The Christian News
Open in Telegram
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት። @TCNEW
Show more5 294
Subscribers
-724 hours
-77 days
-1030 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+24
in 0 channels
August '26
+153
in 0 channels
Get PRO
July '26
+296
in 0 channels
Get PRO
June '26
+88
in 0 channels
Get PRO
May '26
+104
in 0 channels
Get PRO
April '26
+90
in 4 channels
Get PRO
March '26
+38
in 1 channels
Get PRO
February '26
+51
in 0 channels
Get PRO
January '26
+39
in 3 channels
Get PRO
December '25
+31
in 0 channels
Get PRO
November '25
+32
in 0 channels
Get PRO
October '25
+23
in 0 channels
Get PRO
September '25
+70
in 0 channels
Get PRO
August '25
+56
in 0 channels
Get PRO
July '25
+65
in 0 channels
Get PRO
June '25
+76
in 1 channels
Get PRO
May '25
+50
in 0 channels
Get PRO
April '25
+57
in 0 channels
Get PRO
March '25
+106
in 1 channels
Get PRO
February '25
+179
in 1 channels
Get PRO
January '25
+93
in 0 channels
Get PRO
December '24
+89
in 3 channels
Get PRO
November '24
+97
in 1 channels
Get PRO
October '24
+108
in 1 channels
Get PRO
September '24
+156
in 1 channels
Get PRO
August '24
+243
in 1 channels
Get PRO
July '24
+121
in 0 channels
Get PRO
June '24
+169
in 2 channels
Get PRO
May '24
+160
in 0 channels
Get PRO
April '24
+268
in 2 channels
Get PRO
March '24
+533
in 2 channels
Get PRO
February '24
+199
in 1 channels
Get PRO
January '24
+292
in 1 channels
Get PRO
December '23
+381
in 0 channels
Get PRO
November '23
+154
in 2 channels
Get PRO
October '23
+54
in 0 channels
Get PRO
September '23
+308
in 0 channels
Get PRO
August '23
+331
in 0 channels
Get PRO
July '23
+132
in 0 channels
Get PRO
June '23
+278
in 0 channels
Get PRO
May '23
+289
in 0 channels
Get PRO
April '23
+233
in 0 channels
Get PRO
March '23
+141
in 0 channels
Get PRO
February '23
+76
in 0 channels
Get PRO
January '23
+450
in 0 channels
Get PRO
December '22
+327
in 0 channels
Get PRO
November '22
+25
in 0 channels
Get PRO
October '22
+41
in 0 channels
Get PRO
September '22
+49
in 0 channels
Get PRO
August '22
+79
in 0 channels
Get PRO
July '22
+210
in 0 channels
Get PRO
June '22
+44
in 0 channels
Get PRO
May '22
+106
in 0 channels
Get PRO
April '22
+97
in 0 channels
Get PRO
March '22
+96
in 0 channels
Get PRO
February '22
+12
in 0 channels
