cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Getachew shiferaw

Show more
Advertising posts
44 562
Subscribers
-2624 hours
-2847 days
-99330 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
Media files
9 2692Loading...
02
የሚገርሙ፣ የሚያሳዝኑም ጉዳዮች ናቸው! 1) የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ውጭ ተንቀሳቅሶ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ራሱ ጌታቸው ለትግራይ ሕዝብ ተናግሯል። ትግራይን የሚያስተዳድረው ከጦርነቱ በፊት የነበረው፣ ወንጀለኛ የተባለው መዋቅር ነው። ይህን ጌታቸው ረዳ በሚዲያ ወጥቶ ያረጋገጠው ነው። ይህ ህገወጥ መዋቅር ስለሆነ ነው ጊዜያዊ አስተዳደር ማዋቀር ያስፈለገው። ትግራይ ውስጥ ከመቀሌ ውጭ ስብሰባ እንኳ ማድረግ የማይችለው የጌታቸው ረዳ አስተዳደር፣ በህጋዊ ስምምነት የተሰጠውን ትግራይን እንዳያስተዳድር ተደርጎ፣ በማያገባው ከትግራይ ውጭ ያሉትን የአማራ ግዛቶች እንዲያስተዳድር ነው የተደረገው። ሰሞኑን ትህነግ በወረራቸው የአማራ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደሩ መዋቅሩን አሰማርቷል። ትህነግ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ የፈቀደለት የወረራ አላማ ስለሆነ ነው። ትግራይ ውስጥ አንድም ቀበሌ እንዳያስተዳደር የተደረገው ጌታቸው የአማራን አካባቢዎች ግን በህገወጥ መንገድ እንዲይዝ ተደርጓል። 2) ሰሞኑን በትግራይ ፖለቲካ አጀንዳ የሆነ ጉዳይ አለ። ትህነግ የአማራ አካባቢዎች ተወልደው ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደላችሁም" እንዳላቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ረዳኢ ሓለፎም ቃል በቃል ተናግሯል። የትግሬ ካባ የሚሰጠንም የሚቀማንም ሌላ ቡድን አለ ብሏል። የአድዋውን ቡድን ነው። ታዲያ ራያ ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደሉም። ባንዳ ናቸው።" ወዘተ እያለ የሚፈርጅ ራያን መሬቱንና መሬቱን ብቻ እንደሚፈልግ ግልፅ ነው። አመራሮቹን በጠላትነት የፈረጀ ለሕዝቡማ ያለው ጥላቻን መገመት ቀላል ነው። በተደጋጋሚ በተግባርም የታየ ነው። 3) ራያን የወረረው የትህነግ ታጣቂ "አርሚ 24" ይባላል። መከላከያን በመታበት ጥቅምት 24 የተሰየመ ነው። መከላከያ የተገደለበትን ቀን ማስታወሻ ያደረገውን ኃይል ነው እያገዘ የሚገኘው። 4) የሰላም ስምምነቱ ያለ ምንም ማወላዳት የደነገገው፣ የጊዜ መንዛዛት ያልተቀመጠበት የትጥቅ መፍታት ነው። በማያሻማ መልኩ በአንድ ወር ውስጥ ትጥቅ ይፍቱ ተብሎ ነበር። ጭራሽ አስታጠቋቸው። መከላከያ ትግራይን ይረከብ ተብሎ ነበር። ጭራሽ መከላከያ ከትግራይ ወጥቶ አማራ ላይ ዘምቶ፣ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ትህነግ አማራ ክልልን በኃይል እንዲይዝ ተደረገ 5) ትህነግ ባለፉት ወረራዎች ዘረፋ የሚፈፅሙትን በየጦሩ አደራጅቶ አሰማርቷል። በዘረፉት ልክ ጥቅም አግኝተዋል። እንደ ጀግና ታይተዋል። ይህ ኃይል ግን ወደ ትግራይ ተመልሶ አረመኔ ሆነ። የአርሶ አደር በሬ አርዶ መብላት፣ የተቋማትን ብረታብረት መዝረፍ ወዘተ። ሰሞኑን የትግራይ ክልል ውሃ መሳቢያ ብረቶች እየተዘረፉ መሆኑ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ይህን የራሴ የሚለውን ትግራይን እየዘረፈ ያለ ኃይል ነው ጠላቴ ወደሚለው አማራ ይዘውት የመጡት። ከራያ ብቻ ከ50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለውም ይህ አረመኔ ኃይል በሚፈፅመው ወንጀል ምክንያት ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው አማራ ላይ ነው!
9 6007Loading...
03
Media files
10 8134Loading...
04
የወረራ ዝግጅት! ራያን የወረረው ትህነግ ጠለምትንና ወልቃይትን ለመውረር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በሱዳን በኩል፣ አርሚ 11 ጠለምትን ለመውረር፣ አርሚ 17 ወልቃይትን ለመውረር ዝግጅት ላይ ነው፣ አርሚ 35 ከአክሱም ወደ ሽሬ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥቅምት 24 መከላከያን የመቱበትን ማስታወሻ ያደረጉት "አርሚ 24" ደግሞ ራያን የወረረው ነው። ይህ በሆነበት ብልፅግና የአማራ አስተዳደሮችን በሕገወጥ መልኩ አፍርሶ በተፈናቃይ ስም የወረራ በር እየከፈተና እያገዘ ይገኛል። እንደ ገለልተኛ "ትጥቅ መፍታት አለባቸው" እያለ የሚቀልደውም ዝግጅታቸውን ስለማያውቅ አይደለም። ማዘናጊያ ነው። በሌላ በኩል በተቃዋሚም ሆነ በሌላ ስም ትህነግ ጋር ስምምነት ለመፈፀም የሚደረግን ሂደት የህዝብ ለህዝብ እያስመሰለ፣ የትህነግን ወረራ የሚያድበሰብስም የትህነግና ብልፅግናን የጓዳ ውልና የወረራ አላማ የሚያስፈፅም የአማራ ጠላት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
11 22111Loading...
05
Media files
11 54327Loading...
06
ያዘዝነውን ካላስፈፀመ መከላከያንም እናቀምሰዋለን ብለዋል! በአማርኛ ነው! ቀጥታ ትዕዛዝ ነው! ሰሞኑን ትህነግ ባደረገው ሰልፍ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር መከላከያ በተገኘበት በአማርኛ ጭምር ያስተላለው ዛቻ ነው። መከላከያ የምንፈልገውን ካላስተገበረ ሱሪያችን ያውቃታል። ይቀምሳል ተብሏል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር የአማራን ርስቶች ለመያዝ ህፃናትና አዛውንቶች ይዘን እንደማንመጣ ይታወቃል ብሏል። እንዳሉት ተፈናቃይ ይዘው አልመጡም። ታጣቂ ነው ይዘው የመጡት። መከላከያም ባዘዝነህ መልኩ ካልሰራህ ሱሪያችን ታውቃታለህ ተብሏል። ይህ ጌታቸው ረዳ የሚያዘው ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር ነው።
11 31120Loading...
07
Media files
14 4508Loading...
08
ትህነግ የጓዳ ውሉን ይፋ አደረገው! ትህነግ በጀኔራል ታደሰ ወረደ በኩል የጓዳ ውሉን በማያሻማ መልኩ ይፋ አድርጓል። ብልፅግና ጠለምትና ራያን በቅርቡ፣ ከዛም ወልቃይትን አሳልፎ ለመስጠት የተዋዋለበትን በይፋ ተናግሯል። ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን በትህነግ ታጣቂ ከራያ የተፈናቀሉት በጓዳ ውሉ መሰረት እንደሆነ ይታወቃል። አማራ እየተወረረ ያለው በጓዳ ውሉ መሰረት ነው። የብልፅግና አመራሮች ስለ ትህነግ ትጥቁን መፍታት ወዘተ ሲያወሩ "ውሸታቸውን ነው" የምንለው በምክንያት ነው። ጦርነት የሚፈልግ ኃይል ወዘተ እያለ የሚያወግዙ የሚመስሉት ውሸት ነው። የአማራን ግዛቶች አሳልፈው ለመስጠት የተዋዋሉት በወረራ መሆኑ ይፋ ወጥቷል። ታደሰ ወረደ ብልፅግና አማራን በኃይል እንዲይዙ የሰጣቸውን ድጋፍና ፈቃድ በሚዲያ ወጥቶ ሲገልፅ ይህ ሁለተኛ ጊዜው ነው። እነ ተመስገን ጥሩነህ "ያፈነገጠ ወዘተ" እያሉ ሀሰት ሲናገሩ፣ ጀኔራል ታደሰ በይፋ መጥቶ ከብልፅግና ጋር የተዋዋሉት የጓዳ ውል መሆኑን እየገለፀ ነው። አማራን በትህነግ እያስወረረ የሚገኘው ብልፅግና ነው። ትህነግ ባለፈው በጌታቸው ረዳና ታደሰ ወረደ፣ ዛሬም በታደሰ ወረደ በኩል ወረራው ከብልፅግና ጋር በተስማሙት መሰረት የተደረገ እንደሆነና እንደሚቀጥል ሲገልፅ ብልፅግና ትንፍሽ አላለም። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደሮች ናቸው ወረራው በስምምነት የተፈፀመ መሆኑን የሚናገሩት። ያፈነገጠ ወዘተ የሚባለው ነጭ ውሸት ነው። ማዘናጊያ ነው። የጓዳ ውሉን ማድበስበሻ ነው!
15 06814Loading...
09
Media files
12 59110Loading...
10
ሬዲዮው የትህነግ/ህወሓት ባትሪ ሳይጎርስ!
11 9873Loading...
11
Media files
15 6065Loading...
