cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

State of all Amhara

Show more
Advertising posts
405
Subscribers
-424 hours
-77 days
-2130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

⭐️⭐️⭐️💡ዓውደ ፋኖ💡⭐️⭐️⭐️ 🫵 🫵 "#አይበገሬው ሰሜናዊ ኮከብ" ዝና፣ እና ክብር ዓለም ዓቀፍም ሽልማት በተገቢው ስፍራ እና ቦታ፣ በፍትሃዊ ማደሪያው ይገኝ ዘንድ ምድሪቷ በሀቅ መንገድ ብትራመድ ይሄን ብርቱ ከዐለት የጠነከረው #ሰው የሚያልፈው አንዳች ክብረ ሞገስ ባልኖረ… #ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ… አዎ፣ ስለርሱ ላወራችሁ ነው። የዛሬው የዓውደ ፋኖ ገፅ እንግዳዬ ነው። ስለዚህ፣ መንጋ እና ቲፎዞ አልባ ታጋይ ጥቂት ልል ብችል እንጅ… የዘመኑን ምልዐት፣ የትውልድ ውርስ በደም ዋጋ የታጀበ በሰቆቃ አመታት ውስጥ የተሻገረ፣ ዛሬው በተጋድሎ ዐውድ ላይ ስለሚገኘው መራራ መርህ መር ታጋይነቱን በዚህች ቅፅበት አትቼ አልጨርሰውም። እርሱ ግን፣ ፍፁም ትሁት ነው። እጁን ጨብጦ ከፍ በማድረግ "ትግልን ከኔ በላይ ለዐሳር" ሲል አታዩትም። ሲበዛ አይን አፋር እና የደግነት ባለ ፀጋ ነው። በጋዜጠኝነት ደሞዙ… 4 በኦሮሚያ ቤተሰቦቻቸው በግፍ የተገደሉባቸው ወላጅ አልባ ህፃናትን ያሳድጋል፣ እጅ ሲያጥረው በስሙ ይለምንላቸዋል። ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ ያልተገለጠ መፅሀፍ ነው። ይህ፣ ሰው… ለውጥ የተባለው ጎርፍ ገፍቶ ያመጣው ሰሞነኛ ፖለቲከኛ፣ የዩቲዩብ አማላይ ክፍያ ወደ ሜዳ ያወጣው ጋዜጠኛም አይደለም። ከዚህ በታች… የማወጋላችሁ በጀብዱ የተሞላው ታሪከ ማስታወሻው… ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ ያልተዘመረለት ካባ ያልደረብንለት ፣ የሰራን ቆፍረን አክባሪ ያለመሆናችንን ያሳብቅብናል። አባይ ዘውዱ… ሰሜናዊ ነበልባል #ፋኖ ኮከባችን… በኦህዴድ መራሹ የብልጽግና አገዛዝ ዳግም በግፍ እስር ላይ የሚገኘው ዓባይ ዘውዱ ማን ነው⁉️ ስለ ዓባይ ዘውዱ አጠር ያለ መረጃ ለማጋራት ወደናል። ዓባይ ዘውዱ ደመቀ የተወለደው በድሮው አጠራር በሰሜን ጎንደር ዞን በጭልጋ ወረዳ ዳዋ ዳንጉራ ልዩ ስሙ መንደር ጊዮርጊስ በተባለ ለማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ አዋሳኝ በሆነውና መዳረሻውን ሱዳን ድረስ ያደረገው የጓንግ ወንዝ በሚለዬው ቀበሌ ነው። ዓባይ ምንም እንኳ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ይወለድ እንጅ እድገቱን ያደረገውና እስከ 6ኛ ክፍልም የተማረው በድሮው አጠራር ታች አርማጭሆ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለአስተዳደር ያመች ዘንድ በሚል ማዕከላዊ አርማጭሆ ተብሎ ራሱን በቻለው ወረዳ ማሰሮ ደንብ ነው። ዓባይ በልጅነቱ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ የተወሰደው አባቱ አቶ ዘውዱ ደመቀን እና ቤተሰቦቹን "ለለውጥ እየታገሉ ነው፣ እምቢተኛ ናቸው፣ እየተገዙን አይደለም" በሚል ደርግ አባቱን ወደ ጭልጋ አፍኖ በመውሰድ ማሰር እና ማንገላታቱን ተከትሎ ነው። በወቅቱ ዘውዱ ደመቀ ብቻ አልነበረም ከመንደር ጊዮርጊስ ቀበሌ የታፈነው ምንም እንኳ ከአጭር ጊዜ የእስር ቆይታ በኋላ ከዳንጉራ እስር ቤት የተለቀቁ ቢሆንም አባቱ ደመቀ ሁነኛው፣ ታላቅ ወንድሙ መልካሙ ደመቀ እና ታናሽ ወንድሙ ጌጡ ደመቀም አብረው ታስረው ነበር። ዘውዱ ደመቀ ግን 'ይህ ነው ዋናው' በሚል ተፈርጆ ወደ ጭልጋ ወረዳ አይከል ማ/ቤት ተወስዶ ከ6 ወራት የግፍ እስር በኋላ መፈታቱን ተከትሎ ነው ባለቤቱን ባንች አምላክ በለጠን እና ልጆቹን ይዞ የጓንግን ወንዝ ከማዶ እና ማዶ ሶስትና አራት ረዣዥም እንጨት ጣል በማድረግ በሰራው ጊዜያዊ መሻገሪያ ድልድይ ተሻግሮ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ያቀናው። የመጀመሪያ ወይም የበክር ልጅ የሆነው ዓባይ ዘውዱ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ተወልዶ በአርማጭሆ ማሰሮ ደንብ ወረዳ ሳንኪ ሚካኤል ነው እድገቱን ያደረገው። ዓባይ የተወለደበት ብቻ ሳይሆን ያደገበት አካባቢም በአብዛኛው በተራራ ሰንሰለት እና በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ ነው። ዓባይ የት ተማረ? የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስከ 6ኛ ክፍል የተከታተለው በማሰሮ ደንብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን የ7ኛ ክፍል ትምህርቱን ደግሞ በታች አርማጭሆ ወረዳ ሳንጃ ት/ቤት ነው። ዓባይ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የተከታተለው በባህር ዳር ነው። ይኸውም፦ 1) 8ኛ ክፍል_በባህር ዳር ቁልቋል ሜዳ ት/ቤት፣ 2) 9ነኛ እና 10ኛ ክፍል_በባህር ዳር ፋሲሎ ት/ቤት፣ 3) 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን በባህር ዳር መሰናዶ ት/ቤት እንዲሁም 4) የዩኒቨርስቲ ትምህርቱንም በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፔዳ ካምፓስ የተከታተለ ሲሆን በጋዜጠኝነትና ግንኙነት (Journalism and Communications) ትምህርት ዘርፍ 3.66 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ እና በሽልማት ተመርቋል። የትግል ሁኔታን በተመለከተ? በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ በመድረክ እና በጽሁፍ ሲያደርገው የነበረው ትግል እንዳለ ሆኖ በዋናነት ከ2005 ዓ/ም ጀምሮ ነው የህወሀት እና ህወሀት ተሸናፊ እና ተንበርካኪ አድርጎ የሰራውን የብአዴን ስርዓትን አምርሮ በመጥላት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)ን ተቀላቅሎ ታግሏል። በተለይ በህወሀት በሀይል ከአማራ የተወሰደው የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ እንዲሁም በሱዳን በጎንደር በኩል የሀገር ሉኣላዊነት ተደፍሮ የተወሰደው ሰፊ ለም መሬት እና በተለያዩ አካባቢዎች በአማራ ህዝብ ላይ ይደርስ የነበረው ሁለንተናዊ ግፍ እና በደል ወደ አንድነት ትግሉ በመግባት ከብርቱ ለውጥ ፈላጊ እና የነቁ ጓደኞቹ ጋር በመሆን በአብርሃጅራ ከተማ ቢሮ በመክፈት ጭምር አገዛዙን እንዲታገል ገፋፍቶታል። በለውጥ ትግሉ መስዋዕት ከሆኑት ነፍሳቸውን ይማርና ከእነ ደስታው ተገኘ፣ አንጋው ተገኘ እና ታናሽ ወንድማቸው ባበይ ተገኘ ጋር በመናበብ አገዛዙን ይታገል ነበር። ደስታው ተገኘ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ አገዛዙን ለመታገል ሲመለስ በአብደራፊ/ምድረገነት አካባቢ ባጋጠማቸው ውጊያ ዶ/ር ብርሃኑ ከተባለ የትግል ጓዱ ጋር ስለ አማራ ህዝብ እና ስለ ሀገር ሲል በጀግንነት በክብር የተሰዋ ሲሆን ወንድሞቹ አንጋው ተገኘ እና ታናሻቸው ባበይ ተገኘ ደግሞ እምብኝ ለወገኔ በማለት በመጋቢት 2016 ዓ/ም ኦህዴድ መራሹን የብልጽግና አገዛዝ በነፍጥ ሲፋለሙ በክብር የተሰው ጀግኖች ናቸው። ዓባይ ከእነ እንግዳው ዋኘው፣ ስርዓቱ ለሰላማዊ ትግል ዝግጁ አይደለም በማለት ወደ ኤርትራ በማቅናት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን ተቀላቅለው ሲታገሉ ከነበሩት ከእነ አብርሃም ልጃለም፣ ከአለልኝ እና ከሌሎችም ጋር በመሆን በምዕራብ ጎንደር ዞን አብርሃጅራ ሲታገሉ ነበር። ከእነ አለላቸው አታለል፣ ቀለብ ስዩም፣ ተገኘ ሲሳይ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ ፈረጃ ሙሉ፣ ሰጠኝ ቢልልኝ፣ አወቀ፣ እንዲሁም ከአነ አግባው ሰጠኝና ከሌሎች ጀግኖች ጋርም በመናበብ አብሮ ለእውነተኛ እና ስር ነቀል ለውጥ ይታገል ነበር። ዓባይ ዘውዱ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ሲታገል ስለደረሰበት እስር፦ (1) በህወሀት ኢህአዴግ ዘመን ከጥቅምት 25/2007 ጀምሮ እስከ ህዳር 2010 ድረስ በፈጠራ የሽብር ክስ 4 ዓመት ከ2 ወር ተፈርዶበት ታስሯል። በአብርሃጅራ፣ በጎንደር 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣በባህር ዳር 9ነኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ በአዲስ አበባ ማዕከላዊ፣ በቂሊንጦ፣ በሸዋሮቢትና በዝዋይ በእስር ተሰቃይቷል። (2) በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ደግሞ ስለ ሰፊው የአማራ ህዝብ እና ስለተገፉ ወገኖች ድምፅ በመሆኑ 4 ጊዜ ታስሯል። ይኸውም፦ 1) ሀምሌ 10/2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ አውቶብስ ተራ እና በመርካቶ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስለምን ለአማራ ተፈናቃዮች ድምጽ ሆንክ በሚል ታስሯል።
Show all...
