WKU Muslim student ጀምዓ(አስ ሰለፊይ)
Open in Telegram
በዚህ ቻናል የጀምዓው የቂርዓት የዳዕዋ እና መሰል የጀመዓው ፕሮግራሞች ይተላለፍበታል ኢንሻአላህ። https://t.me/WKUMuslimstudent
Show more409
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከኳስ ምን አተረፈክ?
▬▬▬▬▬▬▬▬
ዝነኛው ተጨዋች ከሆነ ሞዴልህ፣
በፀጉር አቆራረጥ የልብስ ስታይልህ፣
የዝውውር ዜና አሰላለፋቸው፣
የነሱ አፓርታሞ የደሞወዝ ጣራቸው፣
ማንስ አሸነፈ ጎሉን ማን አገባው፣
ማን ቀይ ካርድ አየ ዋንጫውን ማን በላው፣
ስል አሰልጣኛቸው መረጃ መጎርጎር፣
ተጫዋች መሸምደድ በስማቸው ዝርዝር፣
የትኛው ከተማ መቼ ተወለደ፣
የማልያ ቁጥሩን ሳይቀር ሸመደደ።
💥💥💥💥💥💥💥💥💥
💥💥💥💥💥💥💥💥💥
ግን...
የዚያን ውድ ነብይ የትውልድ ቦታቸው፣
የእናት አባቱን ስም እንዲሁም አያታቸው፣
በኢስላም ፍና ላይ ያኖሩት አሻራ፣
የትግል ታሪካቸውን ያኖሩትን አደራ፣
ምንስ ከለከሉን ምንስ አዘውናል፣
በሳቸው መንገድጋስ መቼ ተዋውቀናል፣
የፀጉር አቆራረጥ አለባበሳቸው፣
አበላል አጠጣጥ ከነ አተኛኛቸው፣
የሀጅ አደራረግ አሰጋገዳቸው፣
የአቀማመጥ አደብ ስነምግባራቸው፣
ስለነገው ህይወት ስለ አኼራችን፣
መች ለማወቅ ጓጓን አሳስቦን ጉዳችን፣
ስለ ሽርክ ጣጣ ስለ ተውሂድ ጥቅም፣
መች አውቅን ቢድአን የኮተቱን ጥርቅም፣
ዋናውኮ አላማ የተፈጠርክበት፣
ልትገዛው ነበር እርሱን በብቸኝነት።
💥💥💥💥💥💥💥💥💥
💥💥💥💥💥💥💥💥💥
እስኪ ምን አተረፍክ!!
▬▬▬▬▬▬▬
ከመስጅድ ተኳርፈህ አሏህን ከረሳህ፣
የመፈጠርህን ግቡን ከዘነጋህ፣
ከዒልም ማእድ ላይ ጠፍተህ ከሰነበትክ፣
አኼራን ረስተክ በኳስ ፍቅር ካበድክ፣
ሶላትን በወቅቱ መስገድን ከልክሎህ፣
ከፈረንጅ ተጨዋች ከሆነማ ውሎህ፣
ስለኳስ ምንነት ጠንቅቀህ ተረድተህ፣
የረሱልን ፈለግ ከተውከው ዘንግተህ፣
ከኳስ ምን አተረፍክ ከእንስሳት ውሎ፣
የኢስላም ትልቅ ፀጋ በአንተ ላይ ጎድሎ።
“የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) ፍልስጤማውያንን በተመለከተ የመከሩት አስደናቂ ምክር...”
✭✭✭✭✭✭✭✭✭✭
ለተከበሩት ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) የሚከተሉት ጥያቄዎች ቀረበላቸው፡
“በአሁኑ ሰዓት በፍልስጥኤማውያን ወንድሞቻችን ላይ እየተደረገ ያለው መከራና ሰቆቃ...ለነሱ (ለፍልስጤማውያን) ዱዓ ማድረግ፣የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ፣ከነሱ ጋር መታገል ይቻላልን?!”
ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) ምላሽ ሲሰጡ እንዲህ አሉ፦
“በሙስሊሞች ላይ ለሚደርሰው ችግር ዱዓ ማድረግ ግዴታ ነው። በንብረትም ሆነ ቁሳዊ ድጋፍ ማድረግ ግዴታ ነው። ለነሱ የሚጠቅመው ይህ ነው።” ይህንኑ ተከትሎ ለሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው፡
“አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁና ይህ ጠያቂ እንዲህ ይላል፡ “የተለያዩ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግና እንዲሁም ይህ ሰላማዊ ሰልፍ ጂሃድ ከማድረግ ይቆጠራልን?!፤ይህ ሰላማዊ ሰልፍ በአላህ መንገድ ላይ እንደመታገል ይቆጠራልን?!” ከዚያም ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) የሚከተለውን ምላሽ ሰጡ፦
“በሰለማዊ ሰልፍ ምንም አይነት የሚገኝ ጥቅም የለውም፤ይልቅስ ከሰላማዊ ሰልፍ የሚገኘው ትርምስ፣ግርግር፣ረብሻ...ነው። ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ጠላቶችን ምን የሚጎዱት ነገር አለ?! ምንም አይጎዱም። በጎዳናዎች ላይ ሰልፎችን ማድረግ ጣላቶችን የሚያስከፋ ሳይሆን የሚያስደስት ተግባር ነው። ኢስላም የተቀደሰ ንፁህ የሆነ ሐይማኖት ነው፤ እንዲሁም ኢስላም በዘፈቀደና በስሜት የሚያስኬድ ሐይማኖት አይደለም። ኢስላም በሸራዓዊ እውቀት ተመርኩዞ የተገነባ እምነት ነው። ኢስላም የትርምስና የውዝግብ ሐይማኖት አይደለም፤ይልቁንም ለተጎዱ ሙስሊሞች ለነሱ የሚያስፈለገው: ዱዓ ማድረግ፣ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ ማድረግ፣ ወታደራዊ...ድጋፎችን ማድረግ ነው። ስለዚህ በእነዚህም ሆኑ በሌሎች ጉዳዮች ሙስሊሞች የሰለፎችን መንሐጅ ነው መከተል ያለባቸው። ኢስላም በሰላማዊ ሰልፍ ጋጋታና ረብሻ አይደለም እዚህ ደረጃ የደረሠው፤ እንዲሁም ድምፆችን ከፍ በማድረግ፣ ንብረቶችን በማውደም አይደለም ኢስላም የተገነባው። እነኝህ ተግዳሮቶች ለኢስላም ጉዳት እንጂ ምንም አይነት ጠቃሜታ የላቸውም። እነኝህና የመሳሰሉት ተግዳሮቶች ለሙስሊሞች ውጤቱ የከፋ ነው። በል እንዳውም ካህዲያኖች ይደሰታሉ፤ ሙስሊሞችን ጎዳናቸው፣ አሰቃየናቸው...እያሉ ደስታቸውን ይገልፃሉ...”
ምንጭ፦ [From his lesson on the night of the 2nd/Safar/1423H (15 April 2002), in his open meeting after Maghrib prayer, and also broadcast on Paltalk. This was translated from the live lecture at the time.]
Copy
የመውሊድ አንጋሾች
በኢስላም ፈጠራ - ማሳፈሩ ቀርቶ
ቢድአ ጨፈረ - ስፖንሰር አግኝቶ፡፡
የቢድአ ጠበቆች
የሽርክ አቀንቃኞች
የመውሊድ አንጋሾች
ተጓዙ በሰሜን - ዘመቱ በደቡብ
ነጎዱ በምስራቅ - ተመሙ በምእራብ፣
ጠዋፍ አድርገው - ለሙታን መንደር
ሱጁዱን ወርደው - ለሙታኖች ቀብር
ሙታንን ዘይረው - ሙታንን ሊማፀኑ
የኩፍር ስራቸውን - በአመፅ ሊያፀኑ፤
ወደ አፅምነት የተመነዘሩ
ወደ አፈርነት የተቀየሩ፣
የሞቱ ሸሆችን፡-
ሊሉ "ድረሱልኝ - ሀጃዬን ሙሉልኝ
ሌላ መጠጊያም - መሸሺያም የለኝ
ለዱንም-ላኬራም - አንቱ ነሁ ያለሁኝ"፡፡
የነጀማ ንጉስ - የእነ ነጃሺን
የእነገትዬ - የነሸህ ሁሴንን
የነቃጥባሪ - የነሸህ ጎንደሬን
