en
Feedback
ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

Open in Telegram

መንፈሳዊ ቻናል እንጋብዛቹ @EOTCY ምን አይነት ነገሮችን ነው የሚፈልጉት? ➢ የተለያዩ ትምህርቶችን ➢ መጣጥፎችን ➢ መንፈሳዊ ግጥሞችን ➢ ተከታታይ ትምህርቶችን ➢ ብሒለ አበው ➢ ወይስ ዜና ቤተክርስቲያን አሁኑኑ ይቀላቀሉን የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ቀጥተኛ አስተምህሮ ያገኙበታል👇👇👇 @EOTCY

Show more
9 059
Subscribers
No data24 hours
+457 days
-430 days
Posts Archive
+ጊዝው ገና ነው+
አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ። በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት፥ ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል። ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ። ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ። ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።  አንዱ ተነሳና፥ “እኔን ብትልከኝ፥ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱ አይሠራም። ብዙዎቹ አያምኑህም። ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ።  ሌላኛው ተነሳና፥ “እኔን ከላክኸኝ፥ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱም አይሠራም። ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ።  ሌላው ደግሞ ተነሳና፥ “እኔን ላከኝ። ፈጣሪም አለ፥ ገነትም አለ፥ ሲኦልም አለ፤ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ።” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል። ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ፥ ለማዘግየት ይፋጠናል። በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን።” (1 ተሰ 2:18) ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል፥ ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል። እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም። ስለ ጸሎት ብታስብ፥ "አሁን ደክሞሃል። ጊዜው አይደለም። ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል። ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ። የምትጾምበት ጊዜ አይደለም፤ ሌላ ጊዜ ትጾማለህ።" ይልሃል። ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ፤ ጊዜው አይደለም፥ ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል። ንስሃ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ፥ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም። ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ፥ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል። 🟢🟡🔴 በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ፥ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም። እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2ኛ ቆሮ 6፥2) እንደሚል እናስታውስ። ለመዳናችን ቀጠሮ አንስጥ።
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