12
የእስር ሰለባው ጋዜጠኛ ለምክክር ኮምሽኑ ያነሳቸው ወሳኝ ጥያቄዎች ‼ ሞኝን እብባ ሁለት ጊዜ ነደፈው፤ አማራስ ሁለት ጊዜ ይነደፍ ይሆን! በፍጹም! (ዳዊት በጋሻው ከቃሊቲ እስር ቤት) ሚያዚያ 13 እና 14 2016 ዓ.ም በትጥቅ ትግል ላይ የሚገኙ ኃይሎች ወደ ምክክር እንዲመጡና ለዚህም ከለላ እንደሚደረግ የሚገልፀ ዜና ተመለከትኩ፡፡ ይህንን ያሉት የሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሞሽነር ሂሩት ገ/ስላሴ ናቸው፡፡ ወቅቱ አሰቃቂ የጭንቅ ጊዜ ሆነ እንጅ ንግግራቸው ሙሉ የኮሜዲ ይዘት ያለው ነው፡፡ ግለሰቧ ይህንን በተናገሩበት ወቅት የአማራ ልጆች በማንነታቸው ብቻ እየተመረጡ የሀገሪቱን እስርቤቶች ሞልተዋል፡፡ የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ እና በሌላው የሀገሪቱክፍሎች በሀሠት እየተከሰሱ ፤ እንደ አዋሽ አርባ ባሉ የማሰቃያ ቦታዎች መከራቸውን እያ ባለበት ወቅት ከለላ እናደርጋን እንመካከር እያሉ ማውራት ህሊና ቢስነት ነው፡፡ በታሪክ ፊትም ተጠያቂ ያደርጋል፡፡ የአማራ ልጆች የዕድሜ ፣የሙያ የፆታ፣ የእምነት፣ የት/ት ደረጃ ልዩነት ሳይኖር በጅምላ እየታሰሩ ነው፡፡ በሀገሪቱ ያሉ እስር ቤቶች በመሙላታቸው የብልፀሸግና ፓርቲ አመራሮች በኦሮምያና በአፋ አማራ የሚታጎርባቸው ወህኒ ቤቶች በአጭር ጊዜ እንዲሰሩ ማዘዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው እንግዲህ ስለምክክርና ስለከለላ ዋስትና እየተወራ ያለው፡፡ እስኪ ለኮሚሽኑ አባላት በተለይም ለዋናና ለምክትላቸው እነዚህን ጥያቄዎች ላንሳ፡- 1. በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ማጥፋትወንጀል እያያችሁና በዚህም ላይ ምንም ሳትሉ ስለምክክር ስታወሩ ህሊናችሁ ምን ይላችኋል? 2. በአስቸኳይ አዋጅ ሰበብ ንፁሀንን በድሮን እየተጨፈጨፉ እናንተ እንመካከር ስትሉ ህዝቡ ምን የሚል ይመስላችኋል? 3. ፖሊስና ደህንነት የነቁ አማሮችንበመላው ሀገሪቱ እያሳደዱ ባሉበት ሁኔታ እናንተን አምኖ ጠረንጴዛ የሚስብ ያለ ይመስላችኋል? 4. እናንተ ከለላ እንስጣችሁ የምትሏቸው የአማራ ህዝብ የትግል መሪዎች በፍትህ ሞኒስቴር ተከሰው በጋዜጣ ተጠርተዋል፡፡በአንድ በኩል የወንጀል ክስ ከፍቶ በሌላ በኩል ከለላ ልስጥ ማለት አይጋጭም ወይ? በመሰረቱ እኔ ጥያቄን ባሳደገኝ ህዝብ ጨዋነት ልክ በትህትና ላቅርብ ብዬ እንጅ ስለ 11ዱም ኮሚሽነሮችመረጃም ማስረጃም አለኝ፡፡ ለምሳሌ ያህል ስለ ፕ/ር መስፍን አርአያ ፣ መሐመድ ድፈር፣ ዮናስ አዳዬ፣ ዘገዬ አስፋው በደንብ መናገር ይቻላል፡፡ የምክክር ኮሚሽኑ አባል አቶ ዘገዬ አስፋው የኦነግ ስራ አስፈጻሚ መሆን በሽግግሩ ወቅት የአማራ ህዝብን አስጨፍጭፏል፡፡ ይህ ተራ አሉባልታ ሳይሆን በሰነድ የተቀመጠ ሀቅ ነው፡፡በመሆኑም በወቅቱ የግብርና ሚኒስትር ነበር፡፡ በጥቅሉ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመና ያስፈፀመ በመሆኑ ህዝብ በወንጀል ይፈልገዋል ፡፡ በተጨማሪም የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ ዙርያ ቤታቸው ፈርሶ፣ ተፈናቅለው በስቃይ ላይ ሆነው ፤ለንብረታቸውና ለህይወታቸው ምንም ይቅርታና ዋስትና ሳይደረግ በማን አለብኝነት ሸገር ከተማ ብሎ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከተማ ሲያስመርቅ አቶ ዘገየ አስፋው የድግሱ ተካፋይ ነበር፡፡ ስለሌሎችም ሙሉ ማስረጃ አለ፡፡ የኮሚሽኑ ገለልተኛነት እዚህ ድረስ ነው፡፡ ለማንኛውም ለአፍና ለይምሰል እንኳን እነዚህን ጥያቄዎች ለማንሳት ሞክሩ፡- 1) መንግስት የምትሉት አካል ተኪስ እንዲያቆምና የዘር ፍጅቱን እንዲተው 2) አዋጅ ተብዬው መግደያና ማሳደጃ እንዲቀርና ለዚህም ተጠያቂ እንዲሆን 3) በመላው ሀገሪቱ ያለውን የንፁሀን ግድያ እንዲያቆም በተደጋጋሚ ብትናገሩ ለይምሰል እንኳን የተሸለ ይሆናል፡፡ በመሰረቱ ዐቢይ አህመድ ምክክር ኮሚሽንና ሽግግር ፍትህ እያለ ያለው፦ 1. በነዚህ ተቋማት ሰበብ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት 2. ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ይሄው ላወያይ ነው ለማለትና ስልጣንን ለማራዘም ነው፡፡ ያም ሆነ ይሕ ግን ከዚህ በኋላ የአማራን ህዝብ ለዓመታት አይደለም ለቀናት መሸወድ ወይም በሽመልስ አብዲሳ አገላለፅ (ኮንቪንስና ኮንፊውዝ) ማድረግ በፍፁም አይቻልም፡፡ ከዚህ በኋላ ጥቅም ላይ የሚውል አይደለም፡፡ ለማንኛውም ለይምሰል የሚደረግ የትኛውም ድርጊት ከህዝብ አያመልጥም፡፡ መንግስቱ ሀይለማርያም በስተርጅና ለስደትና ለውርደት፤ መለስ ዜናዊን በህዝብ ፊት ለውርደት ብሎም ለሞት የዳረጓቸው ሁኔታዎች እልህና ይምሰል ናቸው ( የፈጣሪን ሀያልነት ረስቼ አይደለም)፡፡ ያም ሆነ ይህ አማራን እያሳደዱ መመካከር፤ ማስነገር ጊዜው አልፎበታል፡፡ የአማራ ህዝብ ከዚህ በፊት በወለጋ፣ በመተከል፣ በሀረርጌ፣ በአርሲ፣ …. ሲጨፈጨፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ጭፍጨፋው ቤቱ በር ላይ ነው፤ይ የማንክደው ሀቅ ነው፡፡ ለህልውና መታገል ደግሞ ፈጣሪም ዓለም አቀፍ ማህበረሰብም የሚደግፈው ነው፡፡ ሕዝብ ማሸነው አይቻልም የአማራ ህዝብ ትግል ለእውነት፣ ለፍህ፣ ለለውጥ ነው፡፡
15 62419Loading...
