South Wollo Zone Gov. Communication Department
Open in Telegram
Show more
1 342
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
August '24
August '24
+7
in 0 channels
July '24
+53
in 0 channels
Get PRO
June '24
+15
in 0 channels
Get PRO
May '24
+25
in 0 channels
Get PRO
April '24
+22
in 0 channels
Get PRO
March '24
+32
in 0 channels
Get PRO
February '24
+38
in 0 channels
Get PRO
January '24
+22
in 0 channels
Get PRO
December '23
+42
in 0 channels
Get PRO
November '23
+44
in 0 channels
Get PRO
October '23
+16
in 0 channels
Get PRO
September '23
+21
in 0 channels
Get PRO
August '23
+30
in 0 channels
Get PRO
July '23
+114
in 0 channels
Get PRO
June '23
+103
in 0 channels
Get PRO
May '23
+119
in 0 channels
Get PRO
April '23
+112
in 0 channels
Get PRO
March '23
+112
in 0 channels
Get PRO
February '23
+71
in 0 channels
Get PRO
January '23
+164
in 0 channels
Get PRO
December '22
+144
in 0 channels
Get PRO
November '22
+80
in 0 channels
Get PRO
October '22
+127
in 0 channels
Get PRO
September '22
+48
in 0 channels
Get PRO
August '22
+128
in 0 channels
Get PRO
July '22
+29
in 0 channels
Get PRO
June '22
+9
in 0 channels
Get PRO
May '22
+41
in 0 channels
Get PRO
April '22
+64
in 0 channels
Get PRO
March '22
+379
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 August | 0 | |||
| 05 August | 0 | |||
| 04 August | +1 | |||
| 03 August | +3 | |||
| 02 August | 0 | |||
| 01 August | +3 |
Channel Posts
| 2 | No text... | 394 |
| 3 | No text... | 384 |
| 4 | የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተቸገርንበትና በሁለቱም እምነቶች ፆም ወቅት የምግብ ድጋፍ ማድረጉ የሕዝብ አለኝታነቱን ያሳያል ሲሉ በደጋን መጠለያ ካምፕ የሚገኙ ተፈናቃዮች ተናገሩ፡፡
ደጋን - መጋቢት 21/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተቸገርንበትና በሁለቱም እምነቶች ፆም ወቅት የምግብ ድጋፍ ማድረጉ የሕዝብ አለኝታነቱን ያሳያል ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በደጋን መጠለያ ካምፕ የሚገኙ ተፈናቃዮች ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የዳቦ ዱቄት በኦሮሚያና በአፋር ክልል በተፈጠሩ ግጭቶች ሳቢያ ተፈናቅለው በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በደጋን መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አድርጓል፡፡
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ደሴ ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፉአድ መሐመድ ባንኩ በሀገሪቱ የሚከናወኑ ኢንቨስትመንቶችን ለማበረታታት የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ አንስተዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ በማኅበራዊ አገልግሎት ኃላፊነቱንም ለመወጣት ለችግረኞች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አክለዋል፡፡
በዚህም ከዞኑ ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት በተገኘ መረጃ መሠረት ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደጋን መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ 2 ሽህ ተፈናቃዮች ግምቱ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 300 ኩንታል የዳቦ ዱቄት ባንኩ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ ከአሁን በፊት በአራት መጠለያ ጣቢያዎች 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የምግብ ድጋፍ መደረጉንም አውስተዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቋሚነት እስኪቋቋሙ ድረስም ከመንግስት ጎን በመሆን ባንኩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደርግም ጠቁመዋል፡፡
በድጋፍ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር ተወካይ ቤተልሔም ብርሃኑ እንዳሉት ደግሞ ከ44 ሽህ በላይ የሚሆኑ ወገኖች በሀገሪቱ ከተለያዩ ክልሎች ተፈናቅለው በደቡብ ወሎ ዞን በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎችና በማኅበረሰቡ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥም 35 ሽህ የሚሆኑት ሴቶችና ህጻናት ናቸው ብለዋል፡፡
ለነዚህ ወገኖችም መንግስት ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ የተለያዩ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበረሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኙም አመላክተዋል፡፡ ይሁንና እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የምግብ፣ የመጠጥ ውኃና ሌሎች አስፈላጊና መሠረታዊ የሆኑ ድጋፎች ስለሚያስፈልጓቸው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ግለሰቦች ጭምር ከመንግስት ጎን በመሆን የተቻላቸውን ያህል እንዲደግፉም ጠይቀዋል፡፡
አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ተፈናቃዮቹ ወደ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት እንዲቋቋሙም መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ስለመሆኑም የገለጹት ቤተልሔም ብርሃኑ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስላደረገው ድጋፍ በዞኑ አስተዳደር ስም አመስግነዋል፡፡
ከተፈናቃዮች መካከል መሐመድ እንድሪስና ኤሌኒ ኢብራሂም በነበሩበት አካባቢ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ሰፊ ሐብታቸው እንደወደመ ተናግረዋል፡፡ተፈናቅለው ወደ ደቡብ ወሎ ከመጡ ሦስት ዓመት እንዳለፋቸው ያስረዱት ተፈናቃዮቹ እስካሁን መንግስትና መንግስታዊ ልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም የአካባቢው ማኅበረሰብ የምግብና የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፎችን እንዳደረጉላቸው ተናግረዋል፡፡
ይሁንና ባለፉት ወራት በክልሉ ባጋጠመ የሰላም መደፍረስ ጋር በተያያዘ ድጋፉ የተቆራረጠ በመሆኑ መቸገራቸውን ጠቁመዋል፡፡ በችግርና በሁለቱም የእምነት ተከታዮች ጾም ወቅት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የምግብ ድጋፍ ማድረጉ ለሕዝብ ያለውን ወገንተኝነት ያመላክታል ብለዋል፡፡
መንግስት አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ወደ ቀድሞ ቀያቸው እንዲመልሳቸው ፍላጎታቸው እንደሆነ የገለጹት ተፈናቃዮቹ እስከዛውም ድረስ በዚህ አካባቢ ሠርተው ራሳቸውን የሚችሉበት መንገድ እንዲመቻችላቸውም ጠይቀዋል፡፡
*
የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ
መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et | 499 |
| 5 | No text... | 339 |
| 6 | No text... | 406 |
| 7 | ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተሠጠ መግለጫ
*///**
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ተማሪዎች መማሪያ መጻህፍትን እንደሰበብ ተመርኩዞ ያወጣውን የዛቻ እና የጠብ አጫሪነት መግለጫ ተመልክተናል፡፡
ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የትምህርት ሥርዓትን በማጣቀስ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ያወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካትተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳችና የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ በመሆኑና በትናንትናው ዕለት ማለትም መጋቢት 18/2016 ዓ/ም ከነበረበት አካባቢ በመንቀሳቀስ የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡
ስለሆነም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ግልጽ መግለጫ መስጠት ተገቢ ሆኖ አግኝቶታል፡፡
ጊዚያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍ ውስጥ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ሊያመላክታቸው የተፈለጉት አካባቢዎች ካለፉት 30 ዓመታት በፊት ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ሲያቀርቡባቸው በነበሩ ቦታዎች ላይ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
አሁን በሥራ ላይ የሚገኘው የሀገሪቱ ሕገ መንግስት ከመጽደቁ በፊት በተስተዋሉት የአስተዳደራዊ መዋቅሮች እና አደረጃጀት ቅመራ ጅማሬ አንስቶ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሰሜን ዕዝ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ አሰቃቂ ጥቃት በመፈጸሙ ምክንያት ጦርነት እስከተቀሰቀሰበት ጊዜ ድረስ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች በወቅቱ ለነበረው መንግስት የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን በማንሳት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ መሆኑን በበርካታ ታሪካዊ ሁነቶችና ተጨባጭ ማስረጃዎች የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡
ይሁን እንጂ እነዚህ የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ ሕዝቦች እና አካባቢዎችን ለበርካታ ዘመናት በኃይል ሲገዛ የነበረው የቀድሞው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ላነሱት ታሪካዊና ሕጋዊ ጥያቄዎች ሕጋዊ አሰራርን የተከተለ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የአካባበው ተወላጆችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄ አስተባባሪዎችን በማሰር፣ በማሰደድ እና በመግደል የሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ እስከ ሰሜኑ የህግ ማስከበር ጊዜ ድረስ እንዲገፋ አድርጎታል፡፡
የማንነት እና የአስተዳደር መብት ዙሪያ ላነሳቸው ጥቄዎች የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ትግል በተፋፋመበትና ከፍተኛ መስዋዕትነት ጭምር እየከፈለ በሚገኝበት ወቅት ህወሓት የሠሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አሰቃቂ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሁሉንም ኢትዮጵያዊያንን በማቀናጀት ለሁለት ዓመታት የቆየ የሕግ ማስከበር እርምጃ ለመውሰድ የተገደደበት ሁኔታ መፈጠሩ ይታወሳል፡፡
የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄዎቹ ለዘመናት የታፈኑበት ሕዝብም ከማዕከላዊው መንግስት ጎን ተሰልፎ በህ.ወ.ሓ.ት የክህደት ተግባር በኢትዮጵያ ሕልውና እና ሉዓላዊነትት ላይ የተጋረጠውን ግልጽ አደጋ እንዲቀለበስ የበኩሉን አስተዋጽዖ ከማበርከቱ ባሻገር በሂደቱ ህወሓት በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረውን የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተቀዳጁበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡
በዚህም ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ህዝብ እንደ ማንኛውም የሀገሪቱ ሕዝብ ሁሉ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነት መብቱ ሊቀለበስ የማይችል በመሆኑ በቀድሞው የህ.ወ.ሓ.ት እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት መካከል የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ጀምሮ የአማራ ክልል እንደሌሎቹ ዞኖችና የልማት ትሩፋቶች ሁሉ የአካባቢው ሕዝብም በትምህርቱም መስክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡
አካባቢዎቹን በተመለከተ የነበረው፣ ያለው እና የሚኖረው እውነታ ይሄ ሆኖ ሳለ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ከፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት በስራ ላይ የዋሉ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንደሌሎቹ አካባቢዎች የነዚህ አካባቢ ህፃናትም የመማር መብታቸው እንዲከበር የአማራ ክልል መንግስት ግዴታውን መወጣቱን ሰበብ በማድረግ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም፡፡
የተፈጠሩ ችግሮችን በህግ አግባብ እንዲፈታ እየተደረገ ያለውን ጥረት የአማራ ክልል መንግስት የራሱን ድርሻ እየተወጣ ባለበት ሁኔታ በህዝብ መጎሳቆልና በወጣቶች እልቂት ትምህርት አለመወሰዱና የተለመደ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆኑ እጅጉን አሳዝኖናል፡፡
ስለሆነም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ፣ ሀገራችንንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት በመቆጠብ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር እንዲሁም አንድ ሀገር ለመገንባት ለሚፈለገው ዘላቂ ሠላም እና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር እንመክራለን፡፡
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
መጋቢት18/2016 ዓ/ም
ባሕር ዳር | 362 |
| 8 | No text... | 284 |
| 9 | Facebook: https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
Telegram : https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
X Page : https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
TikTok - tiktok.com/@user6700427471177
Instagram: https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
YouTube: https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
Website : https://www.southwollocommunication.gov.et | 19 |
| 10 | In South Wollo Zone, due to the work done by the people and the security forces together and in coordination, there is peace and developmental and good governance works that can benefit the society are being carried out.
Dessie - Megabit 18/2016 (South Wollo Communication)
South Wollo zone administration announced that due to the work done by the people and the security forces in the zone, development and good governance works that can benefit the society are being carried out as planned.
South Wollo zone chief administrator Mr. Ali Mekonnen in his press release today explained that due to the problem of silence that happened in the past eight months, the inability to supply the farmers with produce on time and lack of support has had a great negative impact on his productivity.
The extremist group in the zone has also stated that summer activities are not being carried out properly, taxes are not paid to the government, students are not allowed to enter the school market, infrastructure is cut and free production and human activity.
Mr. Ali who mentioned that there are 1 thousand 208 schools in the zone by extremist Hailu Sabia is not teaching 57 schools.
Also, Mr. Ali said that there were nine projects that were started in the zone, seven of them were stopped due to the problem of peace, said that at the moment only projects that are from Haik-Bistima-Chifra and Degolo-Kelela are working on.
The chief administrator, who explained that the peace situation is contradictory by the law enforcement measures taken in the zone, said that the owner of the peace is due to the work of the people and the security forces.
Mr. Ali, who said that the zone is in a problem of peace, has said that it has been possible to develop more than 26 thousand hectares of land with summer irrigation wheat.
