cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Getachew shiferaw

Show more
Advertising posts
45 081Subscribers
-3524 hours
-3097 days
-42130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

"የአማራ ሕዝብ ወሰንና ማንነት ጉዳይ በሕልውና ትግሉ ሂደት ቀይ መስመር ነው!" ፋኖ
Show all...
የሰላም ስምምነት የተፈራረመውም፣ ሰላም አስፍነናል ብሎ ድግስ የከረመውም "የፌደራል" ብልፅግና ነው። ጦርነት ሲከፈት መጀመሪያ መግለጫ መስጠት ያለበት እሱ ነው። ለድግሱ ከፊት ከርሞ፣ ለጓዳ ስምምነት ሲባል ናዝሬት ጠርቶ አስተናግዶ አሁን አማራ ክልል የጎን መግለጫ አሰጥቶ ዝም ሊል አይችልም። የአማራን ግዛቶች አሳልፎ ለመስጠት "የኢትዮጵያ መሬቶች ናቸው። ፌደራል ያስተዳድራቸዋል" ይላል። ወረራ ሲፈፀም "ራሳችሁ መግለጫ አውጡ" ብሎ ይሸሻል። እውነታው አላማቸው አማራው ማስወጋት ስለሆነ ነው! ስምምነቱ ሲጣስ መግለጫ መስጠት ያለበት የፌደራሉ አገዛዝ ነው! ስትጨባበጥ ከርመህ፣ ትጥቅ እንዳይፈታ አድርገህ አሁን አማራን ሲወጋ ክልሉ መግለጫ ያውጣ ልትል አትችልም። ሰላም እየፈጠርን ነው ብለህ ለዓለም እንዳወራኸው ሁሉ፣ ሲጣስም ለዓለም መንገር ያለብህ ራስህ ነህ። የሰላም ጊዜ ከፊት፣ ሲጣስ በጎን መግለጫ አይሆንም።
Show all...
አላማጣ አዳሩን ንፁሃንን ሲገድል፣ በርካቶችን ሲያፈናቅል ያደረው ኃይል የደቡብ አፍሪካው ስምምነት በተፈረመ በወር ውስጥ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ነው። አብይ አህመድ ትጥቅ እንዳይፈታ አደረገው! ተፈናቃይ ስለመመለስ ኮሚቴ አዋቅሮ ያለ ፀጥታ ኃይል፣ ያለ ትህነግ መዋቅር ይመለሳል ብሎ መግለጫ በሰጠ በሳምንቱ የትህነግን ታጣቂ ንፁሃንን እየገደለ እንዲገባ ማገዝ ብቻ ሳይሆን መከላከያ የትህነግ ወረራ የተከላከሉትን አማራዎች ገደለ። የትህነግ ሰዎች በይፋ በአብይ አህመድ ድጋፍ ነው የገባነው ብለዋል። የትህነግ ታጣቂ ባለፉት ቀናት ጦርነት ከፍቶ ንፁሃንን ሲገድል ነው የሰነበተው። በአጭሩ አብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ በአማራ ላይ ይህ ወረራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ የሰጡ ናቸው። ንፁሃን የተገደሉት፣ የተፈናቀሉት፣ የተዘረፉት በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ትዕዛዝ፣ በብልፅግና እና ትህነግ/ህወሓት የጓዳ ውል ነው። በተረፈ ትህነግ ወዳጅ ይሆናል ብላችሁ የምታስቡ ካላችሁ እርማችሁን አውጡ። ትህነግ ከብልፅግና ጋር ነው የሚሰራው። በጋራ ነው የወረሩን። አማራን ለመውረር ሲመክሩ ከርመው ንፁሃንን እያፈናቀሉ፣ እየገደሉ ነው። ነገ በጋራ ፋኖ ላይም ቢሆን መዝመታቸው የማይቀር ነው!
Show all...
አማራዎች የትህነግ/ህወሓትን ወረራ ተከላከላችሁ ተብለው በብልፅግና ትዕዛዝ ተገድለዋል! የትህነግን ወረራ ለመቀልበስ እየተዋጉ የዋሉ አማራዎችን መከላከያ ገድሏቸዋል። ትህነግን ከእነ ከባድ መሳሪያው ያስገባው መከላከያ የትህነግን ወረራ ሲመክት የዋለውን የአላማጣ ወረዳ አስተዳደር ሞላ ደርበው ገድሏል። ሌሎችም የትህነግ/ህወሓትን ወረራ እንዳይከላከሉ መከላከያ መሳሪያ "አውርዱ" ብሎ ተኩሶባቸዋል። በትህነግ ወረራ ምክንያት በርካቶች የተፈናቀሉና የተጎዱ ሲሆን ለዚህ ተጠያቂው ብልፅግና ነው! አማራ ከደመኛ ጠላቱ የዘር ፍጅትን እንዳይከላከል በብልፅግና ትዕዛዝ እየተጠቃ ነው!