"አንተ ራስህ ለገዛ ወንድምህ ጨካኝና ይቅር የማትል ኾነህ ሳለስ እግዚአብሔር እንዲራራልህና እንዲምርህ እንዴት መለመን ይቻልሃል? "ባልንጀራህ ምናልባት ንቆህ ሊኾን ይችላል፡፡ አዎ! አንተ ግን እግዚአብሔርን ኹልጊዜ እንደናቅኸው ነው፡፡ በባልንጀራና በእግዚአብሔር መካከልስ ምን ንጽጽር አለ? ባልንጀራህ ምናልባት ጉዳት ሲደርስበት ሰድቦህ ይኾናል፤ አንተም በዚህ ተበሳጭተህ ይኾናል፡፡ አንተ ግን ምንም ሳይጎዳህና በአንተ ላይ ክፉ ሳያስብ ይልቁንም ዕለት ዕለት በረከቱን እየተቀበልክ እያለ እግዚአብሔርን ሰድበኸዋል፡፡ እንግዲህ ተመልከት! ነቢዩ፡- “እመሰ ኃጢአተኑ ትትዐቀብ እግዚኦ መኑ ይቀውም - አቤቱ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ ማን ይቆማል?” ብሎ እንደ ተናገረ እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የምንፈጽመውን በደል ቢመረምር ኖሮ አንዲት ቀንስ እንኳን በሕይወት መቆየት አንችልም ነበር (መዝ.129፡3)፡፡ እያንዳንዱ በደለኛ ሰው ለራሱ የሚያውቀውንና ሌላ ሰው የማይመሰክርበትን እግዚአብሔር ብቻዉን ግን የሚያውቀውንስ ይቅርና የተገለጠውና ሰው ኹሉ የሚያውቀው ኃጢአታችንን እንኳን እግዚአብሔር ቢቈጣጠር ኖሮ ከእነዚህ ኃጢአቶች በኋላ የምንጠብቀው ምንድን ነው? እግዚአብሔር ንዝህላልነታችንንና ጸሎት ስናደርስ የምናሳየው ግድየለሽነታችንን፣ ሠራተኞች ለአሠሪዎቻቸው ወታደሮችም ለአለቆቻቸው ጓደኛሞች ለጓደኞቻቸው የሚያሳዩትን ፍርሐትና ክብር ያህልስ እንኳን ለጸሎትና ለልመና በፊቱ በቆምን ጊዜ አለማሳየታችንን ቢቈጣጠር ኖሮ ምን ነበር የምንኾነው? አንተ ከጓደኛህ ጋር ስትነጋገር ለምታደርገው ማንኛውም ነገር ትጠነቀቃለህ፡፡ ስለ በደሎችህ እግዚአብሔርን ስትጠብቀው፣ ለብዙ መተላለፎችህ ይቅርታን ስትጠይቀው፣ ሥርየትን ለማግኘት ስታሳስበው ግን [በፊቱ ላይ] ኹልጊዜ ግድየለሽ ትኾናለህ፡፡ ጉልበትህ በምድር ላይ ተንበርክኮ ሳለ ልቡናህ ግን እዚህም እዚያም፣ በገበያ ሥፍራም፣ በቤት ውስጥም ይዋልላል፤ ከንፈርህ በከንቱና እንዲሁ ያነበንባል፤ ይህን የምንፈጽመው ደግሞ አንዴ ወይም ኹለቴ ሳይኾን ኹልጊዜ ነው። እንግዲህ እግዚአብሔር ይህን ብቻ እንኳን ቢመረምር ይቅርታን ወይም ምሕረትን እንደምናገኝ ታስባለህን? በእውነት አይመስለኝም!" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ #ትምህርት_በእንተ_ሐውልታት_መጽሐፍ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው @eotcy              @eotcy @eotcy              @eotcy @eotcy              @eotcy

ንስሐ ምንድን ነው? ንስሐ ማለት አንድ ሰው በሠራው ጥፋት፣ ባደረገው ስህተት፣ በፈጸመው ኃጢአት ማዘኑ፣ መፀፀቱ፣ ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኃጢአት ላለማድረግ የሚወስነው ውሳኔ ነው። በአጭሩ ንስሐ ማለት ትርጉሙ ይህ ሲሆን፤ በሰዎች ሕይወት ውስጥ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስገነዝበን ቀጥሎ የተጠቀሱትን ፍችዎች ያጠቃለለ ሆኖ እናገኘዋለን። ➙ ንስሐ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው። ሚልኪያስ 3፥7 ➙ ንስሐ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ ነው። 2 ቆሮንቶስ 6፥19 ➙ ንስሐ ከኃጢአት እንቅልፍ መንቃት ነው። ሮሜ 13፥11 ➙ ንስሐ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ነው። ኤፌሶን 5፥14 ➙ ንስሐ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ እግዚአብሔርን የሚያስወድድ ከንጹህ ልብ የሚመነጭ ጸጋ ነው። ሕዝቅኤል 36፥25-27 ➙ ንስሐ ከኃጢአትና ከዲያቢሎስ ባርነት ነጻ መውጣት ነው። ዮሐንስ 8፥34-36 ➙ ንስሐ ስለ እግዚአብሔር ፍቅርና ስለ ቅድስና ብሎ ኃጢአትን መተው ነው። ምሳሌ 28 ፥13 ➙ ንስሐ ኃጢአትን ከተዉ በኋላ በፍጹም መልሶ አለመስራት ነው። https://t.me/eotcy ➙ ንስሐ ስለ አለፈው ስህተት አብዝቶ ማልቀስ፤ ያለፈውን የኃጢአት ኑሮ ማውገዝና መኮነን ነው። ኢዩኤል 2፥12 ➙ ንስሐ ፍጹም የሆነ የሕይወት ለውጥ እንጂ ጊዜያዊ ስሜት አይደለም፤ ሮሜ 12፥2 ➙ ንስሐ ኃጢአትን ሲሠሩ ከመኖር ይልቅ ከእግዚአብሔር ጋር መኖርን መሻት ነው። መዝሙር 73፥28 ➙ ንስሐ የአዕምሮ መታደስ ነው። ሮሜ 12፥2 ➙ ንስሐ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ የሚያስችል ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር የሚያስገባ ቁልፍ ነው። ማቴዎስ 25፥1-13 ➙ ንስሐ በቀራንዮ መስቀል ላይ እኛን ለማዳንና ከኃጢአት ባርነት ነጻ ለማውጣት የፈሰሰልንን የክርስቶስን ደም እንድናስብ የሚያደርግ መንፈሳዊ ሃብት ነው። ➙ ንስሐ ከኃጢአት የሚያነጻ ሱራፌል ከመንበረ ሥላሴ የወሰዱት የእሳት ፍም ነው። ኢሳያስ 6፥4 https://t.me/eotcy ➙ ንስሐ ከሚመጣው የመጨረሻ መከራና ሃዘን መዳኛ ወይም ማምለጫ መንገድ ነው። ዮናስ 3፥10 ➙ ንስሐ እግዚአብሔር የሰውን ኃጢአት ይቅር የሚልበትና ከኃጢአት ውጤት የሚያድንበት መሳርያ ነው። ➙ ንስሐ ከሰዎች ጋር ለመታረቅ የተዘረጋ የእግዚአብሔር እጅ ነው። መዝሙር 50/51 ➙ ንስሐ እግዚአብሔር ወደ ሰው የሚጣራውን ጥሪ ሰምቶ ወደ እርሱ መመለስ ነው። ዮሐንስ 7፥51። ኤፈሶን 4፥30 ➙ ንስሐ ስለ አለፈው ኃጢአት ከመፀፀት የተነሳ የተሰበረ ልብ ነው። መዝሙር 50/51፥17 ➙ ንስሐ ሰዎች ስለ ኃጢአታቸው ተፀፅተው ከእግዚአብሔር ጋር እንዳይታረቁ በብርቱ በሚጥረው ሰይጣን ላይ የተገኘ ድል ነው። መዝሙር 123/124፥ 6-7:: ወስብሃት ለእግዚአብሔር ! (የንስሐ ሕይወት) ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂ https://t.me/eotcy

#ይህንን_ያውቃሉ የሦስቱ ዲያቆናት ምሳሌነት ምንድን ነው ? ቅዳሴ ላይ እንደሚታወቀው ልዑካኑ  ከሁለት እስከ ሃያ አራት ድርስ ሊደርሱ ይችላሉ አምስቱ ልዑካን  ማለት ሁለት ካህን ሦስት ዲያቆናት በአጠቃላይ የአምስቱ አማዕደ ምሥጢራት ምሳሌ ናቸው ሦስቱ ዲያቆናት የየራሳቸው ምሳሌነት አላቸው 1. የዋና ዲያቆን (ሠራዒ ) ይህ ዲያቆን የቅዱስ እስጢፋኖስ ምሳሌ ነው መጾር ወይም መስቀል ይዟ መቀደሱ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተቀበለውን ሰማዕትነት ለማሰብ ነው 2. ተጨማሪ (ንፍቅ ) ዲያቆን ይህ ዲያቆን ደግሞ መጥመቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ምሳሌ ነው ከፊት ከፊት እየቀደመ  ካህናቱን መምራቱ ሊቀ ካህናት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከፊት ቀድሞ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ጥርጊያውን መንገድን የማዘጋጀቱ ይህ ዲያቆን መብራት ወይም ጠፋፍ የሚያዙ ከመስዋዕት ከማቅርብ አልፎ በዚህ ይመሰላል 3. ፍሬ ሰሞን (መጽሐፍ ገላጽ )   ይህ ዲያቆን የሐዋርያት አባቶቻችን ምሳሌ ነው እንዴት ቢሉ መጽሐፍ ይዞ በአራቱም አቅጣጫ ይዞራል ይህም ሐዋርያት በአራቱ አቅጣጫ ወንጌልን የመስበካቸው ምሳሌ ነው ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂ @eotcy @eotcy @eotcy

ትዝብት
ልጅቷ ሥራ የላትም ፣ ከመኖሪያዋ አጠገብ ካለው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ዘወትር እየተገኘች ልመናዋ ሥራ ስጠኝ ብቻ ከሆነ ሰንብታለች፡፡ በነጋ በጠባ ቁጥር “እባክህን አምላኬ ውዬ የምገባበት ሥራ ስጠኝ” እያለች ትጸልያለች፡፡ አንድ ቀን ቤተክርስቲያን ደርሳ ወደ ቤቷ ስትመለስ ከአንድ መሥሪያ ቤት አጠገብ ትደርስና የተለጠፈ የሥራ ማስታወቂያ አይታ ቆማ ማንበብ ትጀምራለች፡፡ የሥራው ዓይነት እና የትምህርቱ ደረጃ ሁሉ በዝርዝር ሰፍሯል፡፡ ሁሉም እሷ ልታሟላ የምትችለው መስፈርት ነበር፡፡ ደሞዙም አንድ ሺህ ብር ይላል፡፡የመሥሪያ ቤቱ ለመኖሪያ ቤቷ ቅርብ መሆን፣ የትምህርት ደረጃ መስፈርቱ ከእርሷ የትምህርት ደረጃ ጋር መመሳሰል፣ የመነሻ ደመወዙም ቢሆን ይህ ሁሉ ተደምሮ የመቀጠር ጉጉቷን ከፍ አደረገው፡፡ ይኹን እንጂ ከሌሎች ተመዝጋቢዎች ጋር መወዳደር ግድ ስለሆነ የማለፍና ያለማለፍ ጉዳይ እንዳለ ስትረዳ በጣም ተጨነቀች፡፡ ስለዚህ ተመዝግባ ስታበቃ ወደ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አቅንታ “እባክህን ይህን ፈተና አሳልፈኝና የሥራውን እድል ስጠኝ” ስትል ተማጸነች፡፡ ሁሉም አልፎ ውጤት የሚለጠፍበት ቀን ደረሰና በናፍቆትና በጉጉት ታጅባ ለማንበብ ሄደች፡፡ውጤቱ ግን የእሷን ማለፍ የሚያረጋግጥ አልነበረም፡፡ የእሷ ስም የለም ያለፉት ሌሎች ናቸው፡፡ ምንም ሳትናገር ወደ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሮጠች፡፡ እዚያም እንደደረሰች “መድኃኔዓለም ታዘብኩህ” ስትል