Alem-maya primary school lideta
Open in Telegram
334
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1000279677866 nigid 2279528000019 Bunna finot saving and credit private limited campany or association
እንዴት አደራችሁ ውድ መምህራን እና ር/መ/ራን ባለፈው ሳምንት የመኪና ቁጠባ ለመመዝገብ ፈልጋችሁ ካላችሁ 3ጉርድ ፎቶ÷የቀበሌና የስራ ቦታ መታወቂያ ኮፒ በመያዝ4500 ብሩን ቀጥሎ በተቀመጠው አካውንት በማስገባትእኔ ጋር መታችሁ ከሰኞ እስከ ረቡዕ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እገልፃለሁ::
መምህራንን በህብረት ስራ ለማደራጀት እና መኖሪያ ቤት እንዲገነቡ በሚደረግ ሂደት ቅድመ ቁጠባ ማለትም 30% ማሟላት የሚችሉ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንዲደራጁ እና ቀሪዎቹ ደግሞ እየቆጠቡ እንዲደራጁ ለማድረግ የተግባር እንቅስቃሴ ላይ መግባት እንድንችል ቀድሞ የተላከው መረጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ቅድሚያ የሚቆጥቡትን በቤት አይነት በመለየት እስከ አርብ 17/5/2016 እንድታሳውቁ እናሳስባለን።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
መምህራኑ በቀረቡላቸው አማራጮች መሰረት የቁጠባ ባህላቸውን በማሳደግ በህብረት ስራ ማህበር ተደራጅተው የባለ 1፣ባለ 2 እና የባለ 3 መኝታ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቆ ወደ ተግባር ለመግባት በእንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን የህብረት ስራ ኮሚሽን እንዲሁም የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አመራሮች በውይይቱ ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚያስተምሩ መምህራን የጋራ መኖሪያ ህንጻ በህብረት ስራ በማደራጀት ግንባታ ለማስጀመር በተዘጋጀ ሰነድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።
(ቀን ጥር 16/2016 ዓ.ም) በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር አመራሮችን ጨምሮ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የህብረት ስራ ኮሚሽን አመራሮችና የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል ከተማ አስተዳደሩ የመምህራንን የቤት ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ አማራጮችን በመከተል ላይ መሆኑን በመግለጽ ከነዚህ አማራጮች መካከል አንዱ መምህራንን በህብረት ስራ ማህበራት በማደራጀት የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻል መሆኑን ጠቁመው የዛሬው ውይይት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ወደ ተግባር ለመግባት የሚያግዝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ሰኔ ስድስት 2015 ዓ.ም ባፀደቀው መመሪያ መሰረት መምህራን ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ማህበሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸው በቀጣይ ዛሬ የቀረበውን የማስፈጸሚያ ሰነድ መሰረት በማድረግ በአስቸኩዋይ ወደተግባር የሚገባ መሆኑን አስታውቀዋል።