13
Media files
12 29310Loading...
14
ማጭበርበሪያ ነው! ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ትህነግ/ህወሓት የተናገረው ማጭበርበሪያ ነው። 1) ያፈነገጠ ኃይል አይደለም። ጌታቸው ረዳ፣ ታደሰ ወረደ፣ ደብረፅዮን የሚመሩት፣ የሚስማሙበት አንድ ኃይል ነው ያላቸው። ራያን ሲወርሩ ጌታቸው ረዳም፣ ታደሰ ወረደም ናቸው መግለጫ የሰጡት። ታጣቂው የትህነግ ነው፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩም ነው። ተሰብስበው፣ መክረው፣ መግለጫ አውጥተው ነው ወረራ እየፈፀሙ ያሉት። 2) "የፌደራል መንግስት" ኃላፊነት ትጥቅ መፍታት አለባቸው እያለ ማላዘን አይደለም። ኃላፊነቱ ትጥቅ ማስፈታት ነው። በሰላም ስምምነቱ ትጥቅ አስፈታ ቢባልም እንዳይፈቱ ያደረገው ራሱ ነው። እንዲያውም ተጨማሪ ትጥቅ እንደሰጣቸው የውስጥ ምንጮቻቸው እየተናገሩ ነው። እውነታውም ይታወቃል። 3) ትህነግ ትጥቅ እንዲፈታም የብልፅግና ፍላጎት አይደለም። አማራን ይወጋልኛል ብሎ ያቆየው ነው። ሰሞኑን ራያ ላይ ትህነግ ወረራ ያደረገው በብልፅግና ፍላጎት እንደሆነ የፖለቲካና ወታደራዊ መሪዎቻቸው፣ አክቲቪስቶቻቸው በግልፅ ነግረውናል። በተወረሩት ከተሞች የትህነግ ታጣቂ ከመከላከያ ጋር እንደሚውል የትህነግ ሰዎች እየፃፉ ነው። አፈንጋጭ አይደለም። 4) ከሰላም ስምምነቱ ያፈነገጠውም፣ ትህነግን ትጥቅ እንዳይፈታ፣ አማራን እንዲወር የሚያደርገውም ብልፅግና ነው። አፈንጋጭ፣ ትጥቅ ይፍታ ወዘተ የሚሉት ለማዘናጋት፣ ተጠያቂ ላለመሆን፣ አልኩ ለማለት ነው። ማጭበርበሪያ ነው! 5) ከ50 ሺህ በላይ ህዝብ ተፈናቅሎ፣ አርሶ አደሩ በሩ ላይ እየተገደለ፣ ሀብትና ንብረቱ እየተዘረፈ፣ ከተሞች እየተራቆቱ ብልፅግና አንድም ነገር ያላለው ብልፅግና እና ትህነግ/ህወሓት ባደረጉት የጓዳ ውል የተፈፀመ ወረራ በመሆኑ ነው። ጦርነት የሚፈልግ ሳይሆን አማራ ላይ ጦርነት የከፈተ፣ ትግራይ ውስጥ ሳይሆን አማራ ላይ ጦርነት የከፈተ ኃይል ሆኖ እያለ ብልፅግና ትግራይ ውስጥ ጦርነት የሚፈልግ ወዘተ እያለ ያጭበረብራል። ውሸት ነው! ማጭበርበሪያ ነው!
12 6485Loading...
15
Media files
16 4178Loading...
