en
Feedback
South Wollo Zone Gov. Communication Department

South Wollo Zone Gov. Communication Department

Open in Telegram
1 342
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የተፈጥሮ ሐብት ልማት ሥራ (ለጋምቦ - ደቡብ ወሎ)
የተፈጥሮ ሐብት ልማት ሥራ (ለጋምቦ - ደቡብ ወሎ)

ጤፍ ለመንግስት ሠራተኞች የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ወሎ ዞን ኅብረት ሥራ ማስፋፊ ተጠሪ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የካቲት 30/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙዩኒኬሽን) ጤፍ ለመንግስት ሠራተኞች በሦስት ወር ክፍያ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ወሎ ዞን ኅብረት ሥራ ማስፋፊያ ተጠሪ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ ገበያ የማረጋገት ሥራ አንዱ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ተግባር መሆኑ ይታወቃል፡፡ እናም የደቡብ ወሎ ዞን ኅብረት ሥራ ማስፋፊያ ተጠሪ ጽ/ቤት የወልና ታቦር ዩኒየኖችን በማስተባበር ከ300 ኩንታል በላይ ጤፍ በሦስት ወር ክፍያ ለዞኑ መንግስት ሠራተኞች ማቅረቡን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ሶፊያ እብሬ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በፊት ነጭ ዱቄት ለመንግስት ሠራተኞቹ መሰራጨቱን የገለጹት ኃላፊዋ ማኅበራት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ገበያውን ለማረጋጋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ብለዋል፡፡ በመሆኑም ማኅበራት ለመንግስት ሠራተኞች በተመጣጣኝ ዋጋ በሦስት ወር ክፍ የሚያደርጉትን አቅርቦትና ስርጭት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እንደሚሠራም አመላክተዋል፡፡ *** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

ሴቶችን ከጥቃት በመከላከል ሁሉን አቀፍ ተሳታፊና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት ሊሠራ ይገባል - የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች፣ ህጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ደሴ - የካቲት 29/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) ዓለማቀፍ የሴቶች ቀን ከማክበር ባለፈ ሴቶችን ከጥቃት በመከላከል የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች፣ ህጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች ህጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ "ሴቶችን እናብቃ፤ ሰላምና ልማትን እናረጋግጥ" በሚል መሪ መልዕክት 113ኛ ዓለማቀፍ የሴቶች ቀንን በደሴ ከተማ በድምቀት አክብሯል፡፡ በዕለቱም የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች ህጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ቤተልሄም ብርሃኑ ባሰሙት ንግግር በአማራ ክልል በተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ሴቶች፣ ህጻናትና አረጋዊያን የበለጠ ተጎጂ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ አሁን ላይ በሁሉም አካባቢ አንጻራዊ ሰላም እየተፈጠረ ቢመጣም ጠንካራና ዘላቂ ክትትል እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡ የዘንድሮውን ዓለማቀፍ የሴቶች ቀንን በመድረክ ከማክበር ባለፉ የሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ሊያረጋግጥ የሚያስችል ከየካቲት 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ ከሰላም መደፍረሱ ጋር ተያይዞ በዞኑም ሆነ በክልሉ የተረጋጋ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሴቶች የበኩላቸውን እንዲወጡ 158 ሽህ 210 ሴቶች የተሳተፉበት የሰላም ኮንፈረንስ ተካሂዷል፡፡ ሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማጎልበትም ከ6 ሽህ በላይ ሴቶች በገንዘብ ቁጠባ ኅብረት ሥራ እንዲደራጁ በማድረግ 4 ሚሊየን ብር የቆጠቡ ሲሆን 911 ሴቶች ደግሞ ከ7 ሚሊየን ብር በላይ ብድር ወስደዋል፡፡ 338 ሴቶች በተለያዩ ገቢ ማስገኛ ተግባራት ተሰማርተዋል፡፡ በተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የደሀ ደሀ የሆኑ ከ5 ሽህ በላይ ሴቶች ከ9 ሚሊየን ብር በላይ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም የደሀ ደሀ የሆኑ 8 ሽህ 141 ሴቶች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማስተባበር 6 ሚሊየን ብር ክፍያ በመፈጸም የጤና መድን አባል ሆነው የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉንም የገለጹት መምሪያ ኃላፊዋ ከወሊድ ጋር በተያያዘ የእናቶች ሕይወት እንዳያልፍ 443 ዩኒት ደም መለገሱንም አስረድተዋል፡፡ የሴቶችን ቀን በመድረክ ከማክበር ባለፈ በተግባር ከጥቃትና ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በመከላከል ሁለንተናዊ ተሳታፊና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ሥራ ሊሠራ እንደሚገባም መምሪያ ኃላፊዋ አስገንዝበዋል፡፡ በደቡብ ወሎ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የሴቶች ፎረም ሰብሳቢ ወ/ሮ ሃና አለባቸው በበኩላቸው በዓሉ ሲከበር ሴቶች በሰላምና ልማት ያላቸው ሚና እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በተሰማራንበት ሁሉ ብቁ ልንሆን ይገባል ብለዋል፡፡ ይህ በዓል ሲከበር የጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል በዓል ባከበርንበት ማግስት መሆኑ ደግሞ ልዩ ያደርገዋል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በአማራ ክልል የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግና ሁለንተናዊ ልማትን በማረጋገጥ የብልጽግና ጉዟችንን ስኬታማ ለማድረግም ከሴቶች የሚጠበቀውን ሁሉ አስተዋጽኦ ለማበርከት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ዝግጁ ልንሆን ይገባል ሲሉ ወ/ሮ ሃና መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በበዓሉ የተሳተፉት ሴት አመራሮች ሕይወት ጌታሁን እና ሰአዳ አሊ እንደተናገሩት በዓሉ በድምቀት መከበሩ ሴቶችን ለበለጠ ትጋት እንዲበረታቱና ሌሎችም ለሴቶች ትኩረት ሰጥተው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ያነሳሳል ብለዋል፡፡ ለሰላምና ልማት ሴቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው በመሆኑም የጀመሩትን ተሳትፎ አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ *** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ በእንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታና እንቁላል ምርት ግብይት ኀብረት ሥራ ማኀበር ተደራጅተው በመስራት ተጠቃሚ በመሆን ላይ ከሚገኙ አርሶ አደሮች እንቅስቃሴ በከፊል *** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

በመቅደላ ወረዳ ማሻ ከተማ በ21 ሚሊየን ብር የተሠሩ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተመረቁ። ማሻ - የካቲት 29/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ በማሻ ከተማ  በ2016 ዓ.ም ባለፉት ወራት በ21 ሚሊየን ብር ወጭ የተገነቡ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተገንብተው ለምረቃ በቅተዋል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱም የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማምን ጨምሮ ሌሎች የዞን እንዲሁም የመቅደላ ወረዳ አመራሮችና የማሻ ከተማ ነዋሪዎች ታድመዋል። የመቅደላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብድሮህማን ይመር በ31 ሚሊየን ብር በማሻ ከተማ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች እየተሠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ከነዚህ ውስጥ በ21 ሚሊየን ብር ወጭ የተሠሩት መሠረተ ልማቶች ግንባታቸው ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ነው ያሉት። ከነዚህም ውስጥ በ12 ሚሊየን ብር የተገነባው  ከ8 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ይገኝበታል። 