en
Feedback
The Christian News

The Christian News

Open in Telegram

ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት። @TCNEW

Show more
5 291
Subscribers
-724 hours
-77 days
-1030 days
Posts Archive
አማኞች በዚህ ዘመን ስለ ፈውስ ደፍረው ለመናገር ይቸገራሉ። እኔ ግን ምስክር ነኝ https://www.youtube.com/watch?v=4LFnmP76EoM&t=570s

አማኞች በዚህ ዘመን ስለ ፈውስ ደፍረው ለመናገር ይቸገራሉ። እኔ ግን ምስክር ነኝ https://youtu.be/4LFnmP76EoM

"ድምጽ አልባው ሞገድ" በድምቀት ተመርቋል። በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች እና ምሩቃን ማህበር (Evasu) አዘጋጅነት እግዚአብሔር በተማሪዎች አገልግሎት ዉስጥ እያለፈ በሀገር እና በቤ
"ድምጽ አልባው ሞገድ" በድምቀት ተመርቋል። በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች እና ምሩቃን ማህበር (Evasu) አዘጋጅነት እግዚአብሔር በተማሪዎች አገልግሎት ዉስጥ እያለፈ በሀገር እና በቤተክርስቲያን ውስጥ የሰራዉን ድንቅ ስራ የሚተርክ መጽሐፍ በድምቀት ተመርቆ ለንቧብ በቃ። በ50 ዓመት የተዋቀረው እና በቅርብ ጊዜ ወደ ጌታ በሄደው ተወዳጁ ጽሐፊ እና አርታኢ ወንድዬ አሊ የተዘጋጀው ይህ መጽሀፍ በከፍተኛ ትምርት ተቋማት ፤ በኮሌጆች እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ያለፉ የክርስቲያን ተማሪዎችን እንቅስቃሴ ከምስረታው አንስቶ ባለፉት አምስት አስርት አመታት ውስጥ የነበረውን ጉዞ የሚተርክ እንደሆነ በመድረኩ ተጠቅሷል። በኢንተርናሽና ኢቫንጀሊካል ቸርች (IEC) በነበረው የምርቃት ስነ-ስረዓት የቀድሞ የማህበሩ አመራሮች ፤ ተማሪዎች እና ምሩቃንን ጨምሮ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ እህት ረቂቅ እና የአምላክ ቸርነት ከመፅሐፊ የተቀነጨበ ሃሳብ ያነበቡ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የከፍተኛ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኑ እና የቀድሞ ምሩቃን መካከል የህይወት ምስክርነት ሲሰጡ ጋሽ ንጉሴ ቡልቻ የእግዚአብሔር ቃል በማካፈል አገልግለዋል። ከ300 በላይ ገጾችን የያዘው እና በ15 ምዕራፎች ተከፋፍሎ የተዋቀረው "ድምጽ አልባው ሞገድ" በወቅቱ ድምጽ ከነበረው ሞገድ በተቃራኒ እንዴት በብዙ አቅጣጫ እግዚአብሔር ይጠቀምበት የነበረ ማህበር እንደነበር በማህበሩ ውስጥ ያለፉ ብዙዎች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። በዮሐንስ ግርማ

ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን! 🤲 🤲 🤲 ዛዶግ ፐርዝ የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ጊዜ በZadok Perth International Ministry እየተዘጋጀ በወንድም ተመስገን ነጋሽ በZadok Perth Youtube የሚቀርብ ተከታታይ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት ሙሉ ትምህርቱን ኮሜንት ስር ያገኙታል።

ሰባት ወር ሙሉ ተሰቃየው l 37 ኪሎ ደርሼ ነበር የፓስተር ደረጄ ድንቅ የህይወት ምስክርነት ይመልከቱ 🔥🔥 https://youtu.be/hBzvSRXys-U?si=l7FooZhnw7VNIeHe

ሰባት ወር ሙሉ ተሰቃየው l 37 ኪሎ ደርሼ ነበር የፓስተር ደረጄ ድንቅ የህይወት ምስክርነት ይመልከቱ 🔥🔥 https://www.youtube.com/watch?v=hBzvSRXys-U

