜማ ያወጣሉ፣ እናም አንድ ግዙፍ ጠረጴዛ ላይ ጣፋጭ ምግቦች እና መጠጦች ተሰድረዋል። ጥበበኛውም እርሱን ሊጠይቁ ከመጡ ሰዎች ጋር እየተጨዋወተ ነበር።
ወጣቱ ለምን ወደዚህ እንደመጣ አብራራ። ጥበበኛውም የወጣቱን ምክንያት ካዳመጠ በኋላ፤ "አሁን ለአንተ ደስተኛ የመሆንን ሚስጥር የማስረዳበት ጊዜ የለኝም። ከዚሁ ሳትርቅ ዙርያ ገባውን እየቃኘህ ቆይና ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተመለስ" አለው።
"ፍቅድህ ከሆነ፣ አንድ ነገር ላስቸግርህ" አለ ጥበበኛው። ለወጣቱ ዘይትን የተሞላ ማንኪያ አቀበለው። "አጸዴን ስትጎበኝም ይህንን ማንኪያ ይዘህ ሂድ፤ አንዲትም ጠብታ ዘይት እንዳታፈስ!"
"ወጣቱም ብዙ ደረጃዎችን ወጣ፣ ወረደ። ብዙ ግርግሮችን፣ ብዙ ሰዎችንም አለፈ። ነገር ግን አይኖቹ ከማንኪያው ላይ አልተነቀሉም። ከሁለት ሰዓታት በኋላም ጥበበኛው ወደ ነበረበት ስፍራ ተመለሰ።
"እና?" ጥበበኛው ጠየቀ። "የምግብ አዳራሼ ውስጥ የተነጠፈውን የፋርስ ምንጣፍ አየኸው? አትክልተኞች ለመገንባት አስር አመታት የፈጀባቸውን የአትክልት ስፍራ ውበቱን አደነቅክ? ቤተመጻሕፍት ውስጥ የነበሩትን ግዙፍ መጻሕፍትንስ አስተዋልካቸው?"
ወጣቱም እንደማፈር አለና ምንም ነገር እንዳላየ ተናዘዘ። የእርሱ ማስተዋል፣ በማንኪያው ዘይት አለመደፋት ላይ ያተኮረ ነበር።
"እንደዚያ ከሆነ ተመልሰህ ሂድና ድንቁን ዓለሜን ተመልከት" አለ ጥበበኛው። "ቤቴንም ስታይ ስለኔ ጥበበኛነት ታውቃለህ"
ወጣቱም የእፎይታን ፈገግታ አሳየና ማንኪያውን ይዞ ሽርሽር ጀመረ።
አሁን ጣራ እና ግድግዳው ላይ ያሉትን ጥበቦች በሙሉ ማድነቅ ጀመረ። የአትክልት ስፍራውን አየ፣ ስፍራው በበረሃ መሃል ያለ ገነት እንደሆነም አሰበ። ወብ አበቦችን፣ ጣፋጭ ምግቦችን፣ ቆነጃጅቶችንም ተመለከተ። የአእዋፋትን ዜማ ሰማ፣ የአበባዎችንም መዓዛ ማገ።
ሁሉንም አይቶ ሲጨርስም ወደ ጥበበኛው ተመለሰ። ለጥበበኛውም አንድም ሳያስቀር ያየውን በሙሉ ተረከለት።
"አስደሳች ጊዜን ያሳለፍክ ትመስላለህ፤ ሆኖም ማንኪያው ላይ የነበረው ዘይት የት አለ? ጥበበኛው ጠየቀ።
በእጁ ወደያዘው ማንኪያም ተመለከተ፤ የቀረ ዘይት የለም።
"ያው፤ ልሰጥህ የምችለው ምክር አንድ ነው!" አለ ጥበበኛው ሰው። የደስተኛነት ሚስጥር ይሄ ነው። ዓለምን ሁሉ ተመልከት፣ በውበቷም ተደነቅ፣ በማንኪያ የያዝከውንም ዘይት አትርሳ።'"
እረኛው አንዳችም ነገር አልተነፈሰም። ሽማግሌው ንጉስ የተረከለት በሚገባ ገብቶታል። እረኛ ጉዞን ሊወድ ይችል ይሆናል። ነገርግን በጎቹን በፍጹም መርሳት አይገባውም!!!
©
ውድ አልማዞች!