የነአኒይ - የእነዳይን
የእነጊራና - የእነመጂትን
የእነአርከሶ - የነሸህ ዳንግላን
…
የእነእንትና - የእነእንትንዬን
የእነእንትዬ - የእነእንትናዬን…
ደም ተግቶ
ስብ ጠጥቶ
ስጋ አንክቶ
የደለበ አፈር
ከእሾሁ መንደር
ከሸሆቹ ቀብር
እንደ በሶ - በጥብጠው ሊጠጡ
እንደ ጁስ - ጠጥተው ሊያጠጡ፡፡
የመውሊድ አንጋሾች
የቢድአ ጀግኖች
የሽርክ አርበኞች
የሱና ገዳዮች - ሄዱ፣ ገሰገሱ
በቢድአ ቁሻሻ - ሱናን ሊያራክሱ፡፡
የተውሂድ - ገዳይ-አስገዳዮች
የሽርካሽርክ - አንጋሽ-ፈረሰኞች
ባለአድባር-ባለዛሮች
ባለቆሌ-ባለአውጋሮች
ጋለቡ በሰሜን - ተጓዙ በደቡብ
በረሩ በምስራቅ - ተመሙ በምእራብ፤
በሺዎች ከትመው - ከመቃብር አምባ፣
ሰክረው ተሳክረው - በጫቱ ምርቃና
በድቤ ታጅበው - በመንዙማ ቃና
ያለቅጥ ጀዝበው - በ'ስቲጋሳ ሙሀባ
አነጉት ሌሊቱን - በዳንኪራ፣ በጭብጨባ፡፡
በቢድአ አረቄ - ሰክረው ቢሳከሩ
ሱናን ተፀይፈው - ቢድአን ቢያፈቅሩ
ተውሂድን ነቃቅለው - ጣኦትን ተከሉ
የጀነትን ፀጋ - በእሳት ቀይሩ፡፡
✍ በዶክተር አቡ ኡሰይድ
የሃይማኖት ንጽጽር ኮርስ
በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" 9ኛ ዙር የሙቃረናህ ደርሥ!
"ሙቃረናህ" مُقَارَنَة የሚለው ቃል "ቃረነ" قَارَنَ ማለትም "አነጻጸረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንጽጽር" ማለት ነው፥ ሙቃረናህ የሃይማኖት ንጽጽር"Comparative Religion" ሲሆን በእሥልምና እና በክርስትና መካከል ያለው የሥነ-መለኮት አንድነት እና ልዩነት እየተነጻጸረ የሚቀርብበት ጥናት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 7 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሁለት ተርም አለው።
፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ-አሳብ በፈጣሪ እሳቦት ላይ የሚያውጠነጥነው፦
በሥላሴ"trinity" እሳቤ፣
በነገረ-ክርስቶስ ጥናት"Christology"፣
በነገረ-ማርያም ጥናት"Mariology"፣
በነገረ-መላእክት ጥናት"angelology"፣
በነገረ-ምስል ጥናት"Iconlogy" ላይ ነው።
፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በቅዱሳን መጽሐፍት ላይ የሚያውጠነጥነው፦
በአህሉል ኪታብ"People of the Book"፣
በመጽሐፍት"scriptures"፣
በመጽሐፍ አጠባበቅ"preservation"፣
በመጽሐፍት ልኬት"Standardization"፣
በባይብል ግጭት"Contradiction"፣
በኦሪት"Torah"፣
በወንጌል"Gospel" ላይ ነው።
አባሪ ኮርሶች፦
1. ሥነ ምግባር"ethics"
2. ሥነ አመክንዮ"logic"
3. ሥነ ልቦና"psychology"
4. ሥነ ቋንቋ"linguistics" ናቸው።
ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ!
ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu
እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe
አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa
እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa
ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ!