ሰባት ወር ሙሉ ተሰቃየው l 37 ኪሎ ደርሼ ነበር የፓስተር ደረጄ ድንቅ የህይወት ምስክርነት Sina podcast S1 E2 Part 01 https://www.youtube.com/watch?v=hBzvSRXys-U

የኢትዮጵያ አማኑኤል ሕብረት ቤተክርቲያን የመሪዎች ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደች ነው። በጉዲና ቱምሳ የስልጠና ማዕከል እየተካሄደ የሚገኘው ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሃምሌ 7 እና 8 የሚካሄድ ሲሆን በጉባኤው የ
የኢትዮጵያ አማኑኤል ሕብረት ቤተክርቲያን የመሪዎች ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደች ነው። በጉዲና ቱምሳ የስልጠና ማዕከል እየተካሄደ የሚገኘው ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሃምሌ 7 እና 8 የሚካሄድ ሲሆን በጉባኤው የ2018 ዓ.ም የስራ ሪፖርት እና የ2019 ዕቅድ ጨምሮ የተለያዩ አጀንዳዎች ቀርበው እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።

ያልተነገሩ ነገር ግን የተኖሩ እውነተኛ የህይወት ምስክርነቶች እና አስተማሪ መልዕክቶች እንዳያመልጣችሁ። በክርስቲያን ዜና እየተዘጋጀ በየሳምንቱ የሚቀርበውን ተወዳጅ ሲና የተሰኘውን ፕሮግራም አጫጭር
ያልተነገሩ ነገር ግን የተኖሩ እውነተኛ የህይወት ምስክርነቶች እና አስተማሪ መልዕክቶች እንዳያመልጣችሁ። በክርስቲያን ዜና እየተዘጋጀ በየሳምንቱ የሚቀርበውን ተወዳጅ ሲና የተሰኘውን ፕሮግራም አጫጭር  መልዕክቶች ከInstagram ይመልከቱ! follow ማድረጋችሁን አትርሱ። https://www.instagram.com/sinapodcast26?igsh=aWdrNGdqcTAxcWV6

#ሰው ግን ምን ያክል በቀለኛ ሊሆን ይችላል ? የበቀል መጨረሻውስ ምን ይሁን ? የፓስተር ጻድቁ አብዶ "በቀል በቀለኛውን ያጠፋል" የተሰኘው መጽሀፍ በአፋን ኦሮምኛ እና በትግረኛ እየመጣ ነው። በእን
#ሰው ግን ምን ያክል በቀለኛ ሊሆን ይችላል ? የበቀል መጨረሻውስ ምን ይሁን ? የፓስተር ጻድቁ አብዶ "በቀል በቀለኛውን ያጠፋል" የተሰኘው መጽሀፍ በአፋን ኦሮምኛ እና በትግረኛ እየመጣ ነው። በእንግሊዘኛ የተዘጋጀው መጽሀፍ አሁን ደግሞ በሁለት ቋንቋዎች በዝግጅት ላይ እንደሆነ ፓስተር ጻዲቁ ተናግረዋል። የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ፓስተር ጻዲቁ ከሲና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ ሰኔ 8 / 2017 ዓ.ም ከአንድ ዓመት በፊት ተመርቆ ለንባብ የበቃው መጽሀፍ በአሁኑ ሰዓት ለብዙዎች እንዲደርስ በአፋን ኦሮምኛ እና በትግረኛ እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። በሙሉ ጊዜ አገልጋይነት ከ50 አመት በላይ ያገለገሉ #እና የሙሉ #ወንጌል ሴሚናሪን 9 ዓመታት የሙሉ ወንጌልን ቤተክርስቲያንን ደግሞ በዋና ጸሐፊነት 8 አመታት የመሩ እና በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት የሆኑት ፓስተር ጻዲቁ አብዱ ይህ መጽሀፍ ከ17 ዓመት በላይ ያስተማሩትን ትምህርት ወደ መጽሀፍ የተቀየረ ነው። #ትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ ላይ ተንተርሶ በመንታ ወንድማማቾ ስር በሰደደ ጸብ ምክንያት አንዱ ሞተ አንዱ ተሰደደ በትውልዳቸው ጥላቻ ስር ሰደደ። ይህን #ድንቅ ታሪክ ለሁሉም ሊሆን በሚችል መልክ ተርከውታል። ሙሉ ቃለ መጠይቁን ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ https://www.youtube.com/watch?v=sU79nt70EYg&t=2463s