•••••••
የግመል ነጋዴው በገበያው ለሽያጭ ከቀረቡት ግመሎች መካከል በአንዱ እጅግ ስለተሳበ ከሻጩ ጋር ድርድር ጀመረ። በገዢና በሻጭ መካከል ብዙ ደቂቃዎችን የፈጀ የቀንስልኝ፣ አልቀንስም ክርክር ከተደረገ በኋላ ገዢው በዋጋ ተስማምቶ ግመሉን ገዝቶ ወደ ቤቱ ሄደ።
የግመል ነጋዴው ቤቱ እንደደረሰ አገልጋዩን ጠርቶ የግመሉን ኮርቻ እንዲያወርድ ይነግረዋል። አገልጋዩ የግመሉን ኮርቻ ሲፈታ ከኮርቻው ስር አነስተኛ መጠን ያላት የተቋጠረች ከረጢት ያገኛል። ከረጢቷን ሲፈታ በውድ የአልማዝ ማእድን ተሞልታለች።
አገልጋዩም "አለቃ የገዟት ግመል በነጻ ይዛ ያመጣችውን በረከት ይመልከቱ!" ሲል በደስታ ተሞልቶ ጮኸ። ነጋዴውም በአገልጋዩ መዳፍ ላይ በጸሐይ ብርሀን የሚንቦጎቦጉ የአልማዝ እንክብሎች ሲመለከት እጅግ ተደነቀ።
ይሁንና "ግመሏን እንጂ አልማዞቹን አልገዛኋቸውም። አሁኑኑ ለባለቤቱ መመለስ አለብኝ" አለ - ነጋዴው።
አገልጋዩም "ምን የማይረባ አለቃ ነው ያለኝ?!" ሲል በሆዱ ካወራ በኋላ "ማንም ሰው የአልማዞቹን ትክክለኛ ባለቤት ሊያውቅ አይችልም! ሲል ተናገረ።
ይሁንና ነጋዴው ምክሩን ችላ ብሎ ጊዜ ሳይወስድ ባለቤቱም ፍለጋ ወደ ገበያው ተመለሰ። ብዙም ሳይለፋ የተቀሩ ግመሎችን ለመሸጥ ገዢ ሲጠብቅ የነበረውን የግመል ሻጭ አግኝቶ ትንሿን ከረጢት መለሰለት።
የግመል ሻጩም እጅግ ተደስቶ " እጅግ የከበሩ ማእድናቴን በግላሱ ስር መደበቄን ዘንግቼ ነበር። አሁን ሽልማት እንዲሆንህ በከረጢቱ ውስጥ ካሉት አልማዞች ውስጥ ለዐይንህ ደስ ያሰኘህን ውሰድ!' አለ።
"ለከፈልኩት ገንዘብ ጥሩ ግመል ሽጠህልኛል። ተጨማሪ ሽልማትም ስጦታም አልቀበልም።" አለ - ነጋዴው። ነጋዴው ስጦታውን አልቀበልም ቢልም ግመል ሻጩ እንዲቀበለው ይወተውተው ጀመር።
በመጨረሻም ነጋዴው በፈገግታ ተሞልቶ "ከረጢቱን ልመልስልህ ስወስን ሁለት እጅግ የከበሩ አልማዞችን እራሴ ዘንድ አስቀርቻለሁ! ከእነርሱ የሚልቅ ሽልማት የለም!" አለው።
የግመል ሻጩ የነጋዴው የእምነት ቃል ሲሰማ እጅግ ተበሳጭቶ በከረጢቱ ውስጥ ያሉትን ውድ አልማዞች የጨርቅ እራፊ ላይ ደፍቶ ይቆጥራቸው ጀመረ። ይሁንና ቆጠራውን እንደጨረሰ በእፎይታ ተሞልቶ "በከረጢቱ ውስጥ ከነበሩት አልማዞቼ መካከል አንድም አልጎደለም። የትኞቹን ውድ አልማዞች ነው ለራሴ አስቀርቻለሁ ያልከኝ?"