የምሬት ድምጽ አሰማች፡፡ @eotcy ይህ በሆነ በሳምንቱ ሌላ ማስታወቂያ በሌላ መ/ቤት ወጣ፡፡ ደመዎዙ አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር ነበር፡፡ ይህን ስታይ እንደመጸጸት አለችና “የእኔ መድኃኔዓለም ለካስ ይሄ እንደሚሻል አውቀህ ነው ያኛው እንዲያልፈኝ ያደረከው፣ እባክህን ይቅር በለኝ የአፌን አትቁጠርብኝ ይህን ግን እንዳትከለክለኝ አደራ” ስትል ተማጸነችና ተመዝግባ ውድድሯን ጀመረች፡፡ ሁሉም አልቆ ውጤት ሲለጠፍ አሁንም የእሷ ስም የለም፡፡ ያለፉት ሌሎች ናቸው፡፡ አሁን በጣም አዘነች፡፡ በሃይማኖቷ ላይ ያላት ተስፋ ሲሟሽሽ ተሰማት፡፡ በረዶ እንደወረደበት ሰው የክርስትና ወኔዋ ቀዘቀዘ፡፡ ጊዜ ሳታባክን ወደ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሄደችና  “አሁንስ በጣም ታዘብኩህ” ስትል እሱ የሰጣትን ምላስ እሱው ላይ ዘረጋችው፡፡ @eotcy በዚህ ሁለት ሳምንታት አለፉና አንዲት ጓደኛዋ አንድ መሥሪያ ቤት የሥራ ማስታወቂያ መለጠፉን ነግራት አልመዘገብም ብላ በማኩረፏ በብዙ ጉትጎታ ከቦታው ደረሰች ማስታወቂያውን ስታነበው ሁሉም መረጃ ከሷ ጋር የሚሄድ ሲሆን ደሞዙም ከመጀመሪያው በሁለት እጥፍ ጨምሮ ሦስት ሺህ ብር ይላል፡፡ ከሚቀር እስኪ ልሞክረው ብላ ተመዘገበች፡፡ ተገቢውን ሁሉ አድርጋ የመጨረሻ ውጤት የሚለጠፍበት ቀን ከስፍራው ተገኘች፡፡ አሁን ስሟ አንደኛ ተራ ቁጥር ላይ ተለጥፏል፡፡ በከፍተኛ ብቃት ማለፏን ስታይ ዕንባዋ በዐይኗ ግጥም አለ፣ ሁለቱን ዐይኖቿን ስትጨፍናቸው ቋጥረው የያዙትን የደስታ ዕንባ በጉንጮቿ ላይ ከለበሱት፡፡ ቃል ማውጣት አልቻለችም እየበረረች ወደ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መጣችና እየተንቀጠቀጠች ከታቦቱ ፊት ቆማ ለአፍታ ውስጧን አዳመጠች፡፡ ውስጧም አምላኳን በዚሁ ቦታ ተገኝታ ታዘብኩህ ስትል እንዳማረረችው አስታወሳት ያኔ “የኔ መድኃኔዓለም ታዘብከኝ አይደል?” አለች ለራሷ ብቻ በሚሰማ ድምጽ በቀስታ፡፡ @eotcy 🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂 እኛስ በክርስትና ውጣ ውረድ በማይገባን መዓረግና በሌለን አቅም መድኃኔዓለምን  ስንት ጊዜ ታዝበነው ይሆን? አሁን እኛ እሱን ለመታዘብ ብቃቱ አለን ? እሺ ይሁን እሱስ እኛን አንድ ጊዜ ከፍ አንድ ጊዜ ዝቅ እያልን በክርስትና ጉዞ ብልጭ ድርግም በማለት ስንጓዝ ስንት ጊዜ ታዝቦን ይሆን ለማንኛውም አይደለም እግዚአብሔርን ሰውንም እንኳን ቢሆን ለመታዘብ አንቸኩል ያ ሰው እኛንም ሊታዘበን ይችላልና፡፡
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

ክፉ ሀሳብ እያሰቃያችሁ ነውን??     @eotcy      ክፉ ሀሳብ ሳትፈልጉት መጥቶ አዕምሯችሁ ውስጥ ይታሻል?በጣም የሚዘገንን ክፋት በአዕምሯችሁ ውስጥ ይርመሰመሳል⁉️ እኔኮ ይሄን ላስበው በፍፁም አልችልም አዕምሮዬ የሌላ ሰው እየመሰለኝ ነው ትላላችሁ? ኸረ ይሄ ክፉ ሀሳብ ውስጤ ከረመብኝ በምን ላስወግደው ብላችሁ ተጨንቃችኋል?🤔🤔      አዕምሮ ሀሳብን እንዳይገባ የሚከለክል አጥር የለውም። አጥር የሌለው ቤት ሁሉ ነገር ዘው እንደሚልበት አዕምሮ ውስጥም ብዙ ዓይነት ሃሳብ ዘው ብሎ ይገባል። አዕምሯችን የተጠረገ አስፓልት ነው ሃሳቦች እንዳሻቸው እየነጠሩ ይጓዛሉ። የእግዚአብሔር ሀሳብ ያልፍበታል፤ የሰይጣን ሀሳብ ያልፍበታል፤ የስጋና የደም የምኞት ሃሳብ ያልፍበታል። እነዚህ ሁሉ ሃሳቦች የኛ አይደሉም።    ️ በመንገድ የሚያልፈው ሰው ሁሉ የምናውቀው የኛ ሰው አይደለም። የምናውቀውን ብቻ አቁመን ሰላምታ እንሰጠዋለን። ሃሳብም በአዕምሯችን ሽው ብሎ ሲያልፍ ለሁሉም ሀሳብ እጅ አንነሳም✖️✖️ የእግዚአብሔር ሃሳብ የሆነውን ቅልብ አድርገን እንይዘዋለን አላሳልፍም ብለን የራሳችን እናደርገዋለን።       የተበላሸ ነገር ወደ ሆዳችን ስናስገባ በፍጥነት በሽታው ይጀምረናል ወደ አዕምሮም መጥፎ ሀሳብ ሲገባም አጣዳፊ የአዕምሮ ሁከት ይጀምረናል  ከዛ በአዕምሮህ ወደላይ ወደታች ያሯሩጥሀል። ስለዚህ ምን እንደምትሰሙ፣ ምን እንደምታዩ ተጠንቀቁ ይላል ቃሉ። ይሁዳም የሆነው እንደዚሁ ነው። ሰይጣን በይሁዳ አዕምሮ ውስጥ ሀሳብ አገባበት እርሱም ሃሳቡን ንብረቱ አድርጎ ተቀበለው። ወዲያው አዕምሮው ተቃወሰ።     