1 362
Subscribers
+124 hours
+187 days
+2230 days
Posts Archive
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ማስታወቂያ!
(ነሀሴ1/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የሚሰጠዉን ትምህርት ጥራት ለማላቅ ሞዴል አለም አቀፍ የሳይንስ ልህቀት ማዕከል በመፍጠር በትኩረት በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በ2019 የትምህርት ዘመን በምስራቅ ጎህ የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ከ9ኛ እስክ 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የቅድመ ዝግጅት ስራዉን ያጠናቀቀ በመሆኑ በትምህርት ቤቱ ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች በትምህርት ቢሮ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ላይ በተገለጸው የመወዳደሪያ መስፈርት መሰረት በተጠቀሰው የመመዝገቢያ ሊንክ እስከ 8/12/2018 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
መመዝገቢያ ሊንክ፡- https://bs.ministry.et
የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የመንፈሳዊ ሥራ አመራር ኮሌጅ — 60ኛ ዓመት (የአልማዝ ኢዮቤልዩ) የመንፈሳዊ አገልግሎት ጉዞና የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕን ትሩፋትን ለመዘከር ዓለም አቀፍ የኦንላይን (Zoom) ሴሚናር ተዘጋጅቷል።
📅 እሑድ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. 🕗 ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት — በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር
በዚህ ልዩ መርሐ ግብር ላይ እንድትሳተፉ በክብርተጋብዛችኋል።
የZoom መግቢያ ሊንክ - Join Zoom Meeting
https://us06web.zoom.us/j/88944190251?pwd=DTLSeT8VSIm2YKwUxIU4cIA4CHgArm.1
Passcode ፡
Meeting ID: 889 4419 0251
Passcode: 191919
ለውድ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ነባር የተማሪ ወላጆች በሙሉ።
ከሁሉ አስቀድመን የከበረ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረስ።
የ2019 ዓ.ም. የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 6 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. እንዲካሄድ ታቅዶ ቢጀምርም ያልተመዘገቡ ተማሪዎች በመኖራቸው እና ለወላጆች ተጨማሪ ዕድል ለመስጠት ሲባል የምዝገባው ጊዜ ለተጨማሪ ቀናት ተራዝሞ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ተማሪዎችን የመቀበል ሂደት እየተካሄደ በመሆኑ ያሉትን ክፍት ቦታዎች በትክክል ለመለየት የነባር ተማሪዎች ምዝገባን በአፋጣኝ ማጠናቀቅ አስፈላጊ ሆኗል።
ስለሆነም የሁሉም ቅርንጫፎች የነባር ተማሪዎች የመጨረሻ ምዝገባ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ የተራዘመ መሆኑን እናሳውቃለን።
እባክዎ ልጅዎን እስከ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ በሚማርበት ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በመቅረብ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ከተጠቀሰው የመጨረሻ ቀንና ሰዓት በኋላ ያልተመዘገቡ ነባር ተማሪዎች በፈቃዳቸው እንደለቀቁ በመቆጠር በክፍት ቦታው አዲስ አመልካች ተማሪዎችን የምንቀበልበት መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።
ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን።
የዋናው መሥሪያ ቤት
የተማሪዎች ምዝገባና ቅበላ ኮሚቴ