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
Repost from Wolkite University Students' Union
#ማስታወቂያ
#ለግቢያችን_ተማሪዎች_በሙሉ፦
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም የቅድመ-ምረቃ እንዲሁም የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ዓመታዊ የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ (Academic Calendar) ከዚህ በታች የተገለፀ ሲሆን በፕሮግራሙ መሰረት ተገቢውን ዝግጅት ከወዲሁ እንድታደርጉ እያሳወቅን፤ የ2ኛ አመት ተማሪዎች መግቢያ መስከረም 21 እና 22 ሲሆን ከዚያ በላይ ያሉ የግቢያችን ነባር ተማሪዎች የመመዝገቢያ ጊዜ መስከረም 26 እና 27 መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት በየኮሌጃችሁ ሬጅስትራር በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ በጥብቅ እያሳሰብን፤ በሬሚዲያል ት/ት ውጤታችሁን አሻሽላችሁ ያለፋችሁ ተማሪዎች ጥሪ በቅርቡ የሚገለፅ መሆኑን እናሳውቃለን።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
"OUR REWARD IS STUDENTS' HAPPINESS!!!"
የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት ከእኛ ጋር ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም 👉 የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ፌስቡክ 👉የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ድህረ-ገፅ👉የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ለየትኛውም አስተያየት እና ጥያቄ
ቴሌግራም ቦት 👉 @WKUSU_bot
ኢየሱስ
"ነገረ ክርስቶስ"Christology"
ትምህርት በዩቱብ ቪድዮ ተለቋል። መልእክቱ ተደራሽነት እንዲኖረው ላይክ፣ ሼር እና ሰብስክራይብ በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን። ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
https://youtu.be/7oao4CB_JSk
የግብረ – ሶዶማዊነት አደጋ
ግብረ ሶዶማዊነት ማለት የወንድ ለወንድ ፆታዊ ግንኙነት ማለት ሲሆን ይህ ተግባር አላህ እርም ያደረገው ፍፁም የተወገዘ በነብዩላሂ ሉጥ ህዝቦች ላይ መቅሰፍት እንዲወርድ ያደረገ ተግባር ነው ። አላህ የሉጥ ህዝቦችን ያጠፋበት ሁኔታ እንዲ ብሎ ይነግረናል : –
« فَلَمَّا جَاءَ أَمْرُنَا جَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهَا حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ مَّنضُودٍ »
هود ( 82 )
" ትዕዛዛችንም በመጣ ጊዜ (ከተማይቱን) ላይዋን ከታችዋ አደረግን (ገለበጥናት) ፡፡ ተከታታይም የሆነን የሸክላ ድንጋይ በርሷ ላይ አዘነብን ፡፡"
« مُّسَوَّمَةً عِندَ رَبِّكَ ۖ وَمَا هِيَ مِنَ الظَّالِمِينَ بِبَعِيدٍ »
هود ( 83 )
" ከጌታህ ዘንድ ምልክት የተደረገባት ስትሆን (አዘነብናት) ፡፡ እርሷም ከበደለኞቹ ሩቅ አይደለችም ፡፡"
የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም –
" የሉጥ ህዝቦችን ተግባር ሲፈፅም ያገኛችሁት ፈፃሚውም የተፈፀመበትም ግደሉዋቸው " ብለዋል ።