Get PRO
January '22
+30
in 0 channels
Get PRO
December '21
+88
in 0 channels
Get PRO
November '21
+13
in 0 channels
Get PRO
October '21
+232
in 0 channels
Get PRO
September '21
+62
in 0 channels
Get PRO
August '21
+88
in 0 channels
Get PRO
July '21
+228
in 0 channels
Get PRO
June '21
+68
in 0 channels
Get PRO
May '21
+389
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 10 September | +1 | |||
| 09 September | +1 | |||
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | +5 | |||
| 06 September | +6 | |||
| 05 September | +2 | |||
| 04 September | +2 | |||
| 03 September | +4 | |||
| 02 September | +1 | |||
| 01 September | +2 |
Channel Posts
በአዲስ አበባ እስታድየም ልዩ የአዲስ አመት መረሃ ግብር መስከረም 1/2019ዓ.ም
#እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ።
እነሆ አዲስ ነገር አደርጋለሁ እርሱም አሁን ይበቅላል። ኢሳ 43፤19
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት፣ አርብ መስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም የምሥጋና የአምልኮና የጸሎት መርሐግብር አዘጋጅቷል።
ከማለዳው 12፡00 እስከ ረፋዱ 5፡00 ሰአት በሚቆየው በዚህ መርሐግብር ላይ ቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና ፓስተር ስለሺ ክንፉ ዘማሪ ፓስተር ዳንኤል አምደሚካኤል እና የተለያዩ አገልግዮች አብረውን ይኖራሉ።
እግዚአብሔርን ከፍ በማድረግ ወደምንዘልቅበት ወደዚህ የአዲስ አመት መቀበያ መርሐግብር ላይ ወዳጆቻችንን በመጋበዝ ትገኙ ዘንድ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ጥሪውን ያቀርባል።
በከከተማ እና ከሀገር ዉጪ ላላችሁ በእለቱ የቀጥታ ስርጭቱን ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ። You tube;- https://www.youtube.com/@ECFEMedia-et
| 2 | #በጎ አድራጎት ሰዎችን በፍቅር የሚያስተሳስር ተግባር መሆኑ ተገለጸ።
የሆሳዕና ከተማ ካባ ጨፌ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን #አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ65 አቅመ ደካሞች ከ785 ሺህ 830 ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስና የምግብ ድጋፍ አድርጋለች።
የቤተ ክርስቲያኗ የፍቅርና ርኅራኄ አገልግሎት ዘርፍ አስተባባሪ ወንጌላዊ ዘውዴ ተመስገን እንደገለጹት፤ ዘርፉ ለአቅመ ደካሞች የምግብ፣ የአልባሳት፣ የትምህርት ቁሳቁስና ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል።
አገልግሎቱ ከተጀመረበት ከሁለት ዓመት በፊት አንስቶ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን የጠቆሙት አስተባባሪው፣ ለአብነትም ለ16 ሰዎች መነሻ ገንዘብ በመስጠት የራሳቸውን ንግድ እንዲጀምሩ ማስቻሉን አብራርተዋል።
አገልግሎቱ በቋሚነት 65 ሰዎችን እንደሚደግፍ የጠቆሙት ወንጌላዊ ዘውዴ፤ በዘንድሮው የአዲስ ዓመት ድጋፍም ዘይት፣ አልባሳት፣ ዱቄት፣ ጋቢ፣ ብርድ ልብስና የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች መካተታቸውንና አጠቃላይ ወጪውም 785 ሺህ 830 ብር መሆኑን ገልጸዋል።