ነጋዴውም በኩራት ተሞልቶ "እኔ ዘንድ ያስቀረኋቸው ውድ አልማዞች ታማኝነቴና ለፈጠረኝ (ከዚያም ለእራሴ) ያለኝ ክብር ናቸው!" ሲል መለሰለት።
ሻጩ የሰማውን ነገር ባለማመን ዐይኖቹን አፍጥጦ ነጋዴውን ከመመልከት ውጪ መልስ ሊሰጠው አልቻለም።
**
ሁላችንም ወደ እራሳችን መመልከትና እነዚያ ውድ አልማዞች እንዳሉን እንፈትሽ። ሁለቱ ውድ አልማዞች ያሉት ማኛውም ሰው የዓለማችን ባለጸጋው ሰው ነው።
እኔ እራሴን ፈትሼ ሁለቱ ውድ አልማዞች እንደሌለሉኝ አውቂያለሁ። ማነው እኔ ሁለቱም ውድ አልማዞች አሉኝ የሚል?(Anonymous )
🫵YOU HAVE AMPLE TIME TO
🌾get yourself emerged
⚖ Be balanced
📝correct what can be corrected
⚙Improve your thinking
📖 Read more books .
🧰Carefully indulge in self developments.
👨🏫🧑🍳🧑🎓 work on What your choice is.
🏃♀🏃♂ Exercise to be stronger and healthier.
🧒work on your happiness.
🧜♀👩👧👦💑 Be full of self love.
📌📊Check and improve your weaknesses.
🏆Be ready and comfortable about growth.
🌗🧖👩🌾👥be who you were meant to be.
➡️
ማህተመ ጋንዲ
1. ‹‹ ደስታ ማለት የምታስበውን ነገር፣ የምትናገረውን ነገርና የምታደርገውን ነገር ከሌሎች ጋር በመስማማትና በመዋሃድ የምታመጣው ሲሆን ነው፡፡ ››
2. ‹‹ ደካሞች ይቅር አይሉም፡፡ ይቅር ማለት ወይም ይቅርታ ማድረግ የጠንካሮች መገለጫ ነው፡፡ ››
3. ‹‹ ራስህን ስለሆንክና ትክክል ስለሆንክ ብዙ ሠዎች በተለይም አላዋቂ የሆኑ ሠዎች ሊቀጡህ ወይም ሊጠሉህ ይፈልጋሉ፡፡ ለትክክለኛነትህ ይቅርታ አታድርግለት፡፡ ትክክል ከሆንክና ትክክል መሆንህን ካወቅክ ለአዕምሮህ ንገረው፡፡ ምንም እንኳን ከታናናሾቹ አንዱ ብትሆንም እውነት አሁንም እውነት ነው፡፡ ››
4. ‹‹በዓለም ላይ የሰውን ስግብግብነት ለማሟላት ሳይሆን ለሰው ልጅ ፍላጎት የሚበቃ በቂ ነገር አለ።››
5. ‹‹እውነተኛ ሀብት የሆነው የወርቅና የብር ቁርጥራጭ ሳይሆን ጤና ነው።››
6. ‹‹ እኔ ሃይማኖተኛ ነው የምለው የሌሎችን ስቃይ የሚረዳ ሠውን ነው፡፡ ››
7. ‹‹ በዓለም ላይ እውነተኛው ሠላም እንዲሠፍን ከፈለግን ልጆችን ስለሠላም ማስተማር መጀመር አለብን፡፡ ››
8. ‹‹ መንፈሳዊ ጥንካሬ ከማይበገር ውስጣዊ ፈቃድ እንጂ ጡንቻን በማሳበጥ አይመጣም፡፡ ››
9. ‹‹ ነፃነት የመሳሳት ነፃነትን ካላካተተ በራሱ ዋጋ የለውም፡፡ ››
10. ‹‹ ማንም ሠው እኔን ከራሴ ፈቃድ ውጪ ሊጎዳኝ አይችልም፡፡ ››
11. ‹‹ ፀሎት ጧቱን መክፈቻ ቁልፍና እና ማታውን ማጥበቂያ ብሎን ነው፡፡ ››
12. ‹‹ ራስህን ለማግኘት ምርጡ መንገድ በአንተ ውስጥ ያለውን የሌሎች ማንነት መጣል ነው፡፡ ››
13. ‹‹ እንዴት ማሠብ እንዳለባቸው የሚያውቁ ሠዎች መምህር አያስፈልጋቸውም፡፡ ››
14. ‹‹ለመሞት ተዘጋጅቻለሁ፣ ለመግደል ግን የምዘጋጅበት ምንም ምክንያት የለም።››
This book is commonly used for math and English SAT exams. Especially starting from pages 66 for english.