የኢትዮጵያ ገነት ቤተክርስቲያን 31ኛ ጠቅላላ ጉባኤው በምዕራብ ኦሮሚያ እና ደቡብ ክልል ተከናወነ። በመረሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ም/ፕሬዝደንት መጋቢ ሰንበቶ ባሼ
የኢትዮጵያ ገነት ቤተክርስቲያን 31ኛ ጠቅላላ ጉባኤው በምዕራብ ኦሮሚያ እና ደቡብ ክልል ተከናወነ። በመረሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ም/ፕሬዝደንት መጋቢ ሰንበቶ ባሼ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ም/ፕሬዝደንት ፓስተር ታሪኩን ጨምሮ እና የተለያዩ እህት ቤተእምነቶች እና ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል። የቤተክርስቲያኒቱ ብሔራዊ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሀንካራ ሀርቃ ጉባኤውን በኦፊሴሉ ያስጀመሩት ሲሆን የኢትዮጵያ ገነት ቤተክርስቲያን ፕሬዝደንት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ እንግዶችን ተቀብለዋል። ብሔራዊ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሀንካራ ሀርቃ በመክፈቻ ንግግራቸው በበጀት አመቱ ከ1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች የወንጌሉን የምስራች መስማታቸውን እና ከ36ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ ጌታ ኢየሱስን የግል አዳኛቸው አድርገው መቀበላቸውን ጠቅሰው ከ23ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች የውሀ ጥምቀት ወስደዋል ሲሉ ተናግረዋል። በጉባኤው በክልሉ የተገነባውን (ሂሊዮ አካዳሚ) የሚል መጠሪያ ያለውን ትምህርት ቤት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል። በምርቃቱ ላይ በትምህርት ቤቱ ግንባታ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ለሊዮ እና ሂልካ ሪንታኒያሚ ቤተእምነቷ ዕውቅና የሰጠች ሲሆን በቤተክርስቲያኒቱ ታሪክ ውስጥ ካገለገሉ እና ቀደምት አባቶች መካከል አንዱ የሆኑት ሄኪ ፔንትነን በስፍራው ተገኝተው “በቤተክርስቲያኒቱ እድገት መደሰታቸውን እና አሁንም በዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ ወንጌልን መስራታችሁን ቀጥሉ” ሲሉ መልዕክታቸውም አስተላልፈዋል። ተጨማሪ ዝርዝር ለማንበብ Facebook ገፃችንን ይመልከቱ

እሳቸው የሕብረቱ መሪ በነበሩበት 10 ዓመታት እንደ ሕብረት ብቻ ሳይሆን እንደሀገር እጅግ በብዙ ጭንቅ ውስጥ የታለፈበት ጊዜ ነበር። ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ወደ ሃላፊነት ከመጡ ጀምሮ በተግዳሮት ውስጥ ያለፈውን ሃላፊነታቸውን በታማኝነት አስረክበዋል። ነገር ግን ከዚህ ቀደም ያልተሰሙ እና ያለፉባቸውን ተግዳሮቶችን ግን አጫውተውናል። ይህ ከአንጋፋው የወንጌላውያን መሪ ከሆኑት ፓስተር ጻዲቁ ጋር የተደረገ ቆይታ የመጨረሻው ክፍል ነው። 🛑🛑 Sina Podcast ላይ ያለውን ቆይታ ተመልክታችሁ ሃሳባችሁን እንድታጋሩን ግብዣችን ነው። https://youtu.be/sU79nt70EYg

ብዙዎች እረኛቸውን ትተው ሄዱ! 🚶‍♂️‍➡️🚶‍♂️‍➡️🚶‍♂️‍➡️ ዛዶግ ፐርዝ የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ጊዜ በZadok Perth International Ministry እየተዘጋጀ በወንድም ተመስገን ነጋሽ በZadok Perth Youtube የሚቀርብ ተከታታይ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት ሙሉ ትምህርቱን ኮሜንት ስር ያገኙታል።