2) ጳጉሜ 3/2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአባ ሳሙኤል ታስሯል። 3) መጋቢት 28/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ) ታስሯል። 4) ነሃሴ 4/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ፣ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ እና በቂሊንጦ ታስሯል፤ በአማራዊ ማንነቱ እና በጋዜጠኝነት ሙያው ለህዝብ ድምፅ በመሆኑ እና ስር ነቀል ስርዓታዊ ለውጥ እንዲመጣ በመታገሉ አሁንም በግፍ እስር ላይ ይገኛል። ዓባይ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ-ደቡብ እዝ መከላከያ ካምፕ ለ6 ወራት ያህል በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ታግቷል፤ በሜክሲኮ የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮም ከ2 ወራት በላይ ከሌሎች የአማራዊ ማንነት ታጋቾች ጋር በሩ እንዲዘጋ ተደርጎ ታስሯል፤ ከሜክሲኮ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተዛውሮም ታስሯል። ዓባይ አሁን ላይ የፈጠራ የሽብር ክስ ተመስርቶበት በቂሊንጦ እስር ቤት ይገኛል። 4 ዓመት ከ6 ወራት በላይ በታች አርማጭሆ እና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች በባህል እና ቱሪዝም የፕሮሞሽን ባለሙያነት እንዲሁም በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገለው ዓባይ ዘውዱ ህዳር 1/2010 ዓ/ም ከዝዋይ ማ/ቤት ተፈታበት ጊዜ ጀምሮም በጋዜጠኝነት ሙያው በሽብር ተግባር የተሰማራውንና የህወሀት ኢህአዴግ ተቀጥላ የሆነውን የኦህዴድ ብልጽግን አገዛዝና የስሪቱን ገመና በማጋለጥ ጭምር እየታገለ ይገኛል። ዓባይ ዘውዱ እና ቤተሰቦቹ ስለ እውነተኛ ለውጥ በሚል ኢሰብአዊነትን በመቃወም የከፈሉት መስዋዕትነት ከባድ ነው። በማንኛውም ስርዓታዊ ፈተና ሁሉ ከጎኑ የቆሙ ወገኖችን በሙሉ በእጅጉ ያመሰገነው ዓባይ ህዝባዊ ትግል ማሸነፉ አይቀርም ይሏል። ፍትሃዊ የሆነው የአማራው የህልውና፣ የነፃነት፣ የክብር፣ የእኩልነት እና የአብሮነት ትግል ያሸንፋል! ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት ይሁን! ፍትህ ለሁሉም! #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

Photo unavailableShow in Telegram
ትውልዱ እንዳይሳሳት‼️ በ2010 ዓ.ም በደም ዋጋችን የጠራነው ለውጥን፣ ለፋሽት ኦሮሞ ገዳዮች በሆዱ ሸጦ የደማችን ጎርፍ ይፈስስ ዘንድ የተወን፣ ብዐዴን እንጅ ሌላ አልነበረም፣ አይደለምም። ያኔ… ብዐዴን = አብን እና አዴፖ በሚል ጭንብል ተሸፍኖ ሲመጣ…የናፈቅነውን ነፃነትና ፖለቲካዊ እጣ ፋንታችንን ይወስን ዘንድ ከጌቶቹ ጋር ያሰለፍነው ጊዜ…ተሳሳትን። ብዐዴን… መልክ እና ቅርፁን፣ ስምና መሪ መሳዮችን፣ ኢጎ እና ሀብት፣ ወረቀት የሰበሰቡና ምላሰኞችን ከፊቱ እያስቀደመ ስንቴ ደጋግሞ ከዳን፣ ስንቴ ደጋግሞ ወጋን፣ ስንቴ ደጋግሞ አደማን፣ ስንቴ ደጋግሞ አቆሰለን! ዛሬም… የህልውናችንን