ኢስላም ግብረሶዶማዊነትን በጣም ከትላልቅ አላህ ከታመፀባቸው ወንጀሎች ተርታ ይመድበዋል ። ይህ ተግባር ምእራባዊያን የዲሞክራሲ መብት ነው በሚል የእነርሱ ሸይጧናዊ አስተሳሰብ የሰው ልጆች ከአላህ ትእዛዝ አፈንግጠው የሸይጧን አምላኪና ታዛዥ እንዲሆኑ ለማድረግ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም ። የምእራባዊያን ትልቁ ትኩረት እስልምናን መዋጋት ሲሆን ይህን እውን ለማድረግ የእስልምናን አስተምሮዎችን ለመናድ ሙከራ ማድረጉን ተያይዘውታል ።
በሁሉም ጤነኛ አመለካከት ባለውና ከሰማይ የወረደ ኪታብ አለኝ በሚል እምነት የተወገዘና ንፁህ ልቦና የማይቀበለው ተግባር ስለሆነ ሀገራችን ላይ ሶሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ እሰየው የሚያሰኝ ሲሆን የትኛውም እምነት አለኝ የሚልና ጤነኛ ትውልድ እንዲተካ የሚፈልግ እንዲሁም ሀገርና ህዝብ ከአላህ ከሚመጣው መቅሰፍት ሰላም እንዲሆን የሚመኝ ሊደግፈው የሚገባ ነው ።
እንደሚታወቀው ምእራባዊያን የራሳቸውን ደመ ነፍሳዊ ፍላጎትና አይዲዮሎጂ በአፍሪካ ሀገሮች ላይ በሀይል ለመጫን በኢኮኖሚና በማእቀብ ያስፈራራሉ ።
በቅርቡ የኡጋንዳ ህገመንግስት የዚህ አይነት ተግባር የሚፈፅምን ከሞት እስከ እድሜ ልክ እስራት በሚደርስ ቅጣት ለመቅጣት ህግ በማፅደቃቸው ምክንያት የተለያየ የማእቀብ ጫና እየደረሰበት ነው ። ይሁን እንጂ መንግስቱም ይሁን ህዝቡ የማይበገር አቋም በመያዝ ለሌሎች አስተማሪ የሚሆን ስራ ሰርተዋል ።
ምእራባዊያን ማንኛውም ሰው ፆታውን ወደ ፈለገበት መቀየር ይችላል ። አንድ ሰው በተፈጠረበት ፆታ የመቆየት ግዴታ የለበትም የሚል ህግ አውጥተው ለህፃናት በየትምህርት ቤቱ እንዲህ አይነቱን ዝቅጠት እንዲማሩ አድርገዋል !!!!! ። የእነዚህ የምእራባዊያን እንሰሳዊ አስተምሮ ህዝቦቻቸው ከዚህ በላይ እኛ ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን የመቆየት ግዴታ የለብንም የሚል የአእምሮ ጨለማ ዝቅጥት ውስጥ ከተዋቸው ሶሞኑን አንዱ አሜሪካ ላይ ብዙ ሺህ ዶላር በመክፈል ራሱን ወደ ውሻነት መቀየሩንም ተቀብለው እንደጀብድ ያወሩት ይዘዋል ‼።
ሙስሊሞች ባጠቃላይ በምእራቡ አለም የምትኖሩ በተለይ ራሳችሁንና ልጆቻችሁን የዚህ ተግባር ፀያፍነትና የሚያስከትለው ሁለንተናዊ አደጋ በማስተማርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ከጥፋት መጠበቅ ግድ ይላል ።
የምእራባዊያን የመለኮታዊው መመሪያ የመዋጋት ጥረት በብዙ መልኩ የተለያየ እስራቴጄ በተለያየ ጊዜ በመንደፍ ባጀት መድበው የሰው ሀይል አዘጋጅተው እየቀጠሉበት በመሆኑ ሙስሊሞች ዲናቸውን በማወቅና መመሪያውን በራሳቸው ላይ ተግባራዊ በማድረግ ሊከላከሉት ይገባል ።
አላህ ከምእራባዊያን ሸርና ተንኮል ይጠብቀን ።
Copy
#አስላቃሽ_ምከር (በሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን)
- (ሱንዮች) አትበታተኑ
-ጥፋት ካለ ተመካከሩ
-ራስ በራሲችሁ ህሜትን ራቁ (የወንድማችሁን ስጋ አትብሉ) -----❗️
------
Repost from Wolkite University Students' Union
#ማስታወቂያ
#ለሬሚዲያል_ተማሪዎች_በሙሉ፦
ውድ የሬሚዲያል ተማሪዎች የአጠቃላይ ውጤታችሁን የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ(Link) ተጭናችሁ የመታወቂያ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጥሩ ውጤት እንድታስመዘግቡ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።
ውጤት የምታዩበት ማስፈንጠሪያ(Link)👇
https://www.wku.edu.et/en/index.php/en/57-anouncement/571-remwedial-exam-result
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
"OUR REWARD IS STUDENTS' HAPPINESS!!!"
የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት ከእኛ ጋር ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም 👉 የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ፌስቡክ 👉የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ድህረ-ገፅ👉የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት
ለየትኛውም አስተያየት እና ጥያቄ
ቴሌግራም ቦት 👉 @WKUSU_bot
=አንድ ወንድም አለኝ=
አንድ ወንድም አለኝ ሁሌም ሚናፍቀኝ
ሳስተካክል እሰይ ሳጠፋ ሀይ ሚለኝ
ኧረ ጎሽ! ይለኛል ስራዬ ሲያምር
ኧረ ተው! ይለኛል እንዲሁ ባያምር
እኔንጃ እንደሱማ ከቶውንም አላገኝ
አሁኑኑ ናፈቀኝ ካጠገብ ሣይርቀኝ
ታድያ ፈራሁኮ ያኔ ምን ሊውጠኝ
ካጠገቤ ርቆ በስልክ ብቻ ሲገኝ
ኧረ መላ በሉኝ እሱን ማገኝበት
ካጠገቤ ሲርቅ እሱን እማይበት
ለካ እንዲ ያደርጋል መለያየት ሲደርስ
ያኔ ስንገናኝ እንዳላለን ደስ---ደስ
ቀኑ ደረሰና ምረቃ ሚሉት መርዝ
ወይ እንደስሙ አይሆን ከሚያመጣ መዘዝ
ኧረ ይሄስ አይደለም ምኑነው ምረቃ
እኔን ከወንድሜ ልይ-ይት አድረጎ ቃ
ወይ አንድላይ ያርገን ግቢ እንዳገናኘን
ስራም አለሙላይ እንድኖር ተባብረን
ይህ የኔ ምኞት ነው ከምወደው ጋራ
ለማሣለፍ ደስታ ሀዙኑም በጋራ
=ናፍቀኸኝማ አትቀር!
ናፍቀኸኝማ አትቀር መገናኘት ከሻህ
እንገናኛለን አላህ ካለ ኢንሻአላህ
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ውድ የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ለዚህ አበቃችሁ እያልኩኝ በመቀጠል የመውጫ ፈተናው ያለፈም ያላለፈም እንደሚመረቅ የታወቀ ነው ስለሆነም ሰበቡን እስከጥግ (አንዳንዶቻችንማ ተወኩል የሌለን እስኪመስል) ድረስ ስላደረስን የመጣውን በፀጋ በመቀበል ለቀጣይ በርትተን መገኘት ይኖርብናል ለማለት እወዳለሁ!
አካዉንታቹን ታደጉ !!!!!
ከላይ በመጀመሪያ ፎቶ የምትመለከቱት የ200 ብር ኖት ፎቶ የያዘ እና ቻናሉን ሰብስክራይብ አድርጉ የሚለዉ ሚሴጅ ከተላከላቹ በምንም አይነት መልኩ እ ን ዳ ት ሞ ክ ሩ !!!!
በመጀመሪያ ወደ chrome ይወስዳቹና የቴሌግራም አካዉንታቹን login አስደርጓቹ የ login code ያስልክና ኮዱን ስታስገቡ በቃ ተበላቹ!!!! አካዉንታቹ ሀክ ይደረግና ያንኑ የዉሸት ሚሴጅ ስልካቹ ዉስጥ ወዳሉት ግሩፕ ቻናልና አካዉንቶች በሙሉ ይበትናል ስልካቹ ከቁጥጥራቹ ዉጪ ይሆናል !!!!
ነገር ግን ተበልታችሁ ከሆነ በሁለተኛ ላይ በለጠፍኩት ፎቶ መሠረት ወደ setting ትገቡና Device ወደሚለዉ ገብታቹ ፎቶ ላይ ያከበብኩበትን ተጭናቹ በአፋጣኝ Terminate አርጉት አለበለዚያ አካዉንታቹ በአጭበርባሪዎች እጅ ይዘልቃል!!!!!