የሆሳዕና ካባ ጨፌ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ሰብሳቢ አቶ መለሰ ሚሽቆ በበኩላቸው፤ የድጋፉ ዋና ዓላማ አቅመ ደካሞች በዓሉን በደስታ እንዲያከብሩ ማስቻል እንደሆነ ተናግረዋል።
ድጋፉ በበዓላት ብቻ የተገደበ አለመሆኑን የጠቆሙት ሰብሳቢው፤ የትምህርት ቤት ወርሃዊ ክፍያ፣ የቤት ኪራይ፣ እንዲሁም ቤት የማስገንባት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸው በቀጣይም የድጋፉን መጠንና የተጠቃሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ታቅዷል ብለዋል።
በዕለቱ ድጋፍ ካደረጉት የቤተክርስቲያኗ ምዕመናን መካከል "የታምራት ደበሮ እና ቤተሰብ" ዱቄት #ፋብሪካ ባለቤት አቶ ታምራት ደበሮ፤ ድጋፉን በራስ ተነሳሽነት ማድረጋቸውን ገልጸው በቀጣይም በመሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ እንደሚሳተፉ ተናግረዋል።
የቤተክርስቲያኗ ጸሐፊና አስተባባሪ | 505 |
| 3 | የ6ኪሎ ጉባኤ #እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን የማረሚያ ቤት አገልግሎት በዝዋይ (ባቱ) ለሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ማረሚያ ቤት የወንጌል ስርጭት አካሄደ።
በአመት ሶስት ጊዜ በመደበኛነት የወንጌል ስርጭቶችን የሚያካሂደው የ6 ኪሎ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን የማረሚያ ቤት አገልግሎት ከሌሎች አብያተክርስቲያናት ከተወጣጡ አገልጋዮች ጋር በመሆን ለ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክቶ በዝዋይ የክልሉ ማረሚያ ቤት ባዘጋጀው የወንጌል ስርጭት ከ30 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ወንጌልን ሰምተው ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተቀላቅለዋል።
በዕለቱም የአምልኮ፣ የቃል እና የስጦታ እንዲሁም የማረሚያ ቤት ጉብኝት የተካሄደም ሲሆን በማረሚያ ቤቱ ለምትገኘው ቤተክርስቲያን የወንበር፣ የምንጣፍ፣ የመብራት አንፖል፣ የአልባሳት፣ የሴፍቲ ታንከር እንዲሁም ልዩ ልዩ ድጋፎች ተበርክቶላቸዋል።
በዝዋይ ባቱ ለሚገኘው ማረሚያ ቤት ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ድጋፍ መደረጉን የገለፁት የማረሚያ ቤቱ አዛዥ ኮማንደር ኡርጌ ፋዬ የቤተክርስቲያኒቱ የማረሚያ ቤት አገልግሎት በተደጋጋሚ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይም የማረሚያ ቤቱ አገልግሎት አስተባባሪ የሆነው ወንድም አዲስ በቀለ የማረሚያ ቤቱ ታራሚዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ገልጿል ሲል Gmm tv Ethiopia ዘግቧል። | 664 |
| 4 | እንኳን አደረሳችሁ አዲስ አበባ እስታድየም እንገናኝ https://www.youtube.com/watch?v=ZgSge2OoyHM&t=218s | 915 |
| 5 | "ወደ እግዚአብሔር ቃል እንመለስ የሚለውን ሃሳብ በተግባር ያሳየ ስራ ነው" ፓስተር ጻዲቁ አብዶ
የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝደንት እና የሰርክል ተቋም ሃላፊ የሆኑት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ይህንን ያሉት "ቶሎ ና" የተሰኘው የዝማሬ የአልበም ምርቃትና ለ365 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት መዝጊያ መረሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
ቦሌ በሚገኘው በዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን እየተከናወነ በሚገኘው መረሃ ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ፓስተር ጻዲቁ ዘመኑን በዋጀው ዲጅታል ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ለመዋጀት እህት ትዕግስት እጅጉ የሰራችውን ስራ አድንቀዋል።