In the integrated natural resource development work, more than 840 thousand farmers participated 990 streams have been rebuilt and estimated 8 points 1 million birr public participation work has been done.
The federal and regional governments have stated that the green footprint and lemat profit works are also being done with high participation of the people and that they are approaching the zone to ensure that there is no shortage of quality and quality seeds instead of increasing crop production and said that more than 331 thousand quintals of fertilizer has been entered into the zone so far.
They have indicated that they can distribute 260 thousand quintals of fertilizer to the farmers in a timely manner in order to protect them from extremist kidnapping.
More than 368 thousand farmers have said that they have been able to become a member of health care in order to solve financial and health problems. They have said that 255 million birr has been collected in this too.
On the other hand, Mr. Ali, who said that the society was not paying tax to the government by one of the extremist forces in the zone, has stated that he has been planning to collect 3 billion birr in the zone and has been able to collect more than 1 point 3 billion birh.
Mr. Ali said that the impact of the peace problem has on the cost of living is high. He said that efforts are being made to take temporary solutions to stabilize the market. Unions and cooperatives have given more than 222 million birr to provide agricultural and industrial products to the low standard of living and government employees.
In connection with this, it is planned to create more than 133 thousand jobs in the zone and it is possible to create jobs for 69 thousand job seekers.
***
South Wollo zone government communication department
The following addresses are the options to make information available. Be part of our family to get fast and accurate information by clicking on the links and liking! | 363 |
| 11 | No text... | 311 |
| 12 | በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት በመደራጀታቸው የኑሮ ጫናውን ከመቋቋም ባለፈ ሐብት እየፈጠሩ እንደሆነ ተጠቃሚዎች ተናገሩ፡፡
አልብኮ - መጋቢት 16/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
በደቡብ ወሎ ዞን 177 ሽህ 780 አባላት ያሏቸው 566 የገንዘብ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ይገኛሉ፡፡ እነዚህም ከ116 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ያላቸው ሲሆን ከ289 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር በላይ ደግሞ ቆጥበዋል፡፡ ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ብድር አሰራጭተዋል፡፡ በዚህም 104 ሽህ 842 የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ተግባራት ተሠማርተው ተጠቃሚ ሆነዋል - እንደ ደቡብ ወሎ ዞን ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ተጠሪ ጽ/ቤት መረጃ፡፡
1 ሽህ 47 መሠረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በአባልነት ያቀፉ አራት ዩኒየኖች ተደራጅተው እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ የነዚህም ካፒታል ከ75 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ ደርሷል፡፡ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይም ቆጥበዋል፡፡ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ደግሞ ብድር አሰራጭተዋል፡፡
ወ/ሮ ፋጡማ ኢብራሂም ይባላሉ፡፡ በአልብኮ ወረዳ የጀማ ንጉስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር አባል ናቸው፡፡ መሬት ቢኖራቸውም የሚያርሱበት በሬ ስለሌላቸው ከማኅበራቸው ባገኙት ብድር ችግራቸው ተቀርፎ አሁን ላይ የሦስት በሬዎች ባለቤት መሆን እንደቻሉ ይናገራሉ፡፡
አቶ የማነ አሰን ደግሞ በኮምቦልቻ ከተማ የመንግስት ሠራተኛ ሲሆኑ ባገኙት የብድር አገልግሎት ከመንግስት የሥራ ሰዓት ውጭ በመሥራት አሁን ላይ የኑሮ ውድነት ያሳደረውን ጫና ከመቋቋም አልፈው ሐብት መፍጠር እንዳስቻላቸው አስረድተዋል፡፡