🔑🔑 ሃሳብ ወደ አዕምሯችን እንዳይገባ መከላከል አንችልም። ይህ ከኛ አቅም በላይ ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ማድረግ ትችላለህ እርሱም የገባውን ክፉ ሃሳብ በተሻለ ሃሳብ ማሸነፍ ትችላለህ። @eotcy     🔴ሰይጣን ጠላት ነው፡፡ አእምሮ ደግሞ ቤት ነው፡፡ ሰይጣን መቼም የማይታረቅህ የዘላለም ጠላትህ ነው። ሰይጣን ቤትህን የቆሻሻ ዓለም እስኪያስመሰለው ድረስ  ክፉ ሃሳብን ከመጣል አያንቀላፋም፡፡ ጠላት የጣለውን ከቤትህ ማስወጣት ያንተ ትጋት ነው፡፡ ችላ ካልከው ግን አንተ ራስህ ለመግባት እስክትቸገር ድረስ ቤትህ ቆሻሻ በቆሻሻ ይሆናል፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ሳይበዛ የጣለውን ጥቂት በጥቂት አስወጣው፡፡ በዚያም ቤትህ በእግዚአብሔር ጸጋ ንጹህ ይሆናል።     📌 ስለዚህ ለምን ክፉ ሀሳብ ውስጤ ገባ ብለህ አትብሰልሰል። ይሁዳ ከነጴጥሮስና ዮሀንስ የተለየ ፍጥረት ስለነበር አይደለም ሰይጣን የተጠቀመበት ይሁዳ ውስጥ የገባው ክፉ ሀሳብ እነጴጥሮስ ውስጥም ገብቶ ድል ነስተውት ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ሃሳቡ እንዳይገባ ማድረግ አትችልም እንዲወጣ ግን ማድረግ ትችላለህ። @eotcy        ክፉ ሀሳብ ውስጥህ ሲመጣብህ መልካም በሆነው ድል በሚነሳው በወንጌል ቃል አክሽፈው። አቤቱ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ውስጤ ሰርጎ የገባውን ክፉ ሀሳብ በስምህ ጠርገህ አስወግድልኝ፤ ከነዚህ ክፉ ሃሳቦች መዳን ወዳለሁና አቤቱ ከስራቸው ነቅለህ ጣላቸው ብለህ ፀልይ⛪️⛪️። እግዚአብሔር ይንቀልላችሁ!! 📌 "ወፍ ከራስሕ  በላይ  እንዳትበር  ማድረግ አትችልም ይሁን እንጅ በአናትህ ላይ መጥታ ጎጆ እንዳትሠራ ማድረግ ትችላለህ፡፡ ልክ እንደዝሁ መጥፎ ሐሳብ ወደ አዕምሮህ እንዳይገባ ማድረግ አትችልም ነገር ግን የገባውን አለማስተናገድ ትችላለህ" ╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮ ✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥    @eotcy  @eotcy

ከዝሙት መሸሽ እያነበባችሁ ሼር ልጄ ሆይ ከጎደኛህ ቤት ሄደህ ጓደኛህ ባይኖር ሚሥቱ ብቻ ብትኖር እቤት አትግባ ነውር ነው። አንተ ባታሥብ እንኳ ያየህ ሠው በሐሜት ያሰናክልሀልና። እናንተም ሠው ናችሁ እና በፈተና ትወድቃላችሁ መልካም ወንድ የሠው ሚሥትን ፊቷን ሞልቶ አይመለከትም፣ መልካም ሤትም እንደዛው የሠው ባልን ከባሏ ውጭ ያሉትን ፊቷን ሞልታ አትመለከትም። ሞልቶ ከተመለከታት በዝሙት መንገድ እየሄደ ነው ወይም እየሄደች ነው። መልካም ወንድ በጨዋታ ከሴት ጋር አይላፋም፣ ይህን ካደረጉ ክብራቸው ከጫማቸው በታች ነው!!! መልካም ወንድ ሠው በሚያጠራጥረው መልኩ ከሤት ጋር አይቀራረብም። ልክ በሌለው መቀራረብ ተሠናክለው እራሳቸውን ያዋረዱ ብዙዎች ናቸው። / የጓደኛቸውን ሚስት ወይም ባል እያማገጡ ህሊናቸው እንደ ጦር እየወጋቸው እየኖሩ ያሉ በርካታ ናቸው።!!!    የዝሙት ፈተናን ለማለፍ ሸሽተክ አምልጥ እንደ አባታችን ዮሴፍ እጋፈጠዋለሁ ካልክ ትወድቃለክ። ረጅም መንገድ ከማታውቀው ተቃራኒ ፆታ ጋር ተቀምጠው አትጓዝ። መቀራረብ፣ መተዋወቅን፣ መተዋወቅ፣ መዋደድን፣ መዋደድ መፋቀርን፣ ማፍቀር ዝሙትን ወልዶ ከልዑል እግዚአብሔር ደጅ ያሶጣኻል። ወይንም ያሶጣሻል!!! ዘወትር ደሙ ያልደረቀ ሥጋ እየበላክ መዓዛውን በአፍንጫህ የሚሰነጥቅ አልኮል እየጠጣህ እራሴን ከዝሙት እጠብቃለሁኝ ማለት      ግመል ሠርቆ አጎንብሶ መሄድ ማለት ነው። ሤት ልጅ በአፍህ አምሮብሻል ቆንጆ....ነሽ ብለህ ሥታደንቅ በአንደበትክ እየዘሞትክ ነው። በየመንገዱ ልዑል እግዚአብሔር ያሣመራቸውም ይሁኑ በቀለማ ቀለም አምረው ብታገኛቸው አይንህን ከሷ ላይ ቶሎ ካልነቀል በአይንህ እዘሞትክ ነው። ተጠንቀቁ!!! በአሁኑ ዘመን ዲያቢሎስ በውበት ሠበብ ፍቅር አስመስሎ የዝሙት መንፈስ አውርዷል። እራሳችንን እንጠብቅ እግዚአብሔር ከዚህ መንፈስ ይጠብቀን ምን ጊዜም ቢሆን ፈሪሐ እግዚአብሔር ይኑረን። ወሰብሐት ለእግዚአብሔር... 🟢 @eotcy 🟢 🟡 @eotcy 🟡 🔴 @eotcy 🔴