ዘመኑ ክፉ ሆኖ ፍጻሜው በቀረበበት በዚህ ሰዓት የክርስቶስን ምጽዓት እንድንናፍቅ የሚያደርግ እና እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎን እንዳንተኛ ክርስቶስ መምጫው በደጅ ነውና "ቶሎ ና" የተሰኘውን ዝማሬ በማዘጋጀቷ አመስግነዋል። | 807 |
| 6 | አራተኛው የሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት በመካኼድ ላይ ይገኛል።
በአራተኛው የሕንጸት የመጻሕፍት ዕውቅና ሥነ ሥርዐት በፓስተር ጻዲቁ አብዶ ተጽፎ የቀረበው "በቀል በቀለኛን ያጠፋል" የተሰኘው መጽሀፍ በነገረ መለኮት ዘርፍ፥ በስልታዊ ነገረ መለኮት ንዑስ ዘርፍ የ2018 ዓ.ም ተሸላሚ ሆኗል።
በመንፈሳዊ እድገት ዘርፍ የ2018 ዓ.ም. ተሸላሚ መጽሐፍ በበርናባስ ዘመነ የተዘጋጀው "ወንጌል ይዘቱና አቀራረቡ" የተሰኘው መጽሀፍ ተሸላሚ የሆነ ሲሆን በታሪክ ዘርፍ በዮናስ ጎርፌ ተጽፎ የቀረበው "ፕሮቴስታንታዊያን በኢትዮጵያ ፖለቲካ" የተሰኘው መጽሐፍ የ2018 ዓ.ም. ተሸላሚ መጽሐፍ ሆኗል።
በአራተኛው የሕንጸት የመጻሕፍት ዕውቅና ሥነ ሥርዐት በፈጠራ ሥራ ዘርፍ፥ በኢ-ልብ ወለዳዊ ዘውግ በግለ ታሪክ ንዑስ ዘርፍ ደግሞ በዶ/ር ንጉሴ ተፈራ የተጻፈው "ዞር ብዬ ሳየው" የሚል ርዕስ ያለው ግለ ታሪክ መጽሀፍ የ2018 ዓ.ም. ተሸላሚ መጽሐፍ ሆኗል።
በፈጠራ ሥራ ዘርፍ፥ በልብ ወለድ ንዑስ ዘርፍ "በታችም በምድር" በሌሎሳ ግርማ ተሸልሟል። በወጣት ሀንኤል ኩረማ የተዘጋጀው "የእብራውያን መልዕክት ማብራርያ" በነገረ መለኮት ዘርፍ፥ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት ንዑስ ዘርፍ የ2018 ዓ.ም. ተሸላሚ መጽሀፍ ነው።
በነገረ መለኮት ዘርፍ፥ በተግባራዊ ነገረ መለኮት ንዑስ ዘርፍ የ2018 ዓ.ም. ተሸላሚ መጽሐፍ ደግሞ በመጋቢ ሰለሞን አበበ የተጻፈው "ድፍርስ ጅረቶች" ደሃም ስም አለው የተሰኘው እና በቅርብ ጊዜ ለንባብ የበቃው መጽሀፍ ነው።
አራተኛው የሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት አሁንም በETC እየተካሄደ ይገኛል። | 736 |
| 7 | #አዲስ #ዜና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከአለምአቀፍ ሜኖናይት ኮንፍረንስ (MWC) መውጣቷን አሳወቀች።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እያካሄደች በምትገኘው 95ኛው ጠቅላላ መሪዎች ጉባኤ ከአለምአቀፍ ሜኖናይት ኮንፍረንስ (Mennonite World Conference /MWC) ለመውጣት ውሳኔ አሳልፋለች።
በጉባኤው ቤተክርስቲያኒቱ ላለፉት 59 አመታት በዚህ ተቋም ውስጥ የነበራት ተሳትፎና ግንኙነት በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ጥናታዊ ጽሁፍ የቀረበ ሲሆን ከዚህ ጥናት ጋር የቤተ ክርስቲያኒቱ ስነመለኮት ኮምሽን ያዘጋጀው ምክረሃሳብም ተካቷል።
በዚህ መሠረት ጠቅላላ ጉባኤው በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ (መአመጉ) የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ በመቀበል ቤተክርስቲያኒቱ አባል ሆና ለ59 አመታት ከቆየችበት የሜኖናይት አለምአቀፍ ኮንፍረንስ (MWC) እንድትወጣ አጽድቋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከተቋሙ ጋር ምንም እንኳን የገንዘብና የሥራ ግንኙነት ባይኖራትም በዚህ ግብረሰዶማዊነትን በአካታችነት በተቀበለ ተቋም ውስጥ አባል በመሆኗ ምክንያት ላለፉት ወራት ስሟ በተለያየ መንገድ ሲነሳ መቆየቱ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተገናኘ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር በቀጣይ ማብራሪያ የሚሰጥ እንደሆነም አሳውቀዋል።