"እነዚህ 50 ዓመታት የሙላት፣ የሙቀትና የምቾት ዓመታት ብቻ አልነበሩም" ፓስተር ታምራት ሀይሌ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የዝማሬ አገልግሎት ብዙዎችን የባረኩት እና ከአንጋፋ አገልጋዮች መካከል አንዱ
"እነዚህ 50 ዓመታት የሙላት፣ የሙቀትና የምቾት ዓመታት ብቻ አልነበሩም" ፓስተር ታምራት ሀይሌ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የዝማሬ አገልግሎት ብዙዎችን የባረኩት እና ከአንጋፋ አገልጋዮች መካከል አንዱ የሆኑት ፓስተር ታምራት ከሰሞኑ በካናዳ ስለተደረገላቸው ድንገተኛ ሰርፕራይዝ ምስጋናቸው አቅርበዋል። በማህበራዊ ድህረገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የመላ ካናዳ አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት "ለኅብረት ተጠርተናል" በሚል በቶሮንቶ ከተማ ባዘጋጁት በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ታላቅ ኮንፈረንስ ላይ እንድናገለግል በተጠራንበት፣ በኮንፈረንሱ መጨረሻ ላይ "የአገልግሎትህን 50ኛ ዓመት" በሚል በድንገት ሰርፕራይዝ አደረጉን። "ብርሃነ ወንጌል" በተሰኘች ቤተክርስቲያን በመዘምራን ቡድን የተሰለፍኩበት ዓመት ተጨምሮ ሲሰላ በእርግጥም 50 ዓመት መሙላቱን ያስተዋልኩት በኋላ ነው። እነዚህ 50 ዓመታት የሙላት፣ የሙቀትና የምቾት ዓመታት ብቻ አልነበሩም። የምንኖርባት ምድር ጠፍጣፋ (Flat) ብቻ ሳትሆን ወጣገባ እንደሆነች ሁሉ፣ ሕይወትም እንዲሁ ውጣ ውረድ የበዛበት ቢሆንም ቅሉ፣ ጌታን ለመከተል የመጀመሪያዋን እርምጃ እግሬን ካንሳሁበት ዕለት ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ በማንከስም፣ በዳዴም ሆነ በሩጫ ዘመን እጄን ይዞ የመራኝን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፣ ይህን የሰማ ሁሉ ያመስግንልኝ። ወንድሜ ሸዋዬ ዳምጤ እንዳዜመው፣ "ቀሪ ዘመኔን" እንዲባርክልኝ እለምነዋለሁ፣ እናንተም ለምኑልኝ። "ተነሥተንም ወደ ቤቴል እንውጣ፤ በዚያም በመከራዬ ጊዜ ለሰማኝ፥ በሄድሁበትም መንገድ ከእኔ ጋር ለነበረው ለእግዚአብሔር መሠውያን አደርጋለሁ" (ዘፍ. 35:3) "አቤቱ አንተ ተስፋዬ ነህና፥ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከታናሽነቴ ጀምረህ መታመኛዬ ነህና። ተጨማሪ ለማንበብ Facebook

#የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት እጣ ፈንታ #የቄስ ጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ የኢትዮጵያወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት እጣ ፈንታ እና የቄስ ጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ ላይ ያተኮረ የምክክር መ
#የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት እጣ ፈንታ #የቄስ ጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ የኢትዮጵያወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት እጣ ፈንታ እና የቄስ ጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሄደ። “እነርሱም አንድ እንዲሆኑ” የሚለውን የዮሃንስ ወንጌል 17 መሰረት በማድረግ በአዲስ አበባ ቦሌ ኢላሜ ኮንቬንሽን ሴንተር በተካሄደው ፕሮግራም የቄስ ጉዲና ቱምሳን የአገልግሎት እና የህይወት ሌጋሲ ማውሳት እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት እጣ ፈንታ ዙሪያ ጽሁፎች ቀርበዋል ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ የጉዲና ቱምሳ ፋውንዴሽን መስራች እና መሪ እንዲሁም የቄስ ጉዲና ልጅ ወ/ሮ ሌንሳ ጉዲና ተጋባዥ እንግዶችን እንኳን ደህና መጣችሁ ሲሉ ተቀብለዋል። በመድረኩ ቄስ ዶ/ር ሳሙኤል ደረሳ፣ ዶ/ር ተካልኝ ነጋ እና ዶ/ር ለማ ደገፋ ጥናታዊ ጽሁፎች አቅርበዋል። ዶ/ር ምህረት ደበበ የእለቱ ተናጋሪ መልዕክት አስተላላፊ ነበሩ። ቄስ ሃረገወይን ቃለ እግዚአብሔር ያቀረቡ ሲሆን፣ ቄስ ገመቺስ ደስታ (ፕሮፌሰር) እና ሃዋርያው ታምራት ታረቀኝ በጸሎት አገልግለዋል። ዘማሪ መስፍን ጉቱ፣ ዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ፣ ዘማሪት ራሄል ተፈራ እና ዘማሪ ጉቱ ሽፈራው በዝማሬ ያገለገሉ ሲሆን የቢፍቱ ቦሌ መካነ ኢየሱስ ታዳጊዎች “አንድ ነን” የተስኘ ኬሮግራፊ አቅርበዋል። በኦቦሌሳ አዶላ