በተረፈ ሌሎችንም ለማስጠንቀቅ ይሄን መልዕክት ሼር አርጉ የበኩሌን ተወጥቻለሁ።
🗣 الآ فاليبلغ الشاهد الغائب
https://t.me/daewaselefiyaArbaminch/14072
✅ የጁምዓ ቀን ሱናዎች
❶ኛ ገላን መታጠብ።
➋ኛ ሽቶን መቀባባት እና መዋብ።
❸ኛ ሲዋክን መጠቀም።
❹ኛ የክት ልብስ መልበስ።
❺ኛ በጊዜ መስጂድ መጓዝ።
❻ኛ በእግር እየተጓዙ ወደ መስጅድ መሄድ።
❼ኛ መስጂድ ከደረሱ በኋላ የሰዎችን ትከሻ በመረማመድ ሰዉን አለማስቸገር።
❽ኛ ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ቢሆንም ተህየቱ መስጂድ መስገድ።
❾ኛ ኹጥባ ወደ የሚያደርገው ኢማም መዞርና እሱን እያዩ ኹጥባ ማድመጥ።
❿ኛ ኹጥባ በሚደረግበት ሰዓት ፀጥታን መላበስ።
⓫ኛ ሰደቃን ማብዛት።
⓬ኛ ከሀሙስ ማታ ጀምሮ እሰከ ጁምዓ ዐስር ድረስ ሱረቱ ከሕፍ መቅራት።
⓭ኛ ዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሰዓትን መጠባበቅ።
⓮ኛ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን በብዛት ማውረድ።
منقولሪዝቅ ያጣህበት፣ ከድህነት መላቀቅ የተሳነብህ፣ በፍርሃት እንድትዋጥ የሚያደርግህ፣ ልብህ እንዲደርቅ፣ የኢማንን ጥፍጥና እንድታጣ የሚያደርግህ፣ በቤትህ ውስጥ በገንዘብህም ጭምር በረካ እንዳይኖርህ የሚያደርግህ፣ ዒባዳህ ስትፈጽም ጣዕሙን እንድታጣ የሚያደርግህ፣ ለሐጅና ዑምራ እንዳትናፍቅ የሚያደርግህ፣ ግዴለሽ የሚያደርግህ… ዋነኛው ምክንያት ምን እንደሆነ ታውቃለህ⁉️
በድብቅ የምትሠራቸው ወንጀሎች ናቸው።
አላህን በድብቅ እንደከዳኸው ሁሉ እርሱ በይፋም በድብቅም ይከዳሃል። ስውር ወንጀልን ስትተው እነዚህን ያጣሃቸውን ነገሮች ሁሉ በአላህ ፈቃድ ታገኛለህ።
أكبر سبب لانقطاع الرزق والفقر والخوف وقسوة القلب وعدم البركة في بيتك ومالك وراتبك شاهد ماهو
Copy
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
የተፈጥሮ ሳይንስ የምትማሩ የሪሚድያል ወንድሞችና እህቶች ነገ የባዮሎጂ ፈተና እንዳለባቹ ይታወቃልና ከፈተና መግቢያ ሰዓት ጋር በተያያዘ የጁመዓ ሰላት ጥያቄ ከተፈጠረባቹ ሰግዳቹ በፍጥነት በመመለስ መግባት እንደምትችሉ ለማስታወስ እንወዳለን!
💥 ወደ ጀነት የሚያደርሱ (( 15 )) መንገዶች !!
ይህንን ጠቃሚ መልዕክት SHARE ያድርጉ::
1,👉 በአላህ አንዳችም ነገር ሳያጋራ ከአላህ የተገናኘ ሰው ጀነት ገባ፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
2,👉 በአላህ እና በመልዕክተኛው ያመነ፣ ሶላትን በትክክል የሰገደ፣ ረመዳንን የጾመ አላህ
ጀነት ሊያስገባው ግድ ነው፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
3,👉 የአላህን ውዴታ ፍለጋ መስጂድ የገነባ ሰው አላህ በጀነት ውስጥ ተመሳሳይ ቤት
ይገነባለታል፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
4,👉 ጠዋትም ሆነ ማታ ወደ መስጂድ የሚመላለስ ሰው በተመላለሰ ቁጥር አላህ በጀነት
ውስጥ ማረፊያ ያዘጋጅለታል፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
5,👉 በቀንና ሌሊት ውስጥ አሥራ ሁለት ረከዓዎችን (ሱና) የሰገደ ሰው በነሱ ምክንያት
በጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል፡፡ (ሙስሊም ዘግበውታል፡፡)
6,👉 አንድ ሰው ዉዱኡን አሳምሮ አድርጎ በሙሉ ሀሳቡን አሰባስቦ ሀሉት ረከዓዎችን
አይሰግድም ጀነት የፀናችለት ቢሆን እንጂ፡፡ (አቡ ዳዉድ እንደዘገቡት)
7,👉 ‹አላህን በጌትነት፣ እስልምናን በሃይማኖትነት፣ ሙሐመድን በነቢይነት ወደድኩ፡፡› ያለ
ሰው ጀነት ፀናችለት፡፡ (አቡ ዳዉድ ዘግበውታል፡፡)
8,👉 የመጨረሻ ቃሉ ‹ላ ኢላሀ ኢልለላህ› የሆነ ሰው ጀነት ገባ፡፡ (አቡ ዳዉድ ዘግበውታል፡፡)