.                   ግን ለምን❓ መጽሐፍ ቅዱስ የኛ ሆኖ ሳለ ግን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አውጥተው ሚጠይቁን ሌሎች ናቸው ለምን ይህ ሆነ? ለምን ጠያቂ አልሆንም? ለምን በጥያቄ አስጨናቂዎች አልሆንም? 👉እውነት ነው ሁላችንም ዘመን የማይሽረው ስህተትን እየሰራን ነው። ✝ በአንድ  ወቅት አንድ ህጻን ልጅ መጽሐፍ ቅዱስ ሊነካ ሲል እናቱ ይሄ የእግዚአብሔር ነው እያለች ትቆጣዋለች ልጁም በዚህ ድርጊቱ ይቀጥልበታል  እናም አንድ ቀን እንደተለመደው ሲነካ እናት "የእግዚአብሔር ነው አትንካአላልኩህም ነበር ወይ!" ስትለው ልጁም :-" የእግዚአብሔር ከሆነ ለምን አንመልስለትም?" ብሎ መለሰላት 👉 ሁላችንም ትራሳችን ውስጥ፣ በየመጽሐፍ መደርደሪያው ላይ ያኖርነው መጽሐፍ ቅዱስ  ቅዱስ ካስባሉት አንዱና ዋነኛው ወደ ቅድስና ስለሚመራን ነው ። እኛ ኦርቶዶክሳዊያን ለሁሉም ነገር መልስ ኖሮን ሳለ በእራሳችን ስህተት ብዙ ሺ በጎችን አጥተናል። እያጣንም እንገኛለን በዚሁ መተኛታችን ከቀጠልን ዘመንና ትውልድ ይወቅሰናል "...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2 ☟︎︎︎ ━━━━━━━━━━━━━━━ ☟︎︎︎     ♡ ㅤ   ⎙ㅤ     ⌲         ✉️       ˡᶦᵏᵉ     ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ

ይህ ጹፍ ካላስተማረን ምን ሊያስተምረን ይችላል❓ ሴተኛ አዳሪ ስለሆንኩ ጧፉን ልነካ አልችልም❗️ ምን ቢመሻሽም ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትን ተሳልሜ ልምጣ ብዬ ወደ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሄድኩኝ፣ ወርሃዊ በዓላቸው እንደመሆኑ መጠን መግቢያው በር ላይ ግርግር አለ፣ አንዲት ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ጧፍ የምትሸጥ ነጋዴ ጋር አንዲት ነጠላ የተከናነበች ወጣት ጧፍ ለመግዛት ቆማለች፣ እኔም አጠገባቸው ነኝ "ወንድም ይቅርታ አለችኝ" ወጣቷ "አቤት" አልኳት እኔ ስለማልገባ ነው ይህንን ጧፍ ስጥልኝ" አለችኝ እኔም ተሳልሜ ነው የምመለሰው ለሚገባ ሰው ስጪው" አልኳት እሺ ለሚገባ ሰው አንተ ስጥልኝ አለችኝ፣ እኛ ስንነጋገር ተሽከርካሪ ወንበሩ ላይ ያለችው ጧፍ ነጋዴ ጧፉን እንደያዘች እጇን ዘርግታለች፣ እሺ ችግር የለውም እሰጥልሻለሁ ግን ለምን አንቺ አትሰጪም አልኳት፣ እኔ ሴተኛ አዳሪ ነኝ እንዴት በእጄ እነካዋለሁ ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ ሲቀደስ የሚበራ አይደለም❓ አረክሰዋለሁ ብዬ ነው አለችኝ ደነገጥኩ አንዳቺ የሆነ ፍርሃት ሰውነቴን ወረረኝ ከዚህ በኋላ መልስ አልሰጠዋትም። እሺ ብቻ ብዬ ጧፉን ከጧፏ ነጋደዋ ተቀበልኩላት፣ ብሩን ስትከፈላት እግዚአብሔር ይስጥልኝ ብላ ስትመርቀኝ አስታውሳለሁ፣ አንገቴን አቀረቀርኩኝ እኔ ግን ንጹሕ ሁኜ ነው❓ ይህንን ጧፍ የያዝኩት እንዴት ያለሁ ደፋር ነኝ ፣ ለምን እኔም ካንቺ የባስኩኝ ኃጢያተኛ ነኝ እኔም አልነካውም አላልኳትም❓ ስል ራሴን ሞገትኩት፣ አንተ ውሸታም ጧፍ አይደለም ከታቦቱ ጋር ስትጋፋ አላውቅህም ሲል ጭንቅላቴ ወቀሰኝ፣ እኔ ዞርም ብዬ አላየዋትም ምናልባት እሷ ግን እየተመለከተችኝ ከሆነ ብዬ ወትሮ አደርጌው የማላውቀውን ወደ ቤተክርስቲያኑ ቅጥር ስገባ ተንበርክኬ መሬቱን ሳምኩኝ ፣ አረማመዴንም አስተካከልኩኝ ፣ ምናልባት ንጽሕናዬን ካረጋገጠልኝ ብዬ ወይ አምላኬ በስንቱ ታስተምረኛለህ❓ አቤት ይህን ግን ዮሐንስ ሐጺር በኖረ ስል ተመኘሁ፣ የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው የሚባለው ትርጉሙ ለካስ ይህ ነው ወንጌል ላይ ያለው ቀራጭ ትዝ አለኝ ጌታ ያመሰገነው፣ ከዛ ቀራጭ ግን ይህቺ ሴት ትበልጣለች ፣ እርሱስ ወደ ምኩራብ ገብቶ ነው፣ ይህች ሴት ግን ደጄ ሰላሙ ጋር እንኳን አልቀረበችም ፣ እንዲህ ያለ ትሕትና እንደምን ያለትሕትና ነው❓ እንደዚህስ ያለ እግዚአብሔርን መፍራት እንደምን ያለ ፍርሃት ነው❓ በዚህ ዘመን አይቼውም ሰምቼውም የማላውቀው ወይ ግሩም። እስቲ በዚህ ጽሑፍ እስቲ እራሳችንን እንመርምር አቤቱ የሰራዊት ጌታ ቅዱስ እግዚአብሔር የማደሪያውን መቅደስ እንፈራው እንንቀጠቀጥለት  ዘንድ  ማስተዋልን ይስጠን❗️❗️
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

📌 ቅዱሳን ስእል ለመጀመሪያ ጊዜ የሳለው ማነው❓ 📌 የቅዱሳን ስእሎች ጥቅም ምንድን ነው❓ 📌 በቅዱሳን ስእል ፊት ለምን እንፀልያለን❓
ስእል ከእግዚአብሔር ጋር የተያያዘና በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ያለ ነው ስእል በእግዚአብሔር ፊት የተሠጠ ሕግ ነው። ስእል በብሉይ ኪዳን ለመጀመሪያ ጊዜ የሳለው ነብዩ ሙሴ ነው። ስርየት መክደኛውም በታቦቱ ላይ ታደርገዋለህ እኔም የምሰጥህን ምስክር በታቦቱ ውስጥ ታደርገዋለህ በዚያም ከአንተ ጋር እገናኛለሁ (ዘጸ 25:21-22) በቤቱም ግንብ ዙሪያ በውስጥና በውጪ በኪሩቤል ናዘንባባ የፈነዳ አበባ ምስል ቀረፀ (1 ነገ 6:29) ሠለሞንም የእግዚአብሔርን ቤትና የንጉሱን ቤት ጨረሠ በእግዚአብሔር ቤትና በራሱ ቤት ይሠራው ዘንድ በልብ ያሰበውን ሁሉ አከናወነ እግዚአብሔርም ለሰሎሞን በሌሊት ተገልጦ እንዲህ አለው ፀሎትህን ሰምቻለሁ ይህም ስፍራ ለራሴ ለመስዋት ቤት መርጫለሁ (2 ዜና 7:11-12) እግዚአብሔር ስእሉን መቀበሉን ያሳያል።። አንተ የሰው ልጅ ሆይ ጡቡን ወስደህ በፊትህ አኑረው የኢየሩሳሌምንም ከተማ ስዕል ሳልባት ክበባት ምሽግም ስራባት ይህም የእስራኤል ቤት ምልክት ይሆናል (ሕዝ 4:1-3) ስእል በሐዲስ ኪዳን ለሀዲስ ኪዳን ስዕል መሠረቱ ብሉይ ኪዳን ነው ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስጋ ለብሶ ሠላሳ ሶስት ዓመት ከሶስት ወር በዚች ምድር በተመላለሰ ጊዜ ስዕል ኪሩቤል ባለበት ቤተ መቅደስ የተለየበት ጊዜ አልነበረም ዕለት ዕለት ሥዕለ ኪሩብ ባለበት ቤተ መቅደስ ተገኝቶ አስተምሯል። (ማቴ 26:55) ቤተ መቅደስም የአባቴ ቤት ብሎታል (ዮሐ 2:16) ቤቴ የፀሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው (ማቴ 21:12-3) በሽተኞችን በመቅደስ ውስጥ ተገኝቶ ፈውሶዋቸዋል (ማቴ 21:14) ይህ ሁሉ የተደረገው ስዕለ ኪሩቤል ያለበት መቅደስ ውስጥ ነው። ባያስፈልግ ኖሮ ሥዕሎቹ አግባብ እንዳልሆኑ ባመለከታቸው ነበር። ገንዘብ ለዋጮችን ገበታዎችን የርግብ ሻጮችን ወንበር ገልብጦ ከቤተ መቅደስ ባስወጣ ጊዜ ሥዕል ባስወጣ ነበር። ማታስተውሉ የገላቲያ ሰዎች ሆኖ በዓይኖቹ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተሰቀለ ሆኖ ተሰቅሎ ነበር (ገላ ፣3:1) ቅዱሳን ስዕላት ጥቅሙ ለትምህርተ ወንጌል ይጠቅማል ማንበብ መስማት የማይችሉ ሰዎች ስእሉን ተመልክተው መማር ይችላሉ። ለምሳሌ የጌታችን ብስራቱን፣ ልደቱን ፣ ጥምቀቱን፣ ተአምራቱን ፣ መከራ መሰቀሉን ፣ ርደተ መቃብሩን ፣ ትንሣኤውን ፣ እርገቱን ፣ ዳግም ምፃቱን የሚያመለክቱ ናቸው። በቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን ስዕላት ማስተማሪያ ብቻ አይደሉም ልክ እንደ በትረ ሙሴ እንደ ኤልያስ መጎናፀፊያ እንደ ኤልያስ ቅርፊት እንደ ቅዱስ ጳውሎስ የልብስ ቁራጭ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስም ጥላ የሀይለ እግዚአብሔር መገለጫዎች ናቸው። በቅዱሳን ስዕል ፊት ለምን እንፀልያለን? በስዕል ፊት ቆሞ መፀለይና መስገድ ስዕሉን አምላክ ነው ብሎ ማምለክ ሳይሆን ለስዕሉ ባለቤት ያለንን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽና በረከት ለማግኘት ነው እግዚአብሔር በኦሪት አትስገዱላቸው ያለው ለአህዛብ ጣዖታት ምስሎች ነው እንጂ ለቅዱሳን ስዕላት አለመሆኑን (ዘውልቅ 16:45) ,ሙሴና አሮን ወደመገናኛው ድንኳን መጥተው በታቦትና በስዕል ኪሩብ ፊት እየሰገዱ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ይቀበሉ እንደነበርና የእግዚአብሔር ክብር ይገለጥላቸው እንደ ነበር እናያለን ስለዚህ ለቅዱሳን ስዕል ክብር ልንሰጥ ይገባል አንዳንዶቹ ስዕል የምናመልክ የሚመስላቸው አሉ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል (2 ጢሞ 1:12) እኔ ግን አላፍርም ያመንኩትን አውቀዋለሁ ይላል። ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂ https://t.me/eotcy

​​​​
ሰኔ ፳፩
#
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው❗
