አቡነ ጎርጎርዮስ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት Abune Gorgorios Secondary School Adama
Open in Telegram
Show more
2 692
Subscribers
+124 hours
+77 days
+4530 days
Posts Archive
#Very_Urgent 3/13/2018
=====================
#Filannoo_University
#Manneen Barnootaa sad: 2ffaa tiif
Greetings from MoE
Of the 70,000 students who passed Grade 12, only 44,000 have completed their university placement choices. The remaining students need to complete the process by Thursday, September 10 (5/13/2018 E.C.)
Pls urgently communicate with the students and ensure they finalize their placement.
Thank you.
Placement ያልሞላችሁ እንድትሞሉ መልእክት ተላልፏል።
Repost from N/a
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ
============================
በአገራችን እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠልና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የአገሪቱን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት ለማሟላት በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ከፍተኛ የለውጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ይህንንም እውን ለማድረግ ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተደራጁትን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማዕከላት በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን እያፈሩ ይገኛሉ፡፡
በመሆኑም በ2019 ዓ.ም የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና ኦንላይን (Online) በመስጠት መቀበል ይፈልጋሉ፡፡
የትምህርት መስኮች፡-
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ኢንጂነሪንግ
- አርክቴክቸር
- ሲቪል ኢንጂነሪንግ
- ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ
- ኬሚካል ኢንጂነሪንግ
- ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ
- ኮምፒዩተር ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
- ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ
አፕላይድ ሳይንስ
- አፕላይድ ባዮሎጂ
- አፕላይድ ኬሚስትሪ
- ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ
- ፋርማሲ
- አፕላይድ ፊዚክስ
- አፕላይድ ጂኦሎጂ
- አፕላይድ ማቲማቲክስ
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ኢንጂነሪንግ
- አርክቴክቸር
- ሲቪል ኢንጂነሪንግ
- ኬሚካል ኢንጂነሪንግ
- ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሮሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ
- ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ
አፕላይድ ሳይንስ
- ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ
- ፉድ ሳይንስና አፕላይድ ኒዩትሪሽን
- ጂኦሎጂ
- ባዮቴክኖሎጂ
የምዝገባ ጊዜ፡-
- ከነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡
- የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online) በ https://stu.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et; www.astu.edu.et ድህረ ገፅ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቀን፡- በድህረ ገፃችን የምዝገባው ቀን ካበቃበት በኋላ እናሳውቃለን ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ፡-
- በምዝገባ ወቅት በመረጡት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
· የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ይህንኑ አውቃችሁ ቅድሚያ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
· በቂ አመላካቾች የሌሉባቻው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡
· ለፈተና የሚቀርቡት የአመልካቾች ስም ዝርዝራቸው እና የፈተና ጣቢያዎች በሚከተሉት ድረ-ገፆች፡- www.aastu.edu.et ; www.astu.edu.et እንደአመቺነቱም በe-mail የሚገለፅ ይሆናል፡፡
· አመልካቾች ከወዲሁ ፈተናው በሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፣ ማለትም (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብና እንግሊዝኛ እንዲዘጋጁ ይመከራል፡፡
· ፈተና የሚሰጠው በቀጥታ (online) ስለሆነ አመልካቾች በፈተና ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል ግራ መጋባትን ለማስቀረት በምዝገባ ጊዜ ከመመዝገቢያ ፎርማቱ ጋር ተያይዞ የቀረበውን የሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ ይመከራል፡፡
· አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
· የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
· በውጤታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከላይ በተጠቀሱት ድህረ-ገፆች ይገለፃል፡፡
· በመስፈርቱ መሰረት ያልተመረጡ አመልካቾች ከዚህ በፊት እንደሚደረገው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ይሆናል፡፡
· በፈተናው ዕለት ማንኛውንም የሞባይል ስልኮችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ ነው፡፡
· በፈተና ወቅት ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ከታች የተጠቀሱትን ድረ-ገፆች እና ቴሌግራም ቻናላችንን መጎብኘት ይቻላል፡፡
www.astu.edu.et; www.aastu.edu.et
Telegram:https://t.me/AdamaSTU_ASTU
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
Repost from Ministry of Education Ethiopia
ማስታወቂያ
የዩኒቨርስቲ ምደባ በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
የዩኒቨርሲቲ እና የባንድ ምርጫችሁን፣ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ማመልከቻ ለማቅረብ ከታች ያለውን ቪዲዮ መመሪያ በመከታተል መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
Repost from Ministry of Education Ethiopia
ማስታወቂያ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
Ø የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
Ø ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
v የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር
Repost from Ministry Of Education News
📣 የዩኒቨርስቲዎች የ ትዉልድ ደረጃ ምንድነው ?
