cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሙከሚል የንፅፅር ቤተ መጽሐፍ

https://t.me/mukamil የዪቲዩብ ቻናሌን ሰብስክራይብ ያድርጉ👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@Mukamil123

Show more
Advertising posts
2 674Subscribers
No data24 hours
+287 days
+15030 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

🤣 9👍 3😁 2🤪 2🤯 1
◆▮ውይይት▮◆ 📌  ሥላሴ የባይብል አስተምህሮ ነውን?! 📌 ሥላሴ ቃሉም ሆነ ቃሉን የወከለው ሐሳብ በባይብል ይገኛልን?! ◍ ወንድም ኢብራሂም           🆅🆂 ◍ ወገናችን ፓስተር አቡከር
Show all...
👍 2
የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ነቢይነት ክፍል 4 በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በሆነው! وَيَقُولُ الَّذِينَ كَفَرُوا لَسْتَ مُرْسَلًا ۚ قُلْ كَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا بَيْنِي وَبَيْنَكُمْ  [ ሱረቱ አል- ረዕድ፥ - 43 ] እነዚያም የካዱት ሰዎች «መልክተኛ አይደለህም» ይላሉ፡፡ «በእኔና በእናንተ መካከል መስካሪ በአላህ በቃ በላቸው። ወዳጄ ሁሌም እንደምለው ስለ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ነቢይነት ለማወቅ በመጀመሪያ እነዚያ በጥላቻ የተሞሉ የውሸት ጓንዳዎች ያጠለቁልህን የሻገተ መነጽርህን አውልቀህ ጣለውና ረጋ ሰከን ባለ ስሜት በጥንቃቄ አጥና! ያኔ እውነቱ ፍንትው ብሎ ታገኘዋለህ። በክፍል ሦስት ቅኝታችን ቁርአንን ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ከአለማቱ ጌታ ከአላህ ዘንድ የተቀበሉት መሆኑን ቁርአኑንም ከተቀበሉ በኋላ ቁርአን የፈጣሪ ቃል አይደለም የሚሉ ሰዎችን እንግዲያስ ቁርአን የፈጣሪ ቃል ሳይሆን የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ድርሰት ነው ካላችሁ እስቲ እናንተም የቁርአንን አምሳያው አምጡ ብሎ (ተሐዲ) አቅርቦላቸው ማምጣት አለመቻላቸውን አይተን ነበር። ይህም የሚያሳየው አንድም ቁርአን እውነተኛ የፈጣሪ ቃል መሆኑን ቁርአንን የተቀበሉት ነቢይ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) እውነት የፈጣሪ ነቢይ መሆናቸውንና ቁርአን ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ከተሰጣቸው ትላልቅ ተአምራት ዋነኛው መሆኑን ያሳያል። አንድ ነቢይ ለእውነተኛ ነቢይነቱ እንደ ማስረጃ ሆነው ከሚቀርቡ ነገራቶች ውስጥ አንዱ ተአምር ማሳየት እንደሆነ ይታወቃል። ነቢዩ ሙሐመድም (ሰዐወ) እውነተኛ የፈጣሪ ነቢይ እንደመሆናቸው የተሰጣቸው ተአምር ቁርአን ብቻ ሳይሆን ብዙ ናቸው። እስቲ ዛሬ ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ከፈጣሪ ዘንድ ከተሰጣቸው ከቁርአን ቀጥሎ ካሉ ትላልቅ  ተአምራት ውስጥ አንዱን እንመልከት። ነቢያች ነቢይ ሆነው በተነሱበት ጊዜ የቁረይሽ ሰዎች ነቢዩ ሙሐመድን እስቲ አንተ እውነተኛ የአላህ ነቢይ ከሆንክ ተአምር አሳየን አሉት ነቢዩ ሙሐመድም ጨረቃን ለሁለት በመካፈል ትልቅ ተአምር አሳይቷቸዋል። اقْتَرَبَتِ السَّاعَةُ وَانشَقَّ الْقَمَرُ (ሱረት አል-ቀመር - 1) ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ ጨረቃም ተገመሰ፡፡ أَنَّ أَهْلَ مَكَّةَ سَأَلُوا رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم أَنْ يُرِيَهُمْ آيَةً، فَأَرَاهُمُ انْشِقَاقَ الْقَمَرِ‏. አነስ ኢብኑ ማሊክ (ረ.ዐ) እንደተረከው የመካ ሰዎች የአላህን መልዕክተኛ (ﷺ) ተዓምር እንዲያሳዩአቸው ጠየቁት፣ እሳቸውም ጨረቃን ለሁለት በመክፈል አሳያቸው። (📚 ቡኻሪ መጽሐፍ 61, ሐዲስ ,141) በሌላም ዘገባ እንዲህ ተዘግቧል! ኢብኑ ሙጥዕም ከአባቱ ይዞ انْشَقَّ الْقَمَرُ عَلَى عَهْدِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم حَتَّى صَارَ فِرْقَتَيْنِ عَلَى هَذَا الْجَبَلِ وَعَلَى هَذَا الْجَبَلِ فَقَالُوا سَحَرَنَا مُحَمَّدٌ فَقَالَ بَعْضُهُمْ لَئِنْ كَانَ سَحَرَنَا مَا يَسْتَطِيعُ أَنْ يَسْحَرَ النَّاسَ كُلَّهُمْ በነቢዩ ዘመን ጨረቃ በዚህ እና በዚያ ተራራ ላይ ሁለት እስክትሆን ድረስ ተሰንጥቃ ታየች፣ ቁረይሾችም ‟ነቢዩ በእኛ ላይ አስደግሞብን ነው” አሉ፣ ከፊሎቹ ደግሞ ‟በእኛ ላይ አስደግሞብን ከሆነ ሁሉም ሰው ላይ ማስደገም አይቻለውም” አሉ። (📚ትርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ, 341) ተጨማሪ ማስረጃ ከፈለክ ! Sahih al-Bukhari, 3868 Sahih al-Bukhari, 4867 Sahih Muslim, 2802 Sahih Muslim, 2803 ወዘተ... ተመልከት ታላቁ አሊም ኢብኑ ከሲር ይህን ሐዲስ ሲያብራራ እንዲህ ብሏል! انشقَّ القمرُ بمكةَ حتى صار فرقتَينِ فقال كفارُ قريشٍ لأهلِ مكةَ هذا سحرٌ سحرَكم به ابنُ أبي كبشةَ انظروا  السُّفَّار فإن كانوا رأوا ما رأيتُم فقد صدق وإن كانوا لم يرَوا مثلَ ما رأيتُم فهو سِحرٌ سحركم به قال فسُئل ا السُّفَّارُ قال وقدِموا من كل وِجهةٍ فقالوا رأَينا. በመካ ጨረቃ ሁለት እስክትሆን ድረስ ተከፈለች፣ የቁረይሽ ካፊሮች ለመካ ነዋሪዎች ይህ ኢብኑ አቢ ከበሻ (ሙሐመድ) ያስደገመባችሁ ድግምት ነው፣ ከውጪ የሚመጡትን ተጓዢዎች ስለ ነገሩ ጠይቁአቸው፣ እናንተ የተመለከችሁን ነገር እነርሱም ከተመለከቱ በእርግጥም እውነት ነው፣ ያልተመለከቱ ከሆነ ደግሞ ድግምት ነው አሏቸው። ከዚያም ከሁሉም አቅጣጫ የመጡትን ተጓዦች ጠየቁ እነርሱም ‟አዎ አይተናል” ብለው መሰከሩ። (📚አል-ቢዳያ ወኒሃያ ለኢብኒ ከሲር 3/119) ይህ ክስተት እንዲሁ ተረት ተረት ሳይሆን በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በስጋ ዓይናቸው የተመለከቱት ክስተት ነው። ወደ ዋናው ነጥቤ ስመለስ አንድ ሐሰተኛ ነቢይ ጨረቃን የሚያክል ግዙፍ ፍጥረት ለሁለት መካፈል ይችላልን?? በጭራሽ አይችልም። ታዲያ ነቢዩ ሙሐመድ ይህን ማድረግ እንዴት ቻሉ? መልሱን ለራስህ!! [[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[ [[ይቀጥላል,, ኢንሻ አላህ   ]] [[                                   ]] [[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[[ ✍ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ https://t.me/mukamil12
Show all...
ሙከሚል የንፅፅር ቤተ መጽሐፍ

https://t.me/mukamil

የዪቲዩብ ቻናሌን ሰብስክራይብ ያድርጉ👇👇👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/@Mukamil123

👍 13 3
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ ያ ጀመዓህ! "የተደበቀው እውነት" የሚለው ስድስተኛው መጽሐፌ በገበያ ላይ ውሏል። "የተደበቀው እውነት" የሚያውጠነጥነው ስለ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት በተውራት እና በኢንጂል ተነግሮ የመጽሐፉ ሰዎች ይህንን እውነት እንዴት እንደደበቁት የሚገልጥ እና የሚያጋልጥ ነው። ዝርዝሩን መጽሐፉ ላይ ያንብቡ እና ለሎች የሂዳያህ ሠበብ እንዲሆን አስነብቡ! መጽሐፉን መርካርቶ አንዋር መሥጂድ ኢሥላማዊ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል፥ የበለጠ ለመረጃ +251920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ! መጽሐፉ ተደራሽነት እንዲኖረው ባለው የማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ! ወጀዛኩሙላህ ኸይራ! ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom
Show all...
👍 14
قال أحمدُ بنُ محمَّدِ بنِ حَنبَلٍ رحمه اللهُ: لقيتُ الرِّجالَ، والعُلَماءَ، والفُقَهاءَ، بمكَّةَ والمدينةِ والكوفةِ والبَصرةِ والشَّامِ والثُّغورِ وخُراسان، فرأيتُهم على السُّنَّةِ والجماعةِ، وسألتُ عنها الفُقَهاءَ؟ فكُلٌّ يقولُ: القُرآنُ كلامُ اللهِ، غيرُ مخلوقٍ، منه بدأ، وإليه يعودُ [📚እኽቲሷሱል ቁርአን 1691]
Show all...
4
ኤጲስ ቆጶስ ማር ማሪ ኢማኑኤል ማን ናቸው?
Show all...
1