በቤተክርስቲያኒቱ 95ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ጨምሮ የተለያዩ ቤተክርስቲያናት ፕሬዝዳንቶች ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ለረጅም አመታት ላገለገሉና ከአራቱም አቅጣጫ ለመጡ አባቶች በዛሬው እለት በተካሄደው 95ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የምስጋናና እውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።
የቪዲዮ ዜናዎችን ይመለከቱ YOUTUBE | 796 |
| 8 | የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የ2018 ዓ.ም የልጆች በዓል ሳምንት በተለያዩ ማኅበረ ምዕመናን በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።
የዘንድሮው የልጆች በዓል ሳምንት፣ በምሳሌ 22፥6፣ “ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፤ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም” የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል እንደ መሪ ጥቅስ በመያዝ፣“ ጠንካራ ቤተሰብ፦ ስኬታማ ትውልድ” በሚል መሪ ርዕስ ተከብሯል።
በአንድ ሳምንት የተከበረው ይህ በዓል፣ ልጆች በጸሎት፣ በአካባቢ ጽዳት፣ በስፖርታዊ ጨዋታዎችና ውድድሮች፣ እንዲሁም በተለያዩ የሥነ-ጽሑፍ አገልግሎቶች እንዲሳተፉ በማድረግ ተከናውኗል። ከዚህ በተጨማሪም የልጆችና ወላጆች የጋራ ቀን ተካሂዶ፣ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ልጆች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ በማካሄድ የበዓሉ ሳምንት ተጠናቋል።
ተጨማሪ ዜናዎችን ከFacebook ያንብቡ | 882 |
| 9 | የባለ ትዳሮች ሴሚናር እና የቃል ኪዳን ማጽኛ መረሃ ግብር በጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪካ ተካሄደ።
በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ የምትገኘው ወንጌል አብሳሪዎች አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን አዘጋጅነት በባላ ትዳሮች ላይ ያተኮረ የሶስት ቀናት ሴሚናር ተካሄደ።
ከAugest 28-30/2026 በተካሄደው የባለ ትዳሮች ፕሮግራም ሰልጠናውን የሰጡት በጋብቻ ረጅም ዘመን ያሰቆጠሩት እና በተለያየ ጊዜ የጋብቻ ሴሚናር በመሰጠት የሚታወቁት ወንጌላዊት ሊዲያ ዮናሰ እና የወንጌል አብሳሪዎች ዋና መጋቢ እና የሳውዝ አፍሪካ አብያተ ክርሰትያናት ካውንሰል ፕሬዝዳንት ፖሰተር ብርሃኑ ታምሬ (ዶክተር) ናቸው።
በመጀመሪያ ቀን የእግዚአብሔር ዓላማ በጋብቻ ውስጥ ከሚል ሀሳብ ተነስተው የባል እና የሚስት ሚና በመረዳት መተግበር፤ በውጤቱ ደስተኛ ቤተሰብ መሆን በሚል ርዕስ ሰልጠና ተሰጥቷል።
ሁለተኛ ቀን ከሁለቱም ወገን ከባሎችና ሚስቶች ለቀረቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ተሰጥቶ፡ በተተኪ ትውልድ ባለድርሻነት፤ በሚል አምስት ባለ ድርሻ አካላት ተጠቅሶ ማብራሪያ በጥልቀት የተሰጠ ሲሆን ባለድርሻ አካላት በቅድሚያ ቤተሰብ፤ ሲቀጥል ቤተክርስቲያን፤ ትምህርት ቤት፤ መንግስት እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት በሚለው ቅደም ተከተል ተጠቅሰዋል።
እነዚህ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን ካልተወጡ ከቤተሰብ አንስቶ እስከ ዓለም አቀፍ ደረጃ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው በሴሚናሪው አስገንዘበዋል።
ሴሚናሩ መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ባደረገ መነሻ ሁሉን የሰው ልጅ መስተጋብር የዳሰሰ ሲሆን ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ፤ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊና ዘመናዊ የሥልጣኔ ውቅሮችን አካትቷል።