እኔ ጠይቄ እምቢ ቢሉኝስ የሚል ፍርሃት ነበረኝ / መጀመሪያ ለትዳር ሲጠየቁ ያለቀሱ ነበሩ 😁 የፓስተር ጻዲቁ አዝናኝ የፍቅር ጉዞ https://youtu.be/6-A-b_jNuGs

4627 ሰዎች ወደ #ጌታ መንግስት ተጨምረዋል። "መልካም ወጣት ደማስቆ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን የሚዘጋጀው የ2018 ዓ.ም መልካም ወጣት መረሃ ግብር ከተጀመረ 4ኛ ሳምን
4627 ሰዎች ወደ #ጌታ መንግስት ተጨምረዋል። "መልካም ወጣት ደማስቆ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን የሚዘጋጀው የ2018 ዓ.ም መልካም ወጣት መረሃ ግብር ከተጀመረ 4ኛ ሳምንቱ ላይ ደርሷል። እያንዳንዱ ስልጠናዎች አንድ ሳምንትን የሚፈጅ ሲሆን አሁን 4ኛው ዙር ላይ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ዙር ብቻ 1336 ሰዎች ከአለም ለማምለጥ እና ወደ ዘላለማዊ ሕይወት ለመግባት መወሰናቸውን የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን አሳውቃለች። ባለፉት 3ዙሮች በ1ኛው ዙር 940 ሰዎች በ2ኛው ዙር 1143 ሰዎች በ3ኛው ዙር 1208 ሰዎች ጌታን ለመቀበል የወሰኑ ሲሆን በአጠቃላይ በ4ዙሮች ብቻ 4627 ጌታን ለመቀበል ወስነዋል። #እግዚአብሔር ይመስገን!

"ለአንድ ሀገር ዘላቂ መረጋጋትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ መሠረት በሚሆኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ በሰለጠነ መንገድ ሐሳብ እየተለዋወጥን ነው" ፓስተር ጻዲቁ አብዶ የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን
"ለአንድ ሀገር ዘላቂ መረጋጋትና ለጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ መሠረት በሚሆኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ በሰለጠነ መንገድ ሐሳብ እየተለዋወጥን ነው" ፓስተር ጻዲቁ አብዶ የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ከሰሞኑ እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዙሪያ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው። ፓስተር ጻዲቁ የምክክር ሂደቱ ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያጎለብትና ለትውልድ የሚሻገር ሰላምን የሚገነባ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዋናው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጉባኤው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በመሰባሰብ በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት እየተመካከሩ እንደሚገኙ የኢዜአ ዘገባ የሚጠቁም ሲሆን ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች፤ የምክክር ሂደቱ አሳታፊ፣ አካታችና ነፃ ሆኖ መካሄዱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ መግባባትና ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ተስፋ ሰጪ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን አክሎ ዘግቧል።

ህገ ወጥ መንገደኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ 🚓 🚓 🚓 ዛዶግ ፐርዝ የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ጊዜ በZadok Perth International Ministry እየተዘጋጀ በወንድም ተመስገን ነጋሽ በZadok Perth Youtube የሚቀርብ ተከታታይ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት ሙሉ ትምህርቱን ኮሜንት ስር ያገኙታል።