6 ሚሊየን ብሩ በኅብረተሰቡ ተሳትፎ የተገኘ መሆኑም ተመላክቷል። በተጨማሪም በ13 ሚሊየን ብር ትራንስፎርመርን ጨምሮ የመብራት ዝርጋታ ሥራ መከናወኑንም አቶ አብድሮህማን ገልጸዋል። ከዚህ ውስጥም 7 ሚሊየን ብር የሚሆነው የኅብረተሰቡ ተሳትፎ ነው። ለወጣቶች ሥራ ዕድል መፍጠሪያ ሸድና ሌሎች ሥራዎችም መከናወናቸው  ተብራርቷል። የደቡብ ወሎ ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ መርከቡ ታረቀ እንዳሉት ደግሞ ከ408 ሚሊየን ብር በላይና በሆነ በጀት 90 የከተማ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመሥራት በበጀት ዓመቱ ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል። ይህን በመፈጸም ረገድ የተከሰተው የጸጥታ ችግር እንቅፋት መሆኑን አንስተዋል። ምክንያቱ ደግሞ ከሰላም መደፍረሱ ባሻገር ከተሞች ገቢ ለመሰብሰብ አለመቻላቸው እንደሆነም ተጠቅሷል። አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አምስት ከተሞች የተሻለ ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑም ተመላክቷል። ከነዚህ ውስጥም የመቅደላው ማሻ ከተማ በግንባር ቀደም ተጠቃሽ አድርጎታል። በሰላም እጦትና በበጀት እጥረት ውስጥ ሆነው ኅብረተሰቡን ግንዛቤ በመፍጠርና በማስተባበር የተሻለ ሥራ እንዲያከናውኑ አስችሏል። ሌሎች ከተሞችም በችግር ውስጥ ሀኖ ልማትን እውን ማድረግ ከማሻ ከተማ ትምህርት መውስደውም ይገባቸዋል ብለዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም የመቅደላ ወረዳ ህዝብ የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ ባደረገው ጥረት በአካባቢው አንጻራዊ ሰላም እንዲኖር ማስቻሉን ገልጸዋል። ማኅበረሰቡ ልማቱን ሳያቋርጥ በማከናወኑም በርካታ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን አክለዋል። በከተማ መሠረተ ልማት የተመዘገቡት ውጤቶች ማሳይ ስለመሆናቸውም ጠቁመዋል። ይህንንም ተሞክሮም በሌሎቸ ማስፋት እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ የከተማ የውስጥ ለውስጥ መንገድና መብራት አለመኖር ለተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለዓመታት ተዳርገው እንደነበር ያነጋገርናቸው የማሻ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚህ ዓመት መሠረተ ልማቶቹ በመገንባታቸው ችግሮቹ እንደተቀረፉላቸው ያስረዳሉ። በቀጣይ የተሻለ መሠረተ ልማት ለመሥራት እንዲያስችልም ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው ነዋሪዎቹ ያረጋገጡት። *** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

የመስኖ ስንዴ ልማት በተሻለ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። ማሻ - የካቲት 28/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) የ2016 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ የታሰበውን ምርት ለማምረት የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝ የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ አስታውቋል። ከባለፈው ጥር  ወር መጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ በሰፊ ንቅናቄ የበጋ መስኖ ስንዴ የዘር እርሻ መከናወኑ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የደቡብ ወሎ ዞን የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተንታና በመቅደላ ወረዳዎች  ተንቀሳቅሰው ሰብሉ ያለበትን ሁኔታ ጎብኝተዋል። በተንታ ወረዳ 08 ቀበሌ 158 ሄክታር ሽፋን ያለው  የበጋ መስኖ ስንዴ አንዱ ጉብኝት የተደረገበት ክላስተር ነው። አርሶ አደር አረጋ እንድሪስ፣ አርሶ አደር ከተማው ሙሐመድና ሌሎች እንደነገሩን ከሆነ ባለፈው ዓመት የተሻለ ምርት ማግኘታቸው ለበለጠ ሥራ አነሳስቷችዋል። በዚህ ዓመት በቂ የማዳበሪያ አቅርቦት በመኖሩና የተሻለ እንክብካቤ በማድረጋቸው ከባለፈው የተሻለ ምርት እንደሚያገኙበት ነግረውናል። የተንታ ወረዳ ም/ አስተዳዳሪ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ አለባቸው 936 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ በማልማት ከ25 ሽህ ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ 833 ሄክታር መሬት ለምቷል ብለዋል። በተጨማሪም 232 ሄክታር መሬት በበልግ ተዘርቷል። ከ1 ሽህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ጥቅም ላይም ውሏል። የአረምና ሌሎች የእንክብካቤ ሥራዎች በመሠራታቸው ሰብሉ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ሌላኛው የተጎበኘው የስንዴ ክላስተር በመቅደላ ወረዳ የ012 ቀበሌ ጠቤ መስኖ ልማት ነው። ባለፈው ዓመት በሄክታር ከ20 እስከ 30 ኩንታል ስንዴ በክላስተር አልምተው እንዳመረቱ ተጠቃሚ የ12 ቀበሌ አርሶ አደሮች ይናገራሉ። በዚህ ዓመት የሚፈልጉትን መጠን ማዳበሪያም አግኝተናል ብለዋል። በዚህ ዓመት ሰብሉ በትልቁ ተስፋ እንደሰጣቸውና በሄክታር 40 ኩንታልና ከዚያም በላይ ማምረት እንደሚችሉም ነው ግምታቸውን የገለጹልን። የመቅደላ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ አደም እንዳሉት ደግሞ 1 ሽህ 500 ሄክታር መሬት በመስኖ ለምቷል። ከዚህ ውስጥ  560 ሄክታር መሬቱ በክላስተር የለማ ነው። ከ90 ሽህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ  ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ 20 ሽህ 570 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ፣ 15 ሽህ ሄክታር መሬት ደግሞ በበልግ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን በማጠናቀቅ ወደ ተግባር ተገብቶ 26 ሽህ 600 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈን እንደተቻለ ገልጸዋል። 30 ሽህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ቀርቦ 27 ሸህ ኩንታል የሚሆነው አገልግሎት ላይ ውሏል። በተጨማሪም ከ3 ሽህ ኩንታል በላይ መስራች ዘር ጥቅም ላይ እንደዋለም አቶ አህመድ አክለው አብራርተዋል። በዚህም 719 ሽህ ኩንታል የስንዴ ምርት ይጠበቃል። አሁን ባለው ሁኔታ ሰብሉ ሲታይ የተጣለውን የምርት ግብ ሊያሳካ በሚችል ቁመና ላይ እንደሚገኝም አመላክተዋል። የሚገኘውም ምርት የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋቱም በተጨማሪ ለዱቄት ፋብሪካዎች በቂ ግብዓትን ማቅረብ የሚቻልበት ሁኔታም ይፈጠራል። ከዚህም በተጨማሪ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚቻልበት ዕድልም እንደሚፈጠር አመላክተዋል መምሪያ ኃላፊው። በክልሉም ሆነ በዞኑ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በጥምር የጸጥታ ኃይሉና በኅብረተሰቡ ተሳትፎ ሁኔታው ወደ አንጻራዊ ሰላም መቀየር እንደተቻለ የተናገሩት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም ናቸው። ከሰላም ማስከበር ጎን ለጎን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ትኩረት አድርገን መሥራት እንዳለብን በማመን እየተሠራ ይገኛል። በትኩረት ከሚሠሩት የልማት ሥራዎች መካከል የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ም/ አስተዳዳሪው ሰብሉ  በሁሉም ወረዳ በተሻለ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከባለፈውም ተሞክሮ በመነሳት ለመስኖ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩ ተነሳሽነት በእጅጉ አድጓል ነው ያሉት። ይህንንም የበለጠ ለማስቀጠል እንደሚሠራም አመላክተዋል። *** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ196 ሽህ በላይ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ተካሂዷል - የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች አገልግሎት ኮምቦልቻ - የካቲት 24/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) በ2016 ዓ.ም በግማሽ ዓመቱ ከ196 ሽህ በላይ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መከናወኑን የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች አገልግሎት አስታወቀ። ይህ የተገለጸው የስድስት ወር አፈጻጸሙን ባለድርሻና አጋር አካላት በተሳተፉበት በኮምቦልቻ ከተማ በገመገመበት ወቅት ነው። በበጀት ዓመቱ  830 ሽህ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ለማከናወን ታቅዶ ምንም እንኳ ክልሉ በሰላም እጦት ውስጥ ቢሆንም ከ196 ሽህ በላይ በአራቱም ኩነቶች ምዝገባ ማከናወን ተችሏል ያሉት የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ኃላፊ መዓዛ በዛብህ ናቸው። ይህም በ4 ሽህ 18 የምዝገባ ጣቢያዎች ነው የተከናወነው ተብሏል። ከዚህ ውስጥም 430 የምዝገባ ጣቢያዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ምዝገባ ማከናወናቸውም ተብራርቷል። በጤና ተቋማት በአንድ ማዕከል አገልግሎት መሰጠቱንም በማከል። ከመጭው መጋቢት ወር ጀምሮ በባህር ዳር ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ምዝገባ እንደሚካሄድም ኃላፊዋ ጠቁመዋል። የዚህን ተሞክሮም በደሴ፣ ጎንደርና በሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ሥራም ይተገበራል። ለዚህ ደግሞ ለአምስት ዓመት የሚሆን የቴክኖሎጂ አሠራር በቂ ዝግጅት ስለመደረጉም ኃላፊዋ አረጋግጠዋል። የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አጠቃላይ ለሀገሪቱም ሆነ ለክልሉ ወሳኝ መረጃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ቡድን መሪ ቤተልሔም አበበ የዕቅዱን 22 በመቶ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና ሙሉ በሙሉ ምስክር ወረቅት የመስጠት ተግባርን እንዳከናወኑ ይናገራሉ። በቀጣይ የተሻለ ቅንጅት በመፍጠር ዕቅዳቸውን ለማሳካት እንደሚሠሩ ገልጸዋል። ከወሳኝ ኩነትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራታቸው የወሊድ ምዝገባን አሟልተው መፈጸሞ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ በዋግ ኸምራ ዞን የጤና ባለሙያ የሆኑት ኩሩቤል ፈጠነ ናቸው። ይህንንም የቅንጅት ሥራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ለሀገራዊና ክልላዊ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳው በእጅጉ የጎላ በመሆኑ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይደግፋል ብለዋል። ሌሎች ባለድርሻና አጋር አካላትም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በመድረኩ ተገኝተው አሳስበዋል። **** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ196 ሽህ በላይ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ተካሂዷል - የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች አገልግሎት ኮምቦልቻ - የካቲት 24/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) በ2016 ዓ.ም በግማሽ ዓመቱ ከ196 ሽህ በላይ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መከናወኑን የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች አገልግሎት አስታወቀ። ይህ የተገለጸው የስድስት ወር አፈጻጸሙን ባለድርሻና አጋር አካላት በተሳተፉበት በኮምቦልቻ ከተማ በገመገመበት ወቅት ነው። በበጀት ዓመቱ  830 ሽህ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ለማከናወን ታቅዶ ምንም እንኳ ክልሉ በሰላም እጦት ውስጥ ቢሆንም ከ196 ሽህ በላይ በአራቱም ኩነቶች ምዝገባ ማከናወን ተችሏል ያሉት የአማራ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ኃላፊ መዓዛ በዛብህ ናቸው። ይህም በ4 ሽህ 18 የምዝገባ ጣቢያዎች ነው የተከናወነው ተብሏል። ከዚህ ውስጥም 430 የምዝገባ ጣቢያዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ምዝገባ ማከናወናቸውም ተብራርቷል። በጤና ተቋማት በአንድ ማዕከል አገልግሎት መሰጠቱንም በማከል። ከመጭው መጋቢት ወር ጀምሮ በባህር ዳር ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ምዝገባ እንደሚካሄድም ኃላፊዋ ጠቁመዋል። የዚህን ተሞክሮም በደሴ፣ ጎንደርና በሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ሥራም ይተገበራል። ለዚህ ደግሞ ለአምስት ዓመት የሚሆን የቴክኖሎጂ አሠራር በቂ ዝግጅት ስለመደረጉም ኃላፊዋ አረጋግጠዋል። የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አጠቃላይ ለሀገሪቱም ሆነ ለክልሉ ወሳኝ መረጃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ቡድን መሪ ቤተልሔም አበበ የዕቅዱን 22 በመቶ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና ሙሉ በሙሉ ምስክር ወረቅት የመስጠት ተግባርን እንዳከናወኑ ይናገራሉ። በቀጣይ የተሻለ ቅንጅት በመፍጠር ዕቅዳቸውን ለማሳካት እንደሚሠሩ ገልጸዋል። ከወሳኝ ኩነትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራታቸው የወሊድ ምዝገባን አሟልተው መፈጸሞ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ በዋግ ኸምራ ዞን የጤና ባለሙያ የሆኑት ኩሩቤል ፈጠነ ናቸው። ይህንንም የቅንጅት ሥራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ለሀገራዊና ክልላዊ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳው በእጅጉ የጎላ በመሆኑ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይደግፋል ብለዋል። ሌሎች ባለድርሻና አጋር አካላትም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በመድረኩ ተገኝተው አሳስበዋል። **** የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et

