en
Feedback
Akaki_Kality_Woreda_3 Communication

Akaki_Kality_Woreda_3 Communication

Open in Telegram

ይህ የአቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 3 ኮሙኒኬሽን ቻናል ነው

Show more
718
Subscribers
No data24 hours
-137 days
-4030 days
Posts Archive
የአራዳ የበጎነት መንደር ግንባታ በታቀደለት ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ይገኛል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው የአራዳ በጎነት መንደር የግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት ላይ መሆኑ ተገለጸ። የአራዳ የበጎነት መንደር የአቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጀመሩ ይታወሳል። ቀደም ሲል የደሳሳ ጎጆዎች መገኛና ለመኖር ምቹ ያልነበሩ አካባቢዎችን በመቀየር፣ በርካታ ዜጎችን ችግር ለመቅረፍ የታለመው ይህ ግዙፍ የበጎነት ተግባር በአጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ምዕራፍ ላይ መድረሱን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ባደረገው ቅኝት ታዝቧል። የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ተወካይ ኢንጂነር በሪሁን ደርቤ ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከተጀመረ 54 ቀናት ማስቆጠሩን አስታውቀዋል። ግንባታው በሁለት ዙሮች የተከፈለ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን፣ አንደኛው ዙር ከብሎክ 1 እስከ 3 ያሉ ብሎኮች ግንባታ የተጀመረበት ነው ብለዋል፡፡ ሁለተኛው ዙር ደግሞ ከብሎክ 4 እስከ 15 ያሉትን ብሎኮች አካቶ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአንደኛው ዙር ግንባታቸው የተጀመሩት ስትራክቸራል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን የብሎክ ዎርክ እና የልስን ሥራዎችም እስከ አምስተኛ ፎቅ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱ በ24/7 የስራ ባሕል በከፍተኛ ጥራት እና ፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን ፤ ይህ ስኬት እንዲመዘገብ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት እና ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ሚና እንደተጫወተ ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ስለግንባታው ሃሳብ የሰጡት ከአየሰና ባጫ ተቋራጭ ተወካይ ኃይለሚካኤል ዋቆሽ፣ የፊኒሺንግ፣ የቡሎኬት ግንባታ እና የልስን ስራዎችም በፍጥነት እየተከናወን መሆኑን ገልጸዋል። AMN

በወረዳው አስተዳደር በተለያዩ የስራ ዘርፎች የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለጹ ( ወረዳ 03 ኮሙኒኬሽን) ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 በተለያዩ የኢንተርፕራይዝ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው የተሰማሩ ወጣቶች፣ በተፈጠረላቸው የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለጹ።

በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በሚገኘዉ የአዲስ አበባ እንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል በዓላትን ምክንያት በማድረግ ነዋሪዎች በቂ ምርት አቅርቦት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ እየተሰራ ነው። ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም | አቃቂ ቃሊቲ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በዓላትን ምክንያት በማድረግ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ነዋሪዎች በቂ ምርት አቅርቦት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ያስችላል። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በሚገኘዉ የአዲስ አበባ እንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር እና የገበያ ዋጋ ለማረጋጋት የተለያዩ የግብርና ምርት የሆኑ የእንስሳትና ክንስሳት ተዋፅኦ ዉጤቶችን በጥራት እና በስፋት ለህብረተሰቡ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል። ማዕከሉ በቂ የዶሮ፣ እንቁላል፣ የእርድ እንስሳት፣ ቂቤ፣ወተት እና የወተት ተዋፅኦ በየወረዳዉ በሚገኙ የግብርና ዉጤቶች መሸጫ ሱቆችና በተሀያዩ የሚፈጠሩ የገበያ አማራጮች ለሸማቹ ማህበረሰብ የሚያቀርብ ሲሆን ከክ/ከተማዉ በተጨማሪም በተለያዩ የከተማዋ ገበያዎችና ሱቆች የሚያቀርብ በመሆኑ ነዋሪዎቻችን በሚመቻችሁ አማራጭ መሸመት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን ። "#ፈተናን_በስኬት_ቃልን_በተግባር!" ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication

ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር! የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አስተዳደር ቅንነት፣ ተዓማኒነትና ቅልጥፍና ያለዉ አገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ የሰራተኞች የዉይይት መድረክ ተካሄደ። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ከአጠቃላይ የአስተዳደሩ ሰራተኞች ጋር ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን በመዋጋት የተገልጋይ እንግልትን መቀነስና የተገልጋይ እርካታን ማሻሻል በሚቻልባቸዉ መንገዶች ዙርያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። መድረኩ "ዛሬ የምንሰጠዉ ጥራት ያለዉ አገልግሎት፣ የነገዋን ብሩህ ሀገር ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን፣ በዕለቱም የክፍለ ከተማው ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተው በማወያየት ማጠቃለያ ሀሳቦችን ሰጥተዋል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀንጋቱ መሀመድ በመድረኩ መክፈቻ በሰጡት ማብራርያ ሰራተኞች የህዝብ አገልጋይ መሆናቸውን በመገንዘብ ተቋማዊ ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። አያይዘውም አገልጋይ ባለሙያዎች ከነበሩ ችግሮች መላቀቅና የስራ ስነምግባር በመላበስ የሌብነትና ብልሹ አሰራር ችግሮችን በመቅረፍ ጥራት ያለውና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት የነገዋን ብሩህ ሀገር ለመገንባት ቁልፍ መሰረት መሆኑን ገልጸው፣ የአስተዳደሩ ሰራተኞች የአገልግሎት ስታንዳርዳይዜሽን ማስጠበቅ፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማዳበር እና በቅንነትና በታማኝነት ህዝብን ማገልገል እንደሚገባቸው አሳስበዋል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሃድሶ አበባዉ በበኩላቸው፣ የሌብነትና ብልሹ አሰራሮች ተቋማዊ እድገትን እንደሚያጓትቱና ህዝብን ለከፍተኛ እንግልት እንደሚዳርጉ አንስተዉ እነዚህን ችግሮች በግልጽ በመታገል ህዝብን ያማከለ የአገልግሎት እርካታ ለመፍጠር ባለሙያው በለውጥ መንፈስ ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል። ግልፀኝነት የተሞላበት አገልግሎት አመሰጣጥ ሂደት ለመፍጠር በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፣ ፍትሃዊና የተቀላጠፈ ከእንግልት የፀዳ አገልግሎት በመስጠት ጠንካራ ተቋም መገንባት ያስፈልጋል በማለት ገልፀዋል። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ በበኩላቸዉ የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል የሚቻለው ፍትሃዊነትን በማስፈን፣ ልምድና ተሞክሮዎችን በወርቃማ ሰኞ በማስፋት፣ ለተገልጋይ ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣ ለሰራተኛ ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣ የአስተዳደሩ ሰራተኞች ህፃናት ማቆያ እና ሌሎች የስራ ቦታ ምቹነት ማሻሻል የሰራተኛውን የስራ ዲሲፕሊን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰዋል።ተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት በኩል የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ አብራርተዋል። በመጨረሻም የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት እና በተያዘው የጋራ አቋም መሰረት፣ በቀጣይ በየደረጃው ያሉ የስራ ክፍሎች የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ የተቀናጀ ስራ መስራትና ተላልፈዉ የሚገኙ ባለሙያዎች ላይ ተጠያቂነትን በማስፈን ጸረ-ሌብነት ትግሉን አጠናክሮ ለመቀጠል እንዲሁም የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ላይ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ተጠናቋል። "ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር!" ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