9,👉 ለአላህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት፡፡ ለመቶ አንድ ሲቀር፡፡ እነሱን ጠንቅቆ ያወቃቸው
ጀነት ገባ፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
10,👉 ‹ተቀባይነትን ያገኘ ሐጅ ምንዳው ጀነት ብቻ ነው፡፡› (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
11,👉 እኔና የቲምን የሚንከባከብ ሰው ጀነት ውስጥ እንዲህ ነን፡፡ (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
12,👉 ሰዎች ሆይ ሰላምታን አብዙ፣ ምግብ አብሉ፣ ሰዎች በተኙበት የሌሊት ሰዓት ስገዱ፡፡
ጀነትን በሰላም ትገባላችሁ፡፡ (ቲርሚዚ ዘግበውታል፡፡)
13,👉 ‹ሰዎችን በብዛት ጀነት የሚያስገባው የአላህ ፍራቻና መልካም ሥነምግባር ነው፡፡
…› (ቲርሚዚ ኢብኑ ማህ እና አሕመድ)
14,👉 እኔን የታዘዘ ጀነት ገባ፡፡ እኔን እንቢ ያለ በርግጥ አመፀ፡፡› (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
15,👉 ከያንዳንዱ ሶላት በኋላ ‹ኣየት አልኩርሲይን› የሚያነብ ሰው በርሱና በጀነት መካከል
የሚጋርደው ሞት ብቻ ነው፡፡ (ነሳኢ እና ኢብኑ አስሱንኒይ እንደዘገቡት)
#ሪሜዲያል
ትምህርት ሚኒስቴር ከአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፈተና ጋር በተያያዘ ምን ውሳኔ አስተላለፈ ?
ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፈተና አሰጣጥን በተመለከ ትላንት ሰኞ ምሽት ከፕሬዚደንቶችና የተቋማት ሃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኃላ ከፈተናው ጋር በተያያዘ ውሳኔ ማስተላለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው አካል ለማወቅ ችሏል።
በዚሁ የትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ የሬሜዲያል ፈተና አሰጣጥ በሚከተለው መልኩ እንዲከናወን ተወስኗል።
- በ26/10/2015 የተሰጡት የሬሜዲያል ፕርግራም ፈተናዎች #ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ እንዲደረግ ተወስኗል።
- ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ተሻሽሎ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ #ካምፓስ ያላቸውን #የግል_ከፍተኛ_ትምህርት ተቋማት ፈተና ወደ ፊት ቀርቦ በሚወሰን አግባብ ፈተናው በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እንዲሰጥ እንዲደረግ ተወስኗል።
- በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑትን ተማሪዎች ፈተና መስጠቱን ወደ መስከረም ወር ማስተላለፉ በተማሪዎችና በተቋማት ላይ የሚያሳድረውን ጫና ከግምት በማስገባት የተዘጋጁትን ፈተናዎች በመለወጥ ፈተናዎች ኢንክሪፕትድ ሆነው ለዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንቶች ደርሰው እንዲባዙና ሁሉም ፈተናዎች በተመሳሳይ ጊዜ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ እንዲሰጡ እንዲደረግ።
- የፈተና ጥያቄዎች ለዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንቶች ከመድሳቸው በፊት ተማሪዎች #ከቀኑ_6 ሰዓት ላይ ተፈትሸው ወደ መፈተኛ አዳራሽ ገብተው ፈተናውን እንዲጠባበቁ በማድረግ እንዲፈፀም ውሳኔ ተላልፏል።
ተቋማት ከትምህርት ሚኒስቴር በተላከላቸው ውሳኔ መሰረት ተማሪዎቻቸው #ከቀኑ_6 ሰዓት ተፈትሸው ወደመፈተኛ ክፍል ገብተው ፈተናውን እንዲጠባበቁ መልዕክት እያስተላለፉ እንደሚገኙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከየተቋማቱ የደረሰው መልዕክት ያስረዳል።
#TikvahFamily
More : @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