16
የትህነግ ታጣቂ ራያ ላይ እየፈፀመው ያለው ሰቆቃ በገለልተኛ ሚዲያ እይታ! ከስር ያለው መረጃ ዓል አይን አማርኛ የትህነግ ታጣቂ እየፈፀመው ያለውን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃ በወረራ ስር ያሉትን ነዋሪዎች አናግሮ ከዘገበው የተወሰደ ነው። #የትግራይ ታጣቂዎች ከመጡበት ዕለት አንስቶ ንብረታችን እየተነጠቀ ነው፡፡ ለገበያ የደረሰ ሀብ ሀብ አትክልቴን በልተውብኛል ሲጠግቡ ደግሞ በያዙት ጦር መሳሪያ በሰደፉ እና በአፈሙዙ እየመቱብኝ ነው” #በቀበሌያችን ከገቡበት ከሰኞ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በገበሬው ቤት እየገቡ እየደበደቡን ነው። አርሶ አደር ጦር መሳሪያ አምጡ እያሉ እኛ ገበሬዎች ነን ፖለቲካ አናውቅም ብንልም ሊተውን አልቻሉም" #ከዚህ በፊት አብረውን ይኖሩ የነበሩ ነገር ግን በስጋት ምክንያት ወደ ትግራይ ተፈናቅለው የነበሩ ሰዎች ካሳለፍነው ሰኔ እና ግንቦት ወር ጀምሮ እየገቡ መኖር ጀምረዋል፣ ሳይገቡ የቀሩት ከዚህ በፊት በነበረው አስተዳድር ጊዜ ህዝብን ሲያንገላቱ እና ሲያማርሩ የነበሩት ብቻ ቀርተው ነበር" #ታጣቂዎች ሲቪል እየለበሱ ወደ ከተማዋ ነዋሪ መስለው እየገቡ ነው፣ የመንግስት ተቋማትን እየዘረፉ እና ፋይሎችን እያወደሙ የከተማዋ ነዋሪዎችንም ፍርሃት ውስጥ እንዲገባ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ነው። በከተማዋ ያለው የፌደራል የጸጥታ ሀይል ቢኖርም ነዋሪውን ከመሰደድ አልታደገውም" #የፌደራል መንግስት ለራያ እና አላማጣ ጉዳይ ዘለቄታዊ መፍትሔ ይሰጠዋል ብለን እየጠበቅን ለትግራይ ታጣቂዎች አሳልፎ ሰጥቶናል። #በሰሌን ውሃ ቀበሌ የሚኖረው ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በበኩሉ የትግራይ ታጣቂዎች የራያ እና አላማጣ የገጠር ቀበሌዎችን ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መቆጣጠራቸውን፣ በየቀኑ አዳዲስ እና ተጨማሪ ታጣቂዎች ወደ አካባቢዎቹ እየገቡ መሆኑን አክሏል፡፡ ታጣቂዎቹ በየሰው ቤት እየገቡ የልጆችን ምግብ ሳይቀር እየበሉ እንደሆነ፣ ለባሏ የምሳ እቃ ለማድረስ ወደ እርሻ ቦታ እየሄደች ያለችን እናት ለአማራ ታጣቂ ልትሰጪ ነው በሚል እያንገላቱ ነው ያሉት እኝህ አስተያየት ሰጪ ታጣቂዎቹ ይህን ሲያደርጉም የፌደራል የጸጥታ ሀይሎች እያዩ የማስቆም ፍላጎት እንደሌላቸውም ነግሮናል፡፡ #ከዚህ በፊት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ወደ መቀሌ እና ሽሬ የሄዱ ነዋሪዎች ወደ ቀድሞ ቤታቸው ተመልሰው አብረን በጋራ እያረስን እና እየኖርን ቢሆንም ታጣቂዎቹ በድንገት መጥተው ለእንግልት እንደዳረጓቸውም አክሏል፡፡ #ታጣቂዎቹ በየጊዜው እየሰበሰቡም ከእንግዲህ እምናስተዳድራችሁ እኛ ነን፣ የያዛችሁትም የአማራ ክልል የነዋሪነት መታወቂያ ከእንግዲህ አይጠቅማችሁም፣ ልጆቻችሁን አምጡ እና ለአማራ ታጣቂዎች ድጋፍ እያደረጋችሁ ነው የሚሉ ወከባዎችን እያደረሱባቸው እንደሆነም እኝህ አስተያየት ሰጪ ተናግረዋል፡፡ #ወቅቱ የሚያዚያ ወር አዝመራ የምናዘምርበት ቢሆንም እርሻችንን ትተን በየቀኑ ምን እንሆን ይሆን የሚል ስቃይ ውስጥ ነን"
17 1329Loading...
17
Media files
16 1706Loading...
18
ተፈናቃይ ብለው የሚያስገቡት ይህንን ዘራፊ ኃይል ነው! ትህነግ በወረራው ወቅት አማራና አፋርን መዝረፍን ጀብዱ አድርጎ ለወጣቱ አስተማረው። አትክልትና ፍራፍሬ ጭምር "ከአማራ ክልል የመጣ" እየተባለ በሞንታርቦ እየተጮኸ ሲሸጥ ነበር። የአማራ ክልል ታርጋን አንስተው ታርጋ አልባ መኪና የሚነዱት "አምጥቶ ነው" እየተባሉ በጀብድ ተነገረላቸው። እርጉዝ ሳይቀር ለዘረፋ መጥታ አማራ ወልዳ ተይዛለች። ወጣቱ "እኔም ይህን አምጥቻለሁ" እያለ በጀግንነት እንዲያወራ ተደረገ። ከጦርነቱ በኋላ ግን ዘረፋውን ትግራይ ውስጥ ቀጠሉት። አማራ ላይ ጀግና የተባሉበት ነዋ! የቀራቸው ነገር የለም። ፍርድ ቤት ስላልቻለ እንደ ድሮው በአደባባይ በዚህ መልክ መቅጣት ጀምረዋል። ታዲያ ወደ ራያ የላኩት ይህን ዘራፊ ኃይል ነው። አዲስ ልብስና ጫማ ሳይቀር እያስወለቀ ሲወስድ የሚታወቅ ዘራፊ ራያን እያራቆተ ነው። በወረራው ወቅት ሲዘርፍ ጀግና ያሉትና ከወረራ በኋላ ትግራይን ያስመረረውን ነው ወደ ራያ የላኩት። ወደ ጠለምትና ወልቃይትም ለማስገባት የወሰኑት ይህ ሰው በላ የሆነን ኃይል ነው።
13 8993Loading...
19
Media files
19 5644Loading...
