ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media
Open in Telegram
ይኽ የመካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያደርሳል። Join Us: https://t.me/tekletewoflos https://www.instagram.com/tekletewoflos
Show more1 011
Subscribers
+424 hours
+27 days
-430 days
Posts Archive
+1
እንኳን ደስ አላችኁበያዝነው 2018 ዓ.ም. ተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤታችን ካስተማረቻቸው ተማሪዎች ውስጥ በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተነቻቸውን የ 12ተኛ ክፍል ተማሪዎች በዛሬው ዕለት 30/12/2018 በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ በደማቅ ኹኔታ አስመርቃለች ። ሰንበት ትምህርት ቤታችን በሚከተሉት መስፈርቶች ይህንን ዋንጫ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተበርክተላት ሲኽን መስፈርቶቹም - የሥርዓተ ትምህርቱን በሚገባ መልኩ በማስፈጸሙ - የመጀመሪያ ዙር 12ተኛ ክፍል አስፈታኝ እንደመሆኑ መጠን ሁሉንም ተፈታኝ ተማሪዎች በጥሩ ውጤት በማሳለፉ - በጥቅሉ በ 2018 ዓ.ም. በነበረው ሥርዓተ ትምህርት የተሻለ ተሳትፎ በማድረግ ይህን ዋንጫ ተበርክቶላታል! በድጋሚ ለተማራቂ ተማሪዎች ለወላጆቻቸው ለሰንበት ትምህርት ቤታችንና ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እንኳን ደስ አላችኁ! ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 📌የቴሌግራም ገጽ | TELEGRAM 📌የኢንስታግም ገጽ | INSTAGRAM 📌የቲክቶክ ገጽ | TIKTOK 📌የዩቲዩብ ገጽ | YOUTUBE ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
+7
ዝክረ አብነት ዘጉባኤ ቴዎፍሎስየተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት ትምህርት እና ሐዋርያዊ ተልእኮ ክፍል ከሚሰራባቸው አንዱ የኾነው የአብነት ጉባኤ በትላንትናው ዕለት ማለትም በ17/12/2018 ዓ.ም. በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ 5ኛ የምሥረታ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ያከበረ ሲኾን በዕለቱም እጅግ አስተማሪ መርሐ ግብሮች የነበሩ ሲኾን ከምንወዳቸው መምህራኖቻችን የኔታ ቀሲስ ሙሴ ተሾመ በእንግዳችን መርሐ ግብር ላይ ግለ ታሪካቸውን ያጋሩ ሲኾን ቅኔ በተሰኘ መርሐ ግብር ደግሞ የቅኔ ታሪክና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የነበረውን ጉልህ ድርሻ በቀሲስ ፀሐይ የቀረቡ ሲኾን በሰንበት ት/ቤታችን አባላት ደግሞ የግጥም ፣ መጽሐፍ ዳሰሳ እና ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች የነበሩ ሲኾን በትምህርታቸው ብርቱ ለኾኑትና ለመላው ለአብነት ት/ት ተማሪዎችም ስጦታ ተበርክቷል።
በጅጅጋ አዲስ የሚሠራው የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፈረሰ
ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጅጅጋ ከተማ ያልተጠበቀና አሳዛኝ ድርጊት ተፈጽሟል።
በከተማው አዲስ የተገነባው የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መፍረሱ የታወቀ ሲሆን ትናንት ጉልላቱ እንደተሰቀለ ዛሬ ሕጻናትና ሴቶች በኅብረት በመውጣት እንዲፈርስ ተደርጓል ።
ይህ ድርጊት በአካባቢው ምዕመናን ዘንድ ከፍተኛ ኅዘንን የፈጠረ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ስለዚህ ድርጊት አስቸኳይ ሕጋዊ ማጣራት እንዲያደርጉ ማኅበረሰቡ እየጠየቀ እንደሚገኝ ሀገረ ስብከቱ አስታውቋል።
ምንጭ የሶማሌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት/Somali Diocese Secretary/
#ቤተክርስቲያን #ወቅታዊጉዳይ #የሶማሌሀገረስብከት