የዩኒቨርስቲዎች የ ትዉልድ ደረጃ በ አመሰራርት የጊዜ ሂደት ዩኒቨርስቲዎችን በቅደም ተከትል እንደ አንጋፋነታቸው የማስቀምጥ ሂደት ነው።
ከተመሰረቱ ብዙ አመታትን ያስቆጠሩ ዩንቨርስቲዎች ብዙ ነገሮችን ያሟላሉ ተብሎ ስለሚታሰብ በብዙዎች ዘንድ ተመራጭ ያደርጋቸዋል።
🤩 1st Generation
📚 Addis ababa university
📚 Arba Minch University
📚 Bahirdar University.
📚 University of Gondar
📚 Hawassa University
📚 Haramaya University
📚 Jimma University
📚 Mekele University
🤩 2nd Generation
📚 Dila University
📚 Dire dawa University
📚 Jijiga University
📚 Mede Melabo University
📚 ASTU
📚 Debra Markos University
📚 Aksum University
📚 Debra Birhan University
📚 Wollega University
📚Wollo University
📚 Mizan Teppi University
📚Mekdela Amba University
📚 Ambo University
📚 Semera University
📚 Kotebe motrop. University
🤩 3rd Generation
📚Adigrat University
📚Mattu University
📚 Woldia University
📚 Wolkite University
📚Debratebor University
📚 Wachamo University
📚Assosa University
📚AASTU University
📚Arsi University
📚Gambela University
📚 Bulehora University
📚Wolaita sodo university
🤩 4th Generation
📚Jinka University
📚Bonga University
📚Worabe University
📚Injibara University
📚Debark University
📚Mekdela Amba University
📚Raya University
📚Dembidolo University
📚Selale University
📚Oda Bultum University
📚 Borna university
ትምህርት ሚኒስቴር 💠
🔴ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ!
✈️https://t.me/Tmhrt_Minister
✈️https://t.me/Tmhrt_Minister
Repost from Ministry Of Education News
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል።
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ።
ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡
በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል።
የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 👇
https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements
ትምህርት ሚኒስቴር 💠
🔴ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ!
✈️https://t.me/Tmhrt_Minister
✈️https://t.me/Tmhrt_Minister
*YAADACHIISA!*
*Akkam jirtu, Jaalleewwan?*
1. *Baratootni qormaata CBTdhaan qoramaan* keessaa dogoggorri qabxii baratootaa tokko tokko irratti waan mul’ateef keessattu baratootniqabxii isaanii irratti shakkii qaban gosa barnoota Baayooloojii, Keemistriifi Fiiziiksii akka yeroon ol-iyyannoo(“complain”) (Hanga Hagayya 27,2018 hanga sa’a 11:30) osoo hin xumuramin dhuunfaadhaan akka iyyatan jajjabeessa.
ሰላም 🌟 ዘንድሮ 12ኛ ክፍለእ ተፈትናችሁ በተለይ በባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ እና ፊዚክስ ት/ቶች ላይ ቅሬታ/Complain እንድታደርጉ የተወሰኑ ማስተካከያዎች ስላሉ 📝
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT)
የፈተናው ሁኔታ፦ 100 ባለብዙ ምርጫ ጥያቄዎች በኮምፒውተር ይወሰዳሉ። አጠቃላይ ሰዓት፦ 2 ሰዓት ከ30 ደቂቃ።