20
አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም! ማፈናቀል ነው! እየተተገበረ ያለው የጓዳ ውል እንጅ የሰላም ስምምነት አይደለም! ተፈናቃይ በመመለስ ሰበብ ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን አፈናቅለዋል። ድሮም ይህ ነው የሚባል ተፈናቃይ አልነበረው። ወደራያ አካባቢዎች የገባው የትህነግ ገዳይና ዘራፊ ታጣቂ፣ ትግራይ ውስጥ በወንጀል ያስቸገራቸው ዘርፎ እንዲሄድ የተደረገ ኃይልና የትህነግ መዋቅር ነው። ሁሉም ከመግደል፣ ከመዝረፍና ከማፈናቀል ውጭ መጀመሪያ የተባለውን ተፈናቃይ መመለስ ሲናገሩ አይሰሙም! አላማቸውም በቀል፣ ዝርፊያና ርስት መቀማት እንጅ ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። እንደ አንድ ጠላት ብለው እንደፈረጁት አካባቢ መግደል፣ መዝረፍና ማሳደድ ነው የተያያዙት። የያዙት አካባቢ ሀብትና ንብረት ወደ ትግራይ እየተጫነ፣ መጫን ያልቻሉትን እያወደሙ ነው። አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። ማፈናቀል ነው። ትህነግ በቀሉን ይወጣል። አብይ ለምዕራባውያኑ "የአማራን ግዛት ሰጥቻቸዋለሁ" ብሎ እርዳታ ይለምናል። አላማው የጓዳው ውል ማስፈፀም እንጅ በአደባባይ በመግለጫ የሚነግሩን ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። አብይ በአማካሪዎቹ በኩል በአንድ ስልክ ትዕዛዝ ፀጥ ረጭ የሚያደርገው ብአዴን ደግሞ ይህ ሁሉ እየተፈፀመ እንዳላየ ዝም ብሏል። አንድ ቀን የሰጣት መግለጫ እንኳን ቁጣ አስተናግዳበት ከዛ በኋላ ይህ ሁሉ ህዝብ ሲፈናቀል ትንፍሽ አላለም።
17 8276Loading...
21
Media files
15 3375Loading...
22
አርበኝነት ምልክቱም ወንጀል ሆኗል! በተለያየ የጥበብ ስራ ስለ አርበኝነት መስራት በአገዛዙ ከፋኖ ጋር እየተገናኘ ወንጀል ተደርጓል። አሁን ስለ አርበኝነት መስራት ብቻ ሳይሆን ከአሁን ቀደም የሰሩትም እንደ ወንጀል ተቆጥሮባቸው እየታሰሩ ነው። በአቦል_ቲቪ ዲ ኤስ ቲቪ ኢትዮጵያ ላይ "ገብርዬ" በተሰኘው ተከታታይ ፊልም ዋና ገፀባህርይ የሆነውን ፊታውራሪ ገብርዬን ሆኖ የተወነው ሰለሞን እውነቱ ከታሰረ ሁለት ወራቶችን እንዳስቆጠረ የተዋናዩ የቅርብ ወዳጆቹ ገልፀዋል። በተመሳሳይ አርቲስት አማኑኤል ሰሞኑን የታሰረ ሲሆን ስለ አርቲስቱ ፅፈሃል በሚል ያያ ዘልደታም ለእስር ተዳርጓል። አርቲስቶቹ በተለያየ ጊዜ የአርበኝነት ገፀባህርይ ተላብሰው የሰሯቸው ፊልሞች ጭምር እንደ ወንጀል ተቆጥረው፣ በባለ ጊዜ የአገዛዙ የስነ ጥበብ ሰዎችና አክቲቪስቶች ጥቆማ ለእስር እየተዳረጉ ነው። ያለ ምንም ወንጀል የወከሉት የአርበኝነት ምልክት ወንጀል ተደርጎባቸው ለሚታሰሩት አርቲስቶች ድምፅ መሆን ያስፈልጋል።
14 21110Loading...
23
Media files
14 1819Loading...