በአልብኮ ወረዳ አርሶ አደር ብሩ ይማም ደግሞ በአባልነታቸው ባገኙት ብድር ተጠቅመው በተለያዩ የንግድ ሥራዎች ተሠማርተው ከፍተኛ ለውጥ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ የዳቦ ቤት፣ ወፍጮ ቤትና የአይሱዙ መኪና ባለቤት እንደሆኑም ነግረውናል፡፡
የደሴ አምባ ዩኒየን የገንዘብ ቁባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተገኝ ወርቁ እንዳሉት ደግሞ 413 መሰረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በአባልነት በመያዝ ከ466 ሽህ ብር ካፒታል ጀምሮ አሁን ላይ 19 ሚሊየን ብር ከዕጣ ሽያጭ ብቻ ተሰብስቧል፡፡ 400 ሚሊዮን ብር በቁጠባ የተሰበሰብ ገንዘብ ስለመኖሩም ጠቁመዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ለአባል መሠረታዊ ማኅበራት በማሰራጨት በርካቶች በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ተሠማርተው ሐብት እየፈጠሩ መሆኑንም አያይዘው አስረድተዋል፡፡
መሠረታዊና ዩኒየን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በማደራጀትና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የካፒታል አቅማቸው እንዲጎለብት የተደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ኅብረት ሥራ ማስፋፊያ ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሶፊያ እብሬ ናቸው፡፡ በዚህም ከ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ብድር በማሰራጨት አርሶ አደሮች፣ መንግስት ሠራተኞችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ ከማድረግም በላይ በርካቶች ሐብት እንዲፈጥሩ ማድረግ እንደተቻለም ኃላፊዋ አክለዋል፡፡
*
የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ
መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et | 376 |
| 13 | No text... | 298 |
| 14 | በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ወጣቶች በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚ የኾኑበት ሥራ የሚደነቅ መኾኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር) ገለጹ፡፡
በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር) የተመራ ልዑክ በደቡብ ወሎ ዞን በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመስኖ እየለሙ የሚገኙ የአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት፣ የበጋ መስኖ፣ የበጋ አፈር እና ውኃ ጥበቃ ሥራዎችን ተመልክተዋል።
በቃሉ ወረዳም የሀርቡ አትክልት እና ፍራፍሬ ችግኝ ጣቢያን፣ የማኅበራት ፍራፍሬ ተክሎችን፣ ለክረምት አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየተዘጋጁ የሚገኙ ችግኞችን፣ በ021 ቀበሌ በዶሮ እርባታ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን እና በደጋን ከተማ በፌዴራል መንግሥት እየተገነባ የሚገኝ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።
በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የተመለከቱት እና በተሠሩ የተፋሰስ ሥራዎች ላይ ወጣቶች በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚ የኾኑበት ሥራ የሚደነቅ እና ለሌሎች አካባቢዎችም አርዓያ የሚኾን ነው ብለዋል። በወረዳው በ320 ሄክታር መሬት ላይ የተሸፈነው የበጋ መስኖ ስንዴ ሰብል ልማት ጅምር ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
በቃሉ ወረዳም በማንጎ ተክል ብቻ ከ600ሺህ በላይ ችግኝ እና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ለደን ልማት የሚውሉ ችግኞችን ማየታቸውን የገለጹት ዶክተር ለገሰ በሁለቱም ወረዳዎች የተከናወኑ የበጋ ተግባራት እና የቀጣይ የክረምት ሥራዎች ዝግጅት በጥሩ መልኩ መከናወናቸውን እንደተመለከቱ ነው የተናገሩት ።
በዶሮ እና በወተት ላም እርባታ ላይ የሌማት ትሩፋትን ለማሳካት የተጀማመሩ ሥራዎች ጥሩ መኾናቸውን ገልጸዋል። በስፋት መሥራት እንደሚገባም አመላክተዋል።
በማንጎ ተክል ላይ የታየውን በሽታ በተመለከተም በፌዴራል ደረጃ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚመክሩበት ተናግረዋል። የደቡብ ወሎ ዞን አሥተዳደሪ አሊ መኮንን ዞኑ በአትክልት እና ፍራፍሬ አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም የፌዴራል መንግሥት እገዛ ወሳኝ መኾኑን ተናግረዋል።
እንደ ሀገር በግብርና ዘርፍ በ10 ዓመት ውስጥ ለማሳካት የተያዘውን እቅድ ዞኑ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ነው ያስገነዘቡት። አቶ አሊ የፌዴራል የሱፐርቪዥን ቡድን በዞኑ ይህን መመልከቱ ጥንካሬዎችን ለማጉላት እና ድክመቶችን ለማረም ወሳኝ ስለመኾኑም ነው የተናገሩት።
ከማኅበራዊ ተቋማት ግንባታ አንፃር በደጋን ከተማ ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ቤት በፌዴራል መንግሥት መገንባቱን የጠቀሱት ዋና አሥተዳዳሪው በዞኑ በአጠቃላይ ስምንት ትምህርት ቤቶች በፌዴራል መንግሥት እንደተገነቡ ነው የተናገሩት።
@አሚኮ | 515 |
| 15 | No text... | 511 |
| 16 | የፌዴራል መንግሥት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በደቡብ ወሎ ዞን አርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተመለከቱ።
አርጎባ - መጋቢት 10/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
በመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ክቡር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የተመራው የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተው የልዑካን ቡድን አባላት በዞኑ ውስጥ ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ምልከታ በማድረግ ላይ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ደለመኔ ሞዴል ተፋሰስ ውስጥ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል ለወጣቶች የሥራ ዕድል የተፈጠረበትንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ውጤቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
****
የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ
መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et | 426 |
| 17 | No text... | 393 |
| 18 | የምስራቅ አማራ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት በወቅታዊ ጉዳዮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እያደረገ ነው።
ደሴ - መጋቢት 10/2016 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
የምስራቅ አማራ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት በወቅታዊ ጉዳዮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እያደረገ ነው።
በመድረኩ የደቡብ ወሎና ሰሜን ወሎ ዞኖች፣ የደሴ፣ ወልዲያና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮች፣ የዋግ ኽምራ ዞን የዞን፣ የከተማና የወረዳ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎችና ጸጥታ አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አዛዦች ተገኝተዋል።
መድረኩ የአካባቢውን ሰላም ዘላቂ በማድረግ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን በዝርዝር በመገምገም በቀጣይ ጊዜያት ተግባራዊ የሚደረጉ አቅጣጫዎችን ያመላክታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የአማራ ክልል ም/ ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ የሰሜን ምሥራቅ እዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አሰፋ ቸኮልና ሌሎች የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
*
የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ
መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
ኤክስ ገጽ፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
ቲክቶክ - tiktok.com/@user6700427471177
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et | 268 |
| 19 | No text... | 264 |
| 20 | በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው - ዶክተር ለገሰ ቱሉ
በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ ተግባራት በአካባቢው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ገለፁ።
በዶክተር ለገሰ ቱሉ የተመራ የፌዴራል መንግስት የድጋፍና ክትትል ቡድን በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያና ተሁለደሬ ወረዳዎች የበጋ ወቅት ስራዎችና የሌማት ትሩፋት ተግባራትን ተመልክቷል።
ሚኒስትሩ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት ኢኮኖሚውን በማነቃቃት ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በደቡብ ወሎም የበጋ መስኖ ስንዴን የማልማትና በሌማት ትሩፋትም አስፈላጊ የሆኑ ምርቶችን በማምረት ለህብረተሰቡ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
የስራ ዕድል ፈጠራውን ከሌማት ትሩፋት ጋር በማስተሳሰር በወተት፣ በእንቁላል፣ በማር ምርትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች በማምረት የገበያ ክፍተቱን ለመሙላት እየተሰራ ያለው ስራ አበረታች ነው ብለዋል።
የተቀረጸው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማነት ማረጋገጫ መሆኑን በዞኑ እየተከናወነ ያለው ስራ ማሳያ መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል።
የፌዴራል መንግሥትም በየጊዜው የድጋፍ ቡድን በመላክ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን በበኩላቸው በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ከለማው 26 ሺህ ሄክታር መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም ሁሉም የዞኑ ነዋሪ በአካባቢው አትክልትና ፍራፍሬ፣ ዶሮና የመሳሰሉትን በማልማትና በማርባት በንቃት እንዲሳተፍ መደረጉን ገልጸዋል።
በዶሮ እርባታ በተፈጠረልን የስራ ዕድል ለመለወጥ እየሰራን ነው ያለችው ደግሞ በደሴ ዙሪያ ወረዳ የ015 ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሀቢባ ኢብራሂም ናት።
ዘንድሮ 61 ሆነው በመደራጀት 1 ሺህ 100 እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ማርባት መጀመራቸውን ጠቁማ በቀን ከ600 በላይ እንቁላል ማግኘት መጀመራቸውን ገልጻለች።
የፌደራል መንግስት የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በሐይቅ ከተማ በገበታ ለትውልድ የሚለማውን የሎጎ ሐይቅንም ጎብኝቷል።
ኢዜአ | 326 |