የቃልና የማመዛዘን ክፍል፦ 55 ጥያቄዎች (60 ደቂቃ)። ንባብ መረዳት፣ ቃላት እና ሰዋሰው ይፈትናል።
የቁጥርና የሂሳብ ክፍል፦ 45 ጥያቄዎች (60 ደቂቃ)። የሂሳብ ስሌት፣ ዳታ ትንተና፣ አልጀብራ እና ችግር መፍታት ይፈትናል።
ህግ፦ የተሰጠው ሰዓት ሲያልቅ ክፍሉ በራሱ ይዘጋል። ወደ ኋላ መመለስም ሆነ ዘሎ ማለፍ አይቻልም።
የሚፈቀዱ ቁሳቁሶች፦ ህጋዊ መታወቂያ፣ የመፈተኛ ቲኬት፣ መደበኛ ካልኩሌተር፣ እስክሪብቶ እና እርሳስ።
የተከለከሉ ቁሳቁሶች፦ ስልክ፣ ስማርት ሰዓት፣ የመገናኛ መሳሪያዎች፣ ማስታወሻዎች እና ያልተፈቀዱ ካልኩሌተሮች።
የመግቢያ መስፈርቶች
የ12ኛ ክፍል (ESSLCE)፦ ቢያንስ 300 (ወይም በየዓመቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚወጣው ማለፊያ ውጤት)።
የ UAT ማለፊያ ነጥብ፦
የመንግስት ስፖንሰርሺፕ እና ፕሬዚዳንሻል ስኮላርሺፕ፦ ቢያንስ 70%።
በራስ ወጪ (Self-Sponsorship)፦ ቢያንስ 60%።
ከፍተኛ ውድድር ያላቸው ዘርፎች፦ እንደ ህክምና እና ምህንድስና ያሉ ክፍሎች የበለጠ ከፍተኛ ውጤት ይፈልጋሉ።
የትምህርት እድል (Sponsorship) ዓይነቶች
የመንግስት ስፖንሰርሺፕ (ወጪ መጋራት)፦
ኢኮኖሚ አቅማቸው ደካማ ለሆኑ ተማሪዎች የተዘጋጀ።
ከወረዳ አስተዳደር የኢኮኖሚ አቅም ማረጋገጫ ደብዳቤ ማቅረብ ያስፈልጋል።
ምደባው በአጠቃላይ የፍሬሽማን ዘርፍ (Natural ወይም Social Science) ላይ ይሆናል።
በራስ ወጪ መማር (Self-Sponsorship)፦
ከ2014 እስከ 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱና መክፈል የሚችሉ አመልካቾች።
ቀደም ሲል በሌላ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ (ከ2015-2017 ዓ.ም) ተመዝግበው የነበሩ የወጪ መጋራት እዳቸውን የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
እስከ 4 የሚደርሱ የትምህርት ዘርፎችን መምረጥ ይቻላል።
ፕሬዚዳንሻል ስኮላርሺፕ፦
ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የቀረበ።
በ12ኛ ክፍል 500 እና ከዚያ በላይ ያመጡ እና UAT ያለፉ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ በነጻ ይማራሉ።
ክፍያ እና ወጪዎች
የምዝገባና የፈተና ክፍያ፦ በአጠቃላይ 1,125 ብር የምዝገባ ክፍያ (ወይም 750 ብር የ UAT ፈተና ክፍያ በቴሌብር ይከፈላል)።
የራስ ወጪ ትምህርት ክፍያ፦ በ ECTS ክሬዲት ይሰላል (1,500 ብር በ 1 ECTS)። አንድ መደበኛ የ 35 ECTS ተርም 52,500 ብር ያስወጣል።
ካምፓሶች እና የትምህርት ዘርፎች
የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science)፦
4 ኪሎ፦ ኮምፒውተር ሳይንስ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሒሳብ፣ ስታቲስቲክስ፣ ጂኦሎጂ።
5 ኪሎ (AAiT)፦ ምህንድስና (ሶፍትዌር፣ ሲቪል፣ ኤሌክትሪካል፣ ሜካኒካል፣ ኬሚካል)።
ጥቁር አንበሳ እና ጤና ሳይንስ፦ ህክምና፣ ፋርማሲ፣ ጤና መኮንን፣ የጥርስ ህክምና፣ ነርሲንግ።
ቢሾፍቱ፦ የእንስሳት ህክምና።
የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science)፦
6 ኪሎ (ዋናው ካምፓስ)፦ ህግ፣ ቋንቋዎች፣ ጋዜጠኝነት፣ ፖለቲካ ሳይንስ፣ ሶሺዮሎጂ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ስነ-ልቦና፣ ትምህርት።
FBE እና ኮሜርስ፦ አካውንቲንግ፣ ማኔጅመንት፣ ኢኮኖሚክስ፣ ፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን።
ስነ-ጥበብ (Alle School)፦ ስነ-ጥበብ፣ ቲያትር፣ ሙዚቃ፣ ዲዛይን።
የዶርምና የካፌ አገልግሎት
ከክልል የሚመጡ ተማሪዎች (መንግስት / ፕሬዚዳንሻል)፦ ነፃ የመኝታ እና የካፌ አገልግሎት ያገኛሉ።
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፦ የዶርም እድላቸው ዝቅተኛ ነው (ተመላላሽ ይሆናሉ)።
በራስ ወጪ የሚማሩ ተማሪዎች፦ በወር 1,500 ብር ገደማ በመክፈል የዶርም አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ።
ምዝገባ
ምዝገባና ቲኬት፦ በ admission.aau.edu.et በመመዝገብ የ UAT ፈተና መግቢያ ቲኬት ማውረድ ይቻላል።