24
ጥብቅ ሚስጥር ነው! ዳንኤል ብርሃኑ ወደ ምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል ነው ያደገው። ሌሎች የትህነግ ሰዎች ለመግለፅ የማይደፍሩትን ሚስጥር ዘረገፈው! የችግሩ ምንጭ ይህ አካሄድ ነው! 1) ትህነግ ስምምነቱ በተለይም ትጥቅ ማስፈታቱን ጨምሮ ሌሎችን በጓዳ ውል እንዲዘገይ ያደረገው በእርዳታና ብድር መሆኑን በራሱ ተሞክሮ ይነግረናል። ዳንኤል የአውሮፓውን ዲፕሎማት በብድርና እርዳታ ጫና አድርገልን ያለው በራሱ ተነሳሽነት አይደለም። የዋናው ትህነግ መጫዎቻ ስለሆነ ነው። የኦሮሞ ብልፅግና ካለው ፀረ አማራ ፍላጎት ባሻገር፣ ትህነግ ትጥቅ መፍታቱንም ሌላውንም በጓዳ ውል ያስቆየው በዚህ መንገድ ነው። ዲፕሎማቶች በየቀኑ ወደ መቀሌ ሲመላለሱ ለዚህ እንደሆነ ብልፅግና ያውቃል። ፍላጎቱም ነው። 2) ዲፕሎማቶቹም ሌላ ጥያቄ ሲጠየቁ ያለምንም ማወላዳት "ትጥቅ አትፈቱም" የሚሉት የትህነግ የመጀመሪያ ፍላጎት እንደሆነ ስለሚያውቁ ነው። ብልፅግናም በጓዳ የተዋዋለው፣ የአማራን ርስቶች ለብድርና እርዳታ ቀብድ ያደረጋቸው መሆኑን ማሳያ ነው። 3) ሰሞኑን ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት የአማራን ርስቶች አሳልፎ የመስጠት የአብይ አህመድ እና የትህነግ የጓዳ ውል ተግባራዊ እንዲሆን የሚደረገው አብይ ብድርና እርዳታ ሲፈልግ፤ የሞቀ ድርድር ላይ ሲሆን ነው። የሰሞኑ የራያና የሌሎች አካባቢዎች ወረራ አብይ ከዓለም የገንዘብ አበዳሪዎች ጋር ሲደራደር የተፈፀመ ነው። ዳንኤል ያወጣው ሚስጥርም ከዚሁ ጋር የተገናኘ ነው። 4) እየተተገበረ ያለው የሰላም ስምምነት አይደለም። አብይ የአማራን ርስቶች በብድርና እርዳታ፤ በጓዳ ውል ከሰላም ስምምነቱ በተቃራኒ አሳልፎ ነው እየሰጠ ያለው። ዳንኤል በግልፅ ተናገረው እንጅ የምናውቀው ነው። ዳንኤል ያወጣው ዲፕሎማቶቹ በትህነግ የሚነገራቸውንና እየሆነ ያለውን እውነታ ነው። ይህ ቀላል ጉዳይ አይደለም። ጥብቅ ሚስጥር ነው!
14 96713Loading...
25
Media files
17 97310Loading...
የሚገርሙ፣ የሚያሳዝኑም ጉዳዮች ናቸው! 1) የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ውጭ ተንቀሳቅሶ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ራሱ ጌታቸው ለትግራይ ሕዝብ ተናግሯል። ትግራይን የሚያስተዳድረው ከጦርነቱ በፊት የነበረው፣ ወንጀለኛ የተባለው መዋቅር ነው። ይህን ጌታቸው ረዳ በሚዲያ ወጥቶ ያረጋገጠው ነው። ይህ ህገወጥ መዋቅር ስለሆነ ነው ጊዜያዊ አስተዳደር ማዋቀር ያስፈለገው። ትግራይ ውስጥ ከመቀሌ ውጭ ስብሰባ እንኳ ማድረግ የማይችለው የጌታቸው ረዳ አስተዳደር፣ በህጋዊ ስምምነት የተሰጠውን ትግራይን እንዳያስተዳድር ተደርጎ፣ በማያገባው ከትግራይ ውጭ ያሉትን የአማራ ግዛቶች እንዲያስተዳድር ነው የተደረገው። ሰሞኑን ትህነግ በወረራቸው የአማራ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደሩ መዋቅሩን አሰማርቷል። ትህነግ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ የፈቀደለት የወረራ አላማ ስለሆነ ነው። ትግራይ ውስጥ አንድም ቀበሌ እንዳያስተዳደር የተደረገው ጌታቸው የአማራን አካባቢዎች ግን በህገወጥ መንገድ እንዲይዝ ተደርጓል። 2) ሰሞኑን በትግራይ ፖለቲካ አጀንዳ የሆነ ጉዳይ አለ። ትህነግ የአማራ አካባቢዎች ተወልደው ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደላችሁም" እንዳላቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ረዳኢ ሓለፎም ቃል በቃል ተናግሯል። የትግሬ ካባ የሚሰጠንም የሚቀማንም ሌላ ቡድን አለ ብሏል። የአድዋውን ቡድን ነው። ታዲያ ራያ ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደሉም። ባንዳ ናቸው።" ወዘተ እያለ የሚፈርጅ ራያን መሬቱንና መሬቱን ብቻ እንደሚፈልግ ግልፅ ነው። አመራሮቹን በጠላትነት የፈረጀ ለሕዝቡማ ያለው ጥላቻን መገመት ቀላል ነው። በተደጋጋሚ በተግባርም የታየ ነው። 3) ራያን የወረረው የትህነግ ታጣቂ "አርሚ 24" ይባላል። መከላከያን በመታበት ጥቅምት 24 የተሰየመ ነው። መከላከያ የተገደለበትን ቀን ማስታወሻ ያደረገውን ኃይል ነው እያገዘ የሚገኘው። 4) የሰላም ስምምነቱ ያለ ምንም ማወላዳት የደነገገው፣ የጊዜ መንዛዛት ያልተቀመጠበት የትጥቅ መፍታት ነው። በማያሻማ መልኩ በአንድ ወር ውስጥ ትጥቅ ይፍቱ ተብሎ ነበር። ጭራሽ አስታጠቋቸው። መከላከያ ትግራይን ይረከብ ተብሎ ነበር። ጭራሽ መከላከያ ከትግራይ ወጥቶ አማራ ላይ ዘምቶ፣ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ትህነግ አማራ ክልልን በኃይል እንዲይዝ ተደረገ 5) ትህነግ ባለፉት ወረራዎች ዘረፋ የሚፈፅሙትን በየጦሩ አደራጅቶ አሰማርቷል። በዘረፉት ልክ ጥቅም አግኝተዋል። እንደ ጀግና ታይተዋል። ይህ ኃይል ግን ወደ ትግራይ ተመልሶ አረመኔ ሆነ። የአርሶ አደር በሬ አርዶ መብላት፣ የተቋማትን ብረታብረት መዝረፍ ወዘተ። ሰሞኑን የትግራይ ክልል ውሃ መሳቢያ ብረቶች እየተዘረፉ መሆኑ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ይህን የራሴ የሚለውን ትግራይን እየዘረፈ ያለ ኃይል ነው ጠላቴ ወደሚለው አማራ ይዘውት የመጡት። ከራያ ብቻ ከ50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለውም ይህ አረመኔ ኃይል በሚፈፅመው ወንጀል ምክንያት ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው አማራ ላይ ነው!