በአማራ ክልል በተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት በትምህርት ዘርፍ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ  መሆኑን የክልሉ ተምህርት ቢሮ አስታወቀ። ኮምቦልቻ - የካቲት 24/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን) የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ  የምስራቅ አማራ የትምህርት አመራሮች የተሳተፉበት በትምህርት ዘመኑ የግማሽ ዓመት አፈጻጸምና ቀጣይ ተግባራት የምክክር መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ አካሂዷል። በምክትል ርዕሠ መስተዳድር ማዕረግ የማኀበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምንም እንኳ እስካሁን በክልሉ ያሟላ ባይኖርም የትምህርት ቤቶች ገጽታ ደረጃ አራት መድረስ ይገባቸዋል ብለዋል። የትምህርት ግብዓትና የሰው ኃይል ማሟላት ወሳኝ ከሚባሉት ውስጥም ይጠቀሳሉ። በዚህም በትምህርት ዘመኑ በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት የደረሰባቸውን የትምህርት ተቋማት በመንግስት፣ በመልሶ ማቋቋም ተቋምና በበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንዲሁም በባለሃብቶች መልሶ የመገንባት ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ቢሮ ኃላፊዋ ጠቁመዋል። ከ82 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉንም አመላክተዋል። የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ቴክኖሎጅን የሚጠቀም ብቁ ዜጋ የመፍጠር እንቅስቃሴን በዚህ ዓመት የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ትልቅ እንቅፋት ሆኗል። እስካሁንም 2 ነጥብ 6 ሚሊየን የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርት ቤት አልገቡም። ከ3 ሽህ በላይ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ሥራ አልጀመሩም። የክልሉ መንግስት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ከ14 ሚሊየን በላይ የአንደኛ ደረጃ መጽሐፍትን አሳትሞ ከ8 ሚሊየን በላይ ተሰራጭቷል። ቀሪው በጸጥታ ችግር ምክንያት አልተሰራጨም ብለዋል ቢሮ ኃላፊዋ። ትምህርት ሚኒስቴር 4 ነጥብ 5 ሚሊየን የ2ኛ ደረጃ  መጻሕፍትን በአንደኛ ዙር ለክልሉ አስረክቦ የጸጥታ ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች ተሰራጭቷል። 2ኛ ዙር በሰኔ ወር መጥቶ የሚሰራጭ ነው የሚሆነው። 44 ሽህ 600 ኮምባይን ዴስክ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ማሰራጨቱንም አክለዋል። በዚህ መድረክም የሰላም ችግር ባለባቸውና አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች የገጠሙ ችግሮችን መፍትሄ በማበጀት እጥፍ ለመሥራት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው ቢሮ ኃላፊዋ ያስገነዘቡት። በዞኑ በተፈጠረው አለመረጋጋት 32 ትምህርት ቤቶች እስካሁን ትምህርት አለመጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዓለምነው አበራ ናቸው። ከነዚህ ውስጥም ከሰሞኑ 10 ያህሉ ትምህርት ቤቶች መጀመራቸውን በመጠቆም። ከዚህም በተጨማሪ የሚያቆራርጡ ትምህርት ቤቶች እንዳሉም ተመላክቷል። የጸጥታ መደፍረሱ የፈጠረውን ችግር መፍትሄ ለመስጠትም ዞኑ ማንንም ሳይጠብቅ በሦሰት ካላንደር በመክፈል እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰጠ ታደሰ እንዳሉት ደግሞ በጸጥታ ችግር ምክንት 26 ትምህርት ቤቶች መማር ማስተማር አልጀመሩም። 34 ትምህርት ከቤቶች ደግሞ እያቆራረጡ ነው እያስተማሩ ያሉት። በቀሪዎቹ አንጻራዊ ሰላም በመኖሩ የተሳለጠ መማር ማስተማር ሥራ እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል። በአንጻሩ አንጻራዊ ሰላም በመኖሩ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ተግባሩ አለመስተጓጎሉን የነገሩን ደግሞ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አልይ ተፈራ ናቸው። አብዛሃኞች መምህራን ከኦሮሚያ ክልል የመጡ በመሆኑ በዚህ ዓመት 952 መምህራን መልቀቃቸው ለዞኑ ትልቅ ፈተና ሆኖብናል ነው ያሉት። ይህንንም ፈጥኖ ቅጥር በመፈጸምና በሌሎች መንገዶች ችግሩን ለማቃለል ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። * የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09 ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177 ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et