en
Feedback
ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media

ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media

Open in Telegram

ይኽ የመካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያደርሳል። Join Us: https://t.me/tekletewoflos https://www.instagram.com/tekletewoflos

Show more
1 008
Subscribers
-224 hours
+17 days
-530 days
Posts Archive
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የጽንሰት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኍ!!! በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢ
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የጽንሰት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኍ!!! በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢያቄም ላከው፤ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ጽንሰቷን እና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት እና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው። የተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት On this day, the Lord sent the Archangel Gabriel unto the righteous and exalted Joachim, and Saint Gabriel declared unto him the conception and nativity of the Virgin Mary, who would bring forth the Son of God. Through her, peace and joy shall be granted unto all the earth. Tekle Theophilus Sunday School እንኳን አደረሰን አደረሳችኍ! “ለነገዋ ፡ ቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ ዘመኑን ፡ የቀደሙ ፡ አገልጋዮች ፡ ማፍራት” ብፁዕ ፡ ወቅዱስ ፡ አቡነ ፡ ቴዎፍሎስ ፡ ፓትርያርክ ፡ ዘኢትዮጵያ ተክለ ቴዎፍሎስ Telegram ተክለ ቴዎፍሎስ Instagram ተክለ ቴዎፍሎስ Facebook ተክለ ቴዎፍሎስ YouTube

📌 የቤተሰብ ጥየቃ የተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንክብካቤ እና ግንኙነት ክፍል በቤተሰብ ጥየቃ አሳለፋን የሐምሌ ወር የ 10 ኛ ዙር የቤተሰብ ጥየቃ በመምህር መኮንን ብርሀኑ ቤት
+6
📌   የቤተሰብ ጥየቃ የተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንክብካቤ እና ግንኙነት ክፍል   በቤተሰብ ጥየቃ አሳለፋን የሐምሌ  ወር  የ 10 ኛ ዙር የቤተሰብ ጥየቃ  በመምህር መኮንን ብርሀኑ ቤት ተገኝተን ፈጸምን በቀጣይ ይጠየቅ የምትሉትን ቤተሰብ በውስጥ መስመር አስቀምጡልን ስለምትሰጡን አስተያየት ከልብ እናመሰግናለን ።

“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ" በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን ! በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ! የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ! “ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤ ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡ ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው! ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤ የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣ ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣ በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡ ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤ በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ! ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤ ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው! በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡ በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡ በመጨረሻም በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤ የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

ከቀበሯት ሦስተኛ ቀን በ16ም ዕርገቷ ኾነ፤ እመቤታችንን በጥር ሊቀብሯት ከነበሩት ሐዋርያት መካክል የነበረው ቅዱስ ቶማስ ግን ለተልዕኮ ወንጌል ሀገረ ስብከቱ ነበርና ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ሲመለስ እመቤታችን እንደ ልጇ በታላቅ ክብር፣ በይባቤ መላእክት ስታርግ አይቶ ፤ ‘ቀድሞ ልጅሽ ከትንሳኤው ለየኝ አሁንም ተለየሁ’ ማለት ነው ብሎ ከደመና ሊወድቅ እስኪመኝ ድረስ አዘነ፤ ርኅርኅተ ልቡና እመቤታችን ግን እሱ ብቻ ትንሳኤና ዕርገቷን ለማየት ክብር እንደበቃና እሱንም እንደምትነግረው እያወቀች ማልቀሱን ስታይ አብራው አለቀሰች።ከሌሎቹ ተለይቶ እሱ ብቻ እንዳያትም አበሠረችው የመግነዟን በፍታ ጨርቅም ሰጠችው። ቅዱስ ቶማስም የሰጠችውን ተቀብሎ ምንም ሳይል ሐዋርያት ጋር ሔዶ ‘እመቤታችን እንዴት ኾነች?’ አላቸው። ‘ሞታ ቀበርናት’ አሉት። ‘አዬ ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር? እንዴት ይኾናል አይኾንም! ካላየሁ አላምንም ፤ ” አላቸው። እነሱም ‘ቀድመህ የጌታን ትንሳኤ ተጠራጥረህ ከጎኑ ካላስገባሁ ብለው አስገብተህ እጅህ ተቃጠለ ጌታም ያመንክ እንጂ የተጠራጠርክ አትኹን አለክ፡ አንተ ግን አሁንም የእመቤታችንን መቀበር ትጠራጠራለህ’ ብለው ከመቃብሯ ወስደው መቃብሯን ቢከፍቱት ክቡር ሥጋዋን አጡ፤ ደነገጡ፤ ቅዱስ ቶማስም ‘እኔ እኮ አታምኑኝም ብዬ እንጂ ተነስታለች አርጋለች እኔንም አግኝታኛለች፡ ይኸው በዚህ በፍታ አልነበር የገነዛችኋት’ ብሎ ሰጣቸው ደነገጡ፣ የነገራቸውም እውነት እንደኾነ አመኑ። ለበጎ ነገር ቀናዕያን ሐዋርያት አሁንም ‘እንዴት ቅዱስ ቶማስ ዕርገቷን አይቶ እኛ ሳናይ? እንቀራለን ’ ብለው ልክ በዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ አረገችበት 16ኛው ቀን ድረስ ሱባኤ ገብተው ጾመው ቅዱስ ቶማስ የተገለጠለት ተገልጦላቸዋል።