በዚህ ዘርፍ እንደ ድርጅት፣ እንደ ሃይማኖት ተቋማት፣ እንደ ሀገር እንዲሁም መንግስትም ትኩረት አድርጎ መሰራት የሚገባ ዘርፍ መሆኑ ተመልክቷል።
ተጨማሪ ዝርዝር Facebook | 947 |
| 10 | #ድንቅ የአምልኮ ምሽት 🔥🔥
3ቀን ብቻ ቀረ! 🔥
መዝሙር 150:6
6 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን።
ሃሌ ሉያ።
"ሃሌሉያ! ሃሌሉያ! ሃሌሉያ!" እያልን በጋራ ጌታን የምናመልከበት ልዩ የአምልኮ ምሽት ተዘጋጅቷል።
🗓 ቅዳሜ ነሐሴ 30
📍 አያት መካነኢየሱስ
የአያት መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምእመናን Ayat Mekane Yesus Church
https://maps.app.goo.gl/GYStjnDUYLPN5Ln88
ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን የዚህ ድንቅ ምሽት ተካፋይ ይሁኑ
#የአምልኮምሽት #AyatMekaneYesus #YouthWorship #WorshipNight #5DaysToGo #ሃሌሉያ | 1 036 |
| 11 | በሚዛን መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ኮምፓሽን ፕሮጀክት ለደሀ ደሀ ተማሪዎችና ወላጆች የአዲስ አመት መዋያ ከ1.8 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ፕሮጀክቱ ለ216 የደሀ ደሀ ተማሪዎችን ጨምሮ ከ2ሺ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑም ተገልጿል።
በሚዛን መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የኢቲ - 3002 የህጻናትና ወጣቶች ልማት ፕሮጀክት ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ዘገየ እንደገለጹት ቤተክርስቲያኗ ከኮምፓሽን ፕሮጀክት በምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ በመደበኛ ተግባር 216 የደሀ ደሀ ቤተሰብ ተማሪዎችን የምግብ፣ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ወጪን በመሸፈን እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።
የዛሬው ድጋፍ አዲስ አመትን ከክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ 1 ሚሊየን 813ሺ ብር ወጪ በማድረግ ጤፍ ፣ ዘይት ፣ አልባሳት ፣ ደብተር ፣ እስክሪብቶ ፣ እርሳስና ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።
ቤተክርስቲያኗ ከፕሮጀክቱ ጋር በመተባበር የእምነት ፣ የብሔርና የቀለም ልዩነት ሳታደርግ የደሀ ደሀ ቤተሰብ ተማሪዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ እየሰራች መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተሾመ በቀጣይ ሳምንት የዚሁ ድጋፍ አካል የሆነው የአልባሳት ስርጭት እንደሚደረግም ገልጸዋል።
አሁን ላይ ተማሪዎችን ጨምሮ ከ2ሺ በላይ የተማሪ ቤተሰቦችን አቅፎ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባለሙያ ወይዘሮ ደብሪቱ ሀይሉ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ 216 ህጻናትና ቤተሰቦቻቸውን ከኢኮኖሚ ተጋላጭነት ለማላቀቅ ላለፉት 5 አመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ተጨማሪ አነባለው ካሉ Facebook ዝርዝር አለው | 735 |
| 12 | #ቶሎ ና 🔥🔥🔥 ደረሰ ደረሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ አልበም 🔥🔥
የእህታችን አገልጋይ ትዕግሥት እጅጉ ቶሎ ና የተሰኘው የክርስቶስን ምፅአት እንድንናፍቅ የሚያስታውሰን ኢየሱስን የሚሰብከን ቶሎ ና የተሰኘ ኢፒ (ግማሽ አልበም) የፊታችን ነሀሴ 30 ቅዳሜ ቀን ከ8:30 ጀምሮ በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