ትንቅንቅ… የእጣ እድላችን ወሳኝ የሆነውን የፋኖ ትግል ለመጥለፍ የመጣበት መንገድ አስፈሪም፣ አስደንጋጭም፣ አስጊም እየሆነ ነው። ሚዲያው፣ በባዕዴናዊ ኩሊ እና ጎጠኞች እየተወረረ ነው። በወያኔ ቅጥረኛ ባለ አጀንዳዎች አየሩ እየተሞላ ነው። አላዋቂ ታዋቂዎች፣ በፋኖ ትግል ተጠቅልለው ለፍርድ የምንፈልጋቸው ወንጀለኛችን በክብር መስኮት ይዘው እየመጡ ነው። ትውልዱ፣ እንዳይሳሳት! ይህ እድልን ለብዐዴናውያን ከመስጠት ለጥቆ የሚመጣ ሌላ ጭላንጭል ተስፋ የለም። "ብዐዴን ጅብ ነው" ለሆዱ እና ጥቅም ሟች… በእርሱ አንገት እና ትክሻ ጭነት፣ ገመድ እና ሰንሰለት እንጅ የስልጣን ካባ፣ ካራባት እና ዘውድ አይስማማውም። ዳግም ለሆዱ እና ለጥቅም ይሸጠናል። መራራውን ፅዋ እንጋት ዘንድ ካልሻትን የብዐዴን ጉፋያን አምነን አንከተልም። እያንዳንዱ፣ የብዐዴን ኩሊ ጭንብላም እየገለጥን የምናሰጣበት ቀን ተቃርቧል። በአምሓራ ብሄርተኝነት ጭንብል የሸመቀው፣ ዳግማዊ የበለጠ ሞላ ምስለ #አብን በድፍረት አይኑን እየገለጠ ነው። በምንወደው እና በሆንነው #አምሓራነት እየማሉ… ሊያሳርዱን መለከት እየነፉ ነው። ንቁ!!!
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
አዎ፣ ለራሱ ጎጆ ምስረታ ሀቅም አልባ ውልክሽነት ለሚታይበት፣ ፖለቲካዊ እጣ ፋንታውን ከማይወዱት ጠላቶቹ ጋር አጣብቆ ከማሰብ ወዲህ… የራስ ቅሉ የማያስብለትን ከንቱ… ጣዖታዊ ኢትዮጵያን በአምልኮት የሚካድም ትውልድ ነፃ አይወጣም። ራስን ከመሆን የሚለጥቅ ራዕይ ተከባሪ ነው። ነፃ፣ የአምሓራ መንግስት በፍርስራሿ ላይ ማዋለድ የሚችል እፁብ ድንቅ የራሱን ሀገር ሰሪ ጥበበኛ አምሓራዊ ትውልድ እስካልታዬ… ተስፋችን ሩቅ ነው። #አምሓራ፣ ባለ ሀገርነት ይገባዋል!!! ይሄን ከማለም ወዲህ ያለው፣ ድንግዝግዝ ሀሳብ… ስልጣን ቢያቆናጥጠንም እንኳ፣ ነፃ አያወጣንም። መራራው ሃቅን ተጋፈጡት! የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ በኃይል ባፀናነው ግዙፍ ድርሻችን ላይ ቆመን እንመክርበታለን…! ወይ፣ ትቀጥላለች… አሊያ እራሳችንን በዋስትና እናፀናለን!!! አዲሱ ትውልድ አምሓራን የነፃ ሀገር ባለቤት ያደርጋል! #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ!!! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ወለጋዎች ያመረቱት እህል በፋሽስቱ ኦሮሙማ ተጭኗል‼️ የወለጋ አምሓራ ያመረተው እህል፣ ቤት ለቤት እየተፈተሸ በፋሽስቱ አገዛዝ እየተጫነ ተወስዷል። ከጭፍጨፋ ያመለጡት ሴቶችና ህፃናት በርሐብ እንዲረግፉ በአገዛዙ ተወስኗል። ይሄንን አለም ባላየ የሚያልፈው፣ እኛም… የአንድ ሚሊሻ መማረክን ያህል… የወለጋ አምሓራን ሠቆቃ ትኩረት ስላልሰጠነው ነው። በወለጋ እና በአርሲ በከፋ እየሆነ ያለውን የአምሓራ የትግል ሚዲያ ቻናሎች በቂ ትኩረት አልሰጡትም። በሰብዐዊ ጉዳት ጉዳይ መረጃን ማሰራጨት መተንተን እና በሙያተኛ አቀናጅቶ ዘሄግ ድረስ ወርዶ ክስ መመስረት፣ ስርዓቱም ላይ ጫና መፍጠር የሚቻለው መረጃውን በበቂ በማሰራጨትና ዓለም ዓቀፍ ባህበራዊ ጫና መፍጠር በመጀመር ነው። @ትኩረት! ለወለጋ አምሓራ!! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰበር መረጃ-ጎንደር‼️ "ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ ጎንደር የሚመጣው እጁን ሊሰጠን መሆን አለበት። አንቀን ልንይዘው እየጠበቅነው እንገኛለን።" የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ አማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ከፍተኛ  ወታደራዊ አዛዦች ባወጡት የውጊያ ዕቅድ ጎንደር ከተማ ዙሪያ ልዩ ጀብዱ በመስራት ላይ ነው። በውጊያው የአማራ ፋኖ በጎንደር አጼዎቹ ክፍለ ጦር በመሳተፍ ላይ መሆናቸው ታውቋል። ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነ ውጊያ በከፍተኛ የውጊያ ጥበብ በመመራት ላይ እንዳለ ነንም ብሏል። በዚህ ውጊያ፣ ኢላማ ውስጥ የገቡት በከተማዋ ዙሪያ ያሉ የጠላት ወታደራዊ ካምፖችና የአጼ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ፦ "ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ ጎንደር እንደሚመጣ መረጃዎች ደርሰውናል። ጎንደር የሚመጣው እጁን ሊሰጠን መሆን አለበት። አንቀን ልንይዘው እየጠበቅነው እንገኛል።" ሲል ተናግሯል። ዋና አዛዡ አክሎም "በአሁኑ ሰዓት አጼ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ እየተፋለምን ነው። ውጊያው ይቀጥላል!" በማለት ስለውጊያው ሁኔታ አብራርቷል። በዚህ ውጊያ ወንድማማቾች ብርጌድ በጀግንነት በመፋለም ላይ መሆናቸውን የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። የጠላት ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። የውጊያ ገዥ ቦታዎቹን ጥሎ ወደኋላ እየፈረጠጠ ነው። በዋናው የአዘዞ ካምፕ ውስጥ ከባድ መሳሪያዎችን ወደንጹሃን በመተኮስ ላይ ይገኛል። ከሰሞኑ በተከታታይ ወታደራዊ አንቶኖቮች የብልጽግና ሰራዊት ወደጎንደር ከተማ መግባቱ ይታወቃል። #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ኢንስፔክተሩ ፋኖን ተቀላቀለ‼️ ጎንደር-መተማ ኢንስፔክተሩ ከነ ጦሩ ፋኖን ተቀላቀለ። በመከላከያ ኃይል የ27 አመት ልምድ ያለው እና በልዩ ኃይል አደረጃጀት ደግሞ እስከ ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ኢንስፔክተር ታደሰ ውባለም ሰኔ 30/2016 ዓ/ም ከነጦሩ ፋኖን መቀላቀሉን ተናግሯል። ኢንስፔክተሩ ፋኖን ለመቀላቀል ምቹ ሁኔታን ሲጠብቅ እንደቆየ እና ሰሞኑን ወደ መተማ ወረዳ መዛወሩ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለት አብራርቷል። በአሁኑ ሰዓት በመተማ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው አጣናው ዋሴ ብርጌድን እንደተቀላቀለ እና ደሰተኛ እንደሆነም ተናግሯል። 27+5 አመት የውትድርና ልምዴን ለአማራ ህዝብ ነፃነት አዉለዋለሁ ያለ ሲሆን ስማቸውን መጥቀስ ላልፈለገው የትግል ጓዶቹም በቶሎ እንዲመጡ ጥሪ አቅርቧል። #ድል - ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.