ምክንያተ ጸዊም 
፨በታሪክ ይህንን ጾም ለመጀመሪያ ግዜ የጾሙት ሐዋርያት ናቸው። ፨የእመቤታችን ዕረፍቷ በጥር 21 ነው። ፨ቅዱሳን ሐዋርያትም የእመቤታችንን ሥጋ ሊቀብሩ ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሔዱ ለምቀኝነት የማያርፉት አይሁድ (ክብር ይግባውና) ል’ጇን ተነሳ እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ (ክብር ይግባትና) እናቱም ተነሳች ብለው ሲያውኩን ሊኖሩ እሷም ገቢረ ተአምራት ስታደርግብን ልትኖር አይደል? ኑ በእሳት እናቃጥላት’ ብለው ከመካከላችው ታዎፋኒያ የሚባል ደፋር፣ አርበኛ አይሁዳዊ ላኩት ፤ እሱም የታዘዘውን ሊያደርግ የአልጋዋን ሸንኮር ሲይዝ መልአኩ እጁን ቆረጠው በእመቤታችንም ትእዛዝ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ የታዎፋኒያን እጅ መለሰለት፤ መልአኩም የእመቤታችንን ሥጋና እስከ መስቀል ድረስ ያልተለየውን ሐዋርያውን እንዲጠብቃት የአደራ ስጦታ አድርጎ የሰጠውን ወንጌላዊውን ባለራእዩን ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስን በመንጠቅ የእመቤታችንን ሥጋ ከዕጸ ሕይወት ሥር አኖረው። ለቅዱስ ዮሐንስም ያኖረበትን አሳየው። ቅዱስ ዮሐንስንም ሐዋርያት ‘እንዴት ኾነች? ’ ሲሉት ከዕጸ ሕይወት ሥር ሥጋዋ ማረፉን ነገራቸው። እነሱም ‘እሱ አይቶ እንዴት እኛ ሳናይ እንቀራለን ? ‘ በሚል መንፈሳዊ ቅናት ለ8ወር የተለያቸውን የእመቤታችንን ሥጋ ከነሐሴ 1 - 14  ድረስ በ2 ሱባኤ (በአሥራ አራት ቀን) ከገነት በፈቃደ እግዚአብሔር ተቀብለው ። ከጌቴሴማኒ ቦታ ቀበሩት። እመቤታችንም ወዲያውኑ እንደልጇ ትንሳኤ በሦስተኛው ቀን ተነሳች።

ፍልሰታ የቃሉ ፍቺ - ፈለሰ ከሚለው ግስ ተመዝዞ- ተሰደደ ፣ ተጓዘ፣ ተለየ ወይንም አረገ ማለት ነው ፨ፍልሰታ - ማለት በጥሬው ጉዞዋ ስደቷ ዕርገቷ የሚለውን ሲነግረን ይኸው በቤተክርስቲያናችን እንደ
ፍልሰታ
የቃሉ ፍቺ - ፈለሰ ከሚለው ግስ ተመዝዞ- ተሰደደ ፣ ተጓዘ፣ ተለየ ወይንም አረገ ማለት ነው ፨ፍልሰታ - ማለት በጥሬው ጉዞዋ ስደቷ ዕርገቷ የሚለውን ሲነግረን ይኸው በቤተክርስቲያናችን እንደተለመደው በመደበኛ የሴት አንቀጽ ለእመቤታችን የሕይወት እናት ድንግል ማርያምን ፍልሰት የተነገረ ነው። ፨የእመቤታችንን የሥጋዋን ፍልሰት ስለምንዘክርበት ‘ጾመ ፍልሰታ’ በማለት እንጠራዋለን፤ ስለ እመቤታችንም ስለምናወሳበት 'ጾመ ማርያም' በመባል በሌላ ስም ይታወቃል። ፨በቤተክርስቲያናችን ከአዋጅ አጽዋማት የዓመቱ የመጨረሻው ጾም ይህ ጾም ነው፤ ጾመ ፍልሰታ (ጾመ ማርያም) ይህም ጾም በጥቅሉ የእመቤታችንን የሥጋዋን ማረግና መለየት የሚያስረዳ እና የሚዘክር ጾም ሲኾን ይኸውም በነሐሴ 1 - 16 ድረስ የሚዘልቅ ነው ።