Show all...
ራያ በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ቀጥታ ትዕዛዝ ተወርሯል! ትህነግ/ህወሓት በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ቀጥታ እገዛ ራያን ወርሯል። በጓዳ ስምምነት መሰረት ንፁሃን ላይ ከባደ መሳሪያ ጭምር እየተኮሱ ነው! 1) ወረራ ፈፃሚው በሰላም ስምምነቱ ትጥቅ ይፍታ የተባለ አሁን ብልፅግና በጀት የሚከፍለው የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚያዘው ኃይል ነው። 2) ሰሞኑን ያለ ታጣቂ ተፈናቃይ ይመጣል፣ የፌደራል መንግስቱ ይቆጣጠረዋል ተብሎ መግለጫ ተሰጥቶ ትህነግ በወረራ እንዲይዘው ተደርጓል 3) የጋራ ኮሚቴ ተብሎ የተቋቋመው በቀደም ተገናኝቷል። በጓዳ ስምምነቱ መሰረት ወርራችሁ ያዙ ተብለዋል። 4) የሰላም ስምምነቱ የአማራ ግዛቶች በአማራ ክልል ስር እንዲቆዩ በግልፅ ደንግጓል። 5) አብይ የባህርዳር ሎሌዎቹ አልነበርንም እንዲሉ ወደ አሜሪካ እንዲሄዱ አድርጎ ነው ያስወረረው።
Show all...
ብልፅግና በይፋ ከኢራን ጎን ተሰልፌያለሁ እያለ ነው! ይህ ዘገባ ሆን ተብሎ የተሰራ ነው። ከቱርክ ቀጥሎ ከኢራን ድሮን የሚያገኘው ብልፅግና ውለታውን በፕሮፖጋንዳ እየተወጣ ነው። በዚህ ፍጥነት ከኢራን ጋር መቆሙን የገለፀበት ገራሚ የፕሮፖጋንዳ ዘገባ ነው! 1) እስካሁን በርካታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ከሚገልፁት ውጭ በቁጥር ሁሉ አስቀሞጦ፣ የእስራኤል ስትራቴጅክ ቦታዎች ተጠቁ ብሎ በግልፅ በርዕስ ያስቀምጣል። 2) ይህን የፕሮፖጋንዳ ዘገባውን ታማኒ ለማስመሰል ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እንደዘገቡት አድርጎ ያቀርባል። ዝርዝር ላይ ግን በማስረጃነት የሚያቀርበው የኢራንን የፕሮፖጋንዳ ቻናል ነው። 3) ጦርነቱ የሁለቱ አገራት ሆኖ ርዕስ ያደረገው የኢራን ቻናል ላይ የወሰደውን ሆኖ በውስጥ ዘገባው የእስራኤልን ባለስልጣን ቃል በትንሹ አካትቷል። የዘገባው አንጓ ግን ኢራን ስኬታማ ጥቃት እንዳደረገች ማሳየት ነው። ብዙ ጊዜ መሰል ዜናዎች ሲሰሩ የሁለቱም በርዕስነት የሚካተቱበት መንገድ ይገለፃል። 4) ኢቲቪ በትዕዛዝ የዘገበው ባይሆን በዚህ ደረጃ ፕሮፖጋንዳ አይሆንም ነበር። አሊያም ዜናውን ኢራን ይህን ያህል ኢላማ መታሁ አለች ብሎ በዘገብ ይችል ነበር። ይህም ፕሮፖጋንዳን ማስተጋባት ቢሆንም አሁን ከሰራው ይሻለው ነበር። 5) ኢቲቪ በዚህ መንገድ እየዘገበ ያለው የእስራኤል መንግስት በይፋዊ መግለጫ ጥቃቱን መቀልበሱን በገለፀበት፣ የአንድ የኢራን ጣቢያን እንደ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ ጣቢያዎች አድርጎ በርዕስ አጉልቶ፣ ቀባብቶ ነው። ይህ ዓለምን ያሰጋ ጦርነት ነው። ለብልፅግና ደግሞ ትርፍ አለው። ድሮን ያገኝበታል። ለዛም ነው በዚህ ደረጃ የዓለም አቀፍ ጦርነት ላይ ወገንተኝነትን የሚያሳየው። ኢቲቪ የሚሰራው በብልፅግና ቀጥተኛ ትዕዛዝ ነው። አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ደግሞ እያንዳንዱ ዘገባ የፖለቲካ ቃና ተሰጥቶት፣ ከብልፅግና ኃይል ተዋቅሮ እያረመ የሚወጣ ነው። የአገር ውስጡ አልበቃ ሲል ከአለም ጦርነትም አተርፋለሁ ብሎ የሚሰራው ፕሮፖጋንዳ ነው።
Show all...