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁበነገው የዝክረ አብነት መርሐ ግብራችን ቅኔ በተጋባዥ እንግዳ የሚቀርብ ሲኾን ከዚህ በታች የተቀመጠውን ቅኔ ሰሙንና ወርቁን ተርጉመው ቀድመው በዚህ የአስተያየት መስጫ ሳጥን ለጻፉ 5 ሰዎች በዕለቱ ሽልማት የምንሸልም ይሆናል።
ጉባኤ ቃናአኮ ብእሲት ቤተጉባኤ መካን፣ እስመብዙኃን ተወልዱ ውስተኀምስቱ ዘመን።
ዘአምላኪየመደንግጽ ውእቱ ዘመነ ሳምን ቅኔ፤ ሕጻናት በኢእድሜሆሙ እንተቦ ኩነኔ፤ ምስጢራተ ሰማይ አስናነ እስመ አውጽኡ ኵርጓኔ።
መልካም እድል !▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 📌የቴሌግራም ገጽ | TELEGRAM 📌የኢንስታግም ገጽ | INSTAGRAM 📌የቲክቶክ ገጽ | TIKTOK 📌የዩቲዩብ ገጽ | YOUTUBE ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ተነስታለች!🌹ዛሬ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤ ዕርገቷ ነው፤ 🌹የነቢያት ትንቢታቸው፣ የሐዋርያት ስብከታቸው፣ የሰማዕታት አክሊላቸው፣ የቅዱሳን ተጋድሏቸው፣ የኛ የምዕመናን መጠጊያችን፣ ለሰው ልጆች የባህሪያችን መመኪያ ተነስታለች! 🌹የሕይወት እናቱ እንደ ልጇ እንደ ጌታ ሐዋርያት ሱባኤዋን በጨረሱበት ዕለት፣ ሥጋዋ ከተቀበረበት ወጥቶ እንደ ልጇ ሕይወት ትንሣኤ በ3ተኛው ቀን ተነስታለች! 🌹የሐዋርያት ሱባኤ መልስ ፣ የምዕመናን መማጸኛ፣ ድንግል ተነስታለች ! 🌹የሕይወተ ሥጋ ወነፍስ ፈጣሪ እግዚአብሔር እናቱ ኾና ኃጥአን ማረፏ ድንቅ ኾኖ ሳለ ትንሣኤ ዕርገቷ ግን ግሩምና ልዩ ነው ፤ 🌹ዕርገቷ በተካሔደ ልክ በዓመቱ ፡ ‘እኛስ ዕርገቷን ማየት አይገባንም?’ ብለው ጾም የጀመሩት ቀናዕያን ሐዋርያት ፍጻሜ ሱባኤዋ ድንግልን እሷን በሱባኤያቸው መጨረሻ አገኟት፣ 🌹ነቢያት ትንቢት የተናገሩላት ሐዋርያት በክብር የኖሩለት የጌታ እናቱ እመብርሃን ተነስታለች! 🌹ፍልሰታቸው አንድ ቀን እንዲሆን ሲለምን የነበረው የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእናቱ እናታችን ፍልሰት ጋር በአንድ ቀን በአንድ የኾነለት ሁሉን ምታሰግድለት የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ እመቤት ተነስታለች! 🌹ዕርገቷ አእላፍ መላእክት ባሉበት፣ ንጉሠ ሰማይ ወምድር ባለበት፣ እግዚአብሔር እንደ ልቤ ያለው ቅዱስ ዳዊት እየዘመረ መላእክት እያጀቧት እያመሰገኗት ዐረገች፤ 🌹በዚያ በገነት የሚኖሩ ዛፎ ዘንበል ዘንበል አሉ ለክብርና ገናንቷ አደገደጉ፣ መለኮትን የሚያክል አካል በትንሽ አካሏ የያዘችውን እናቱን ሲያዩ ሰማይና የሰማይና ሠራዊት በሙሉ ተንቀጠቀጠ፣ ሰማይ እጅ ነሳት ንጽሕናዋ ከሰማይ የተሻለ ነበርና፣ አምላክን በመለኮቱ ለመሸከም የተገባች ኾና የተገኘት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተነሳች ዐረገች !!! 🌹እንደ ምልጃዋ ጥግ በሕይወታችን ውስጥ የእርሷንና የልጇን ቃል ላለመስማት ከቀበርንባት መቃብር ልቡናችን ተነስታ በሕይወታችን ኖራ ይዛን እንድታርግ ፈቃዷ ይሁንልን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ክብርና ፍቅር ያሳትፈን!!
እንኳን አደረሳችሁ !!▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 📌የቴሌግራም ገጽ | TELEGRAM 📌የኢንስታግም ገጽ | INSTAGRAM 📌የቲክቶክ ገጽ | TIKTOK 📌የዩቲዩብ ገጽ | YOUTUBE ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
Repost from ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ለዕርገቷ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኍ!!!
በዚች ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ወደ ሰማይ ያረገበት መታሰቢያዋ ኾነ።
የተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤትOn this day, the body of the Virgin Mary, the mother of God, ascended to heaven.
Tekle Theophilus Sunday School
እንኳን አደረሰን አደረሳችኍ!
“ለነገዋ ፡ ቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ ዘመኑን ፡ የቀደሙ ፡ አገልጋዮች ፡ ማፍራት” ብፁዕ ፡ ወቅዱስ ፡ አቡነ ፡ ቴዎፍሎስ ፡ ፓትርያርክ ፡ ዘኢትዮጵያ