በእለቱ የእግዚአብሔር ቃል እንዲሁም ዝማሬ ይቀርባል።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል 🔥🙏🔥🙏 | 784 |
| 13 | "15 ዓመታትን ስለሰላም እየሰራን ተጉዘናል" የሃይማኖት ተቋማት
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የምስረታ 15ኛ ዓመት እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አከናውኗል።
በእስካይ ላይት ሆቴል በነበረው በመረሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች ፤ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ቦርድ አመራሮችና የክልል ጉባኤ አመራሮች ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።
"15 ዓመታት እምነትን በቀጣይነት፣ ሰላምን ህብረብሔራዊ ልማት በኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ ባለው መረሃ ግብር በክብር እንግዳነት የተገኙት የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለ15 ዓመታት ያካሄደው የጋራ ጉዞ በእምነት ተቋማት ትብብርን በማጠናከር፣ ሰላምንና ማህበራዊ ውህደትን በማሳደግ ለሀገራዊ እድገትና ልማት ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው የጋራ ሀብታችን የሆነው ሰላም መጠበቅ እና ማበልጸግ የሚቻለው ሁላችንም ኃላፊነታችንን መወጣት ስንችል ነው ያሉ ሲሆን ሁላችንም ባለንበት አካባቢ እና ተቋም ውስጥ ለሰላም ግንባታ አስተዋጽኦ በማበርከት የሰላም ምሳሌ በመሆን ሰላምን ልናጸና ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የሃይማኖት ተቋማት የሀገራችንን ሰላምና አብሮነት ላይ ላለፉት አስራ አምስት አመታት በመስራት ታሪካዊ ድል ማስመዝገቡን የተናገሩት ደግሞ የኢፌዲሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ ሙሀመድ ኢድሪስ ናቸው።
ተጨማሪ ዝርዝር ያንብቡ Facebook | 994 |
| 14 | ሟች እራት ላይ ተገኘ።
🍔 🍔 🍔
ዛዶግ ፐርዝ የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ጊዜ
በZadok Perth International Ministry እየተዘጋጀ በወንድም ተመስገን ነጋሽ በZadok Perth Youtube የሚቀርብ ተከታታይ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት
ሙሉ ትምህርቱን ኮሜንት ስር ያገኙታል። | 1 589 |
| 15 | አስቸኳይ መግለጫ ለወንጌል አማኞች በሙሉ https://www.youtube.com/watch?v=bxNJFCwPGUg | 1 662 |
| 16 | አስቸኳይ መግለጫ ለወንጌል አማኞች በሙሉ https://youtu.be/bxNJFCwPGUg | 1 |
| 17 | የማይወሰድ ምርጫ።
📖 📖 📖
ዛዶግ ፐርዝ የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ጊዜ
በZadok Perth International Ministry እየተዘጋጀ በወንድም ተመስገን ነጋሽ በZadok Perth Youtube የሚቀርብ ተከታታይ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት
ሙሉ ትምህርቱን ኮሜንት ስር ያገኙታል። | 2 068 |
| 18 | የጎዳና ላይ ወንጌል ስብከት የሌሎችን መብት መንካት የለብንም የፓስተር ደረጄ የመጨረሻ ክፍል ድንቅ ምስክርነት https://youtu.be/QqNYKRfxC8c | 1 879 |
| 19 | አማኞች በዚህ ዘመን ስለ ፈውስ ደፍረው ለመናገር ይቸገራሉ። እኔ ግን ምስክር ነኝ https://www.youtube.com/watch?v=4LFnmP76EoM&t=570s | 2 030 |
| 20 | አማኞች በዚህ ዘመን ስለ ፈውስ ደፍረው ለመናገር ይቸገራሉ። እኔ ግን ምስክር ነኝ https://www.youtube.com/watch?v=4LFnmP76EoM&t=570s | 2 |