Show all...
የወረራ ዝግጅት! ራያን የወረረው ትህነግ ጠለምትንና ወልቃይትን ለመውረር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በሱዳን በኩል፣ አርሚ 11 ጠለምትን ለመውረር፣ አርሚ 17 ወልቃይትን ለመውረር ዝግጅት ላይ ነው፣ አርሚ 35 ከአክሱም ወደ ሽሬ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥቅምት 24 መከላከያን የመቱበትን ማስታወሻ ያደረጉት "አርሚ 24" ደግሞ ራያን የወረረው ነው። ይህ በሆነበት ብልፅግና የአማራ አስተዳደሮችን በሕገወጥ መልኩ አፍርሶ በተፈናቃይ ስም የወረራ በር እየከፈተና እያገዘ ይገኛል። እንደ ገለልተኛ "ትጥቅ መፍታት አለባቸው" እያለ የሚቀልደውም ዝግጅታቸውን ስለማያውቅ አይደለም። ማዘናጊያ ነው። በሌላ በኩል በተቃዋሚም ሆነ በሌላ ስም ትህነግ ጋር ስምምነት ለመፈፀም የሚደረግን ሂደት የህዝብ ለህዝብ እያስመሰለ፣ የትህነግን ወረራ የሚያድበሰብስም የትህነግና ብልፅግናን የጓዳ ውልና የወረራ አላማ የሚያስፈፅም የአማራ ጠላት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
Show all...
01:27
Video unavailableShow in Telegram
ያዘዝነውን ካላስፈፀመ መከላከያንም እናቀምሰዋለን ብለዋል! በአማርኛ ነው! ቀጥታ ትዕዛዝ ነው! ሰሞኑን ትህነግ ባደረገው ሰልፍ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር መከላከያ በተገኘበት በአማርኛ ጭምር ያስተላለው ዛቻ ነው። መከላከያ የምንፈልገውን ካላስተገበረ ሱሪያችን ያውቃታል። ይቀምሳል ተብሏል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር የአማራን ርስቶች ለመያዝ ህፃናትና አዛውንቶች ይዘን እንደማንመጣ ይታወቃል ብሏል። እንዳሉት ተፈናቃይ ይዘው አልመጡም። ታጣቂ ነው ይዘው የመጡት። መከላከያም ባዘዝነህ መልኩ ካልሰራህ ሱሪያችን ታውቃታለህ ተብሏል። ይህ ጌታቸው ረዳ የሚያዘው ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር ነው።
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
ትህነግ የጓዳ ውሉን ይፋ አደረገው! ትህነግ በጀኔራል ታደሰ ወረደ በኩል የጓዳ ውሉን በማያሻማ መልኩ ይፋ አድርጓል። ብልፅግና ጠለምትና ራያን በቅርቡ፣ ከዛም ወልቃይትን አሳልፎ ለመስጠት የተዋዋለበትን በይፋ ተናግሯል። ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን በትህነግ ታጣቂ ከራያ የተፈናቀሉት በጓዳ ውሉ መሰረት እንደሆነ ይታወቃል። አማራ እየተወረረ ያለው በጓዳ ውሉ መሰረት ነው። የብልፅግና አመራሮች ስለ ትህነግ ትጥቁን መፍታት ወዘተ ሲያወሩ "ውሸታቸውን ነው" የምንለው በምክንያት ነው። ጦርነት የሚፈልግ ኃይል ወዘተ እያለ የሚያወግዙ የሚመስሉት ውሸት ነው። የአማራን ግዛቶች አሳልፈው ለመስጠት የተዋዋሉት በወረራ መሆኑ ይፋ ወጥቷል። ታደሰ ወረደ ብልፅግና አማራን በኃይል እንዲይዙ የሰጣቸውን ድጋፍና ፈቃድ በሚዲያ ወጥቶ ሲገልፅ ይህ ሁለተኛ ጊዜው ነው። እነ ተመስገን ጥሩነህ "ያፈነገጠ ወዘተ" እያሉ ሀሰት ሲናገሩ፣ ጀኔራል ታደሰ በይፋ መጥቶ ከብልፅግና ጋር የተዋዋሉት የጓዳ ውል መሆኑን እየገለፀ ነው። አማራን በትህነግ እያስወረረ የሚገኘው ብልፅግና ነው። ትህነግ ባለፈው በጌታቸው ረዳና ታደሰ ወረደ፣ ዛሬም በታደሰ ወረደ በኩል ወረራው ከብልፅግና ጋር በተስማሙት መሰረት የተደረገ እንደሆነና እንደሚቀጥል ሲገልፅ ብልፅግና ትንፍሽ አላለም። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደሮች ናቸው ወረራው በስምምነት የተፈፀመ መሆኑን የሚናገሩት። ያፈነገጠ ወዘተ የሚባለው ነጭ ውሸት ነው። ማዘናጊያ ነው። የጓዳ ውሉን ማድበስበሻ ነው!
Show all...
00:52
Video unavailableShow in Telegram
ሬዲዮው የትህነግ/ህወሓት ባትሪ ሳይጎርስ!
Show all...