የዘመነ መሰረተ ልማት፤ የዘመነ አገልግሎት ለዘመናዊ ከተማ! ዛሬ በከተማችን አራት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ተርሚናሎችና ገበያ ማዕከላት (በጎተራ፥ ቦሌ፣ የካ እና ቀበና) መርቀን አገልግሎት አስጀምረናል። እነዚህ መሰረተ ልማቶች የትራፊክ መጨናነቅን የሚያቃልሉ፣ የትራንስፖርት ሥርዓትን የሚያሻሽሉ፣ ህዝባችንን ከዝናብና ፀሐይ እንግልት የሚከላከሉ፣ በርካታ የስራ እድሎችን የሚፈጥሩ ምቹ ፣ ንፁህ እና የሰውን ክብር የሚመጥኑ የዘመነ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው። መሰረተ ልማቶቹ በአንድ ጊዜ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ ዓቅም ያላቸው ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ እና የአውቶቡስ ተርሚናሎች፣ የአየር ብክለትን የሚከላከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያዎች፣ ሰፊ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች፣ የንግድ ሱቆች፣ ካፍቴሪያና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻና ማረፊያ ስፍራዎች፣ ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች፣ የአስተዳደር እና የትኬት መቁረጫ ቴክኖሎጂዎች፣ አሳንሰሮች እና ንፁህ መፀዳጃ ቤቶች እንዲሁም የደህንነትና የአደጋ ቅድመ መከላከል ሥርዓቶች የተሟሉላቸው የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎትን ለማሳለጥ ትልቅ አስተዋጽዖ የሚያበረክቱ ናቸው። ከለውጡ በፊት 3 ሺህ ብቻ የነበረውን የአንድ ጊዜ የተሽከርካሪ ማቆሚያ አቅም እና ምንም ያልነበረንን ተርሚናል በአሁኑ ጊዜ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ፣ ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን እና ተርሚናሎችን ከ170 ሺህ በላይ ማድረስ ችለናል ። ለከተማችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በተጨባጭ ቃላችንን በተግባር ስራዎችን እየፈጸምን በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን። አዲስ አበባ ከዚህ በላይ ይገባታል ቀጣይም ከሰራነው በላይ እንተጋለን! የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ ለተጋችሁ፣ ላስተባበራችሁ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች በዚህ ስራ የተሳተፋችሁትን ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ጤናው የተጠበቀ ብቁና አምራች ዜጋን ለማፍራት ሚናቸው የጎላ ነዉ። ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጤናው የተጠበቀ ፣ ምርታማ፣ እንዲሁም በአካልና በስነ-ልቦና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ጥራትና ደረጃቸዉ ተጠብቀዉ አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን በየወቅቱ እድሳት እየተደረገላቸዉ ቀጣይነታቸዉም እየተረጋገጠ ይገኛል። ። አስተዳደሩ የታዳጊዎችና ወጣቶች የስፖርት ተሳትፎ ለማሳደግና ጤናማ ትውልድ ለመቅረፅ እያከናወነ ባለው እንቅስቃሴ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ይገኛል። እነዚህ ደረጃቸውን ጠብቀው ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የስፖርት ማዘውተሪያዎች ለታዳጊዎች ምቹ የስፖርት ቦታ ከመሆናቸው ባሻገር የነገ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና በተለይም በዚህ ክረምት ወራት ታዳጊዎችና ወጣቶች ጊዜያቸውን ትርጉም ባለዉ መልኩ በተገቢ ቦታ እንዲያሳልፉ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው። ፕሮጀክቶቹ የታዳጊዎችንና የወጣቶችን ተሰጥኦ ቀድሞ በመለየት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ያለዉ ሲሆን ክፍለ ከተማው በቀጣይም የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማጠናከር እና ስፖርትን የዕለት ተዕለት ባህል ለማድረግ የሚያስችሉ ተጨማሪ መሰረተ ልማቶችን የመገንባትና የማስፋፋት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። "ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር!" ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication

በዓል መውሊድ ኣብ ሓዱሽ ገዛ ፅባሕ ኣብ በዓል መውሊድ ተፀበዩና! AMN plus ትግርኛ #ልዩ_የበዓል_ዝግጅት ነገ ከ7:00 ጀምሮ በAMN plus ትግርኛ ይጠብቁን

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ******* ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉን ስናከብር እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፤ ለሌላቸው በማካፈል፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የታመሙትን በመጠየቅ እንዲሆን እመኛለሁ። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ - ኢድ ሙባረክ!