ሰኔ20 እና 21ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል። የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የታነጸው በዛሬዋ ቀን ነው አናጺውም እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ✍ ቦታው ፊልጰስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው። ጴጥሮስ፤ ዮሐንስ በርናባስና ሌሎችም ሐዋርያት በፊልጰስዩስ ተሰብስበው ሳለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል እመቤታችን በቀኙ ነበረች፤ 3 ድንጋዮችን አንስቶ ጎተታቸው እንደ ሰም ተለጠጡ እንደ ግድግዳም ሆኑ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድረጎ አነጻት ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፤ ዳግመኛ በበነጋው ሰኔ 21 ቀን እመቤታችንን እና ቅዱሳን መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል ቅዳሴ ቀድሶ ለሐዋርያቱ አቆረባቸው ፍጹም ደስታም ሆነ። ከዚህ በኃላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያን አንጸዋል። ከዚያ በፊት የነበረው የነሶሎሞን ቤተ መቅደስ የአይሁድ ምኩራብ የአይሁድ ስርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ እንጂ የአዲስ ኪዳን የቁርባንም ሆነ የጥምቀት ስርዓት መፈጸሚያ አልነበረም፤ ታዲያ ሐዋርያት የት ነበር ህዝቡን የሚያጠምቁት የሚያቆርቡት ካሉ በየሰው ቤት ነበር። ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን ታላቁ ነብይ ኤልሳዕ አረፈ። ይህ ነብይ በ 12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነብዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው፤ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ይለዋል ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርቢኝ ይለዋል፤ እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት፤ ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። የእምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች፤ የዚህ ነብይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገስት ላይ በስፋት ተጽፏል ሰኔ 20 ቀን እረፍቱ ነው ቤተክርስቲያን የዛሬውን ቀን እመቤታችንን እና ነብዩን አስባ ትውላለች። .......የተወደደችው ጊዜ አሁን ፤ የመዳን ቀን አሁን ነው። 1ኛ ቆሮ 6÷2          Join @eotcy

+++ " #ለዚህ_መቼ_ጸለይን❓" +++ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ቤተሰባዊ የሆኑ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲረዳ የተቋቋመ የካህናት (የቀሳውስት) ጉባኤ ነበረ። የቀድሞው የቅብጥ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳም ይህን ስብስብ እንዲቀላቀሉ ለአባ ሚካኤል ባቀረቡላቸው ጥሪ መሠረት የዚህ ጉባኤ አባል ሆኑ። ታዲያ አንድ ቀን አባ ሚካኤልን ጨምሮ የጉባኤው የበላይ ኃላፊ የሆኑት ጳጳስና ሌሎችም ካህናት የተጣሉ ባልና ሚስትን ሊያስታርቁ ተሰበሰቡ። ይሁን እንጂ የባልና የሚስትየው ጠብ እንዲህ በቀላሉ ሊበርድ የሚችል አልነበረምና ጳጳሱም ሆኑ ቀሳውስቱም ሁለቱን ለማስማማት ብዙ ቢጥሩም ግን አልተሳካላቸውም። በስተመጨረሻም ጳጳሱ ወደ አባ ሚካኤል እየጠቆሙ "አባ ሚካኤል ለምን ዝም ብለው ተቀመጡ? እስኪ እርሶ ይሻላል ብለው የሚያስቡትን ይንገሩን❓" አሏቸው። አባ ሚካኤልም "ብፁዕነትዎ፣ #እንጸልይበት❗" አሉ። ጳጳሱም " #ይህን_ጉባኤ_ከመጀመራችን_በፊት_እኮ_ጸልየናል" ቢሏቸው አባ ሚካኤል " #አዎን_አባታችን_ለዚህ_ችግር_ግን_አልጸለይንም" አሉ። ከዚያ ሁሉም ለጸሎት ተነሡ። በጳጳሱ ፈቃድ በአቡነ ሚካኤል መሪነት ጸሎት አደረጉ። ጸሎቱ እንዳለቀም እነዚያ የተጣሉት ባልና ሚስት ክርክራቸውን ሁሉ ትተው በጉባኤው ፊት በፍቅር ተቃቀፉ። ሰላም አወረዱ። ይህን ጊዜ ከቀሳውስቱ አንዱ "አባታችን ከመጀመሪያ እንዲህ ቢሉን ምን ነበር❓ #አሳረፉን_እኮ" ብለው ጉባኤውን ፈገግ አሰኙት። እኛስ ያልጸለይንባቸው ስንት ችሮች አሉብን❓ ብዙ ቋጠሮ የሚፈታው ግን በብዙዎች የሚረሳው ትልቁ መፍትሔ፣ ጸሎት❗ (አባ ሚካኤል ኢብራሂም (1899-1975) የግብጽ ቤተ ክርስቲያንን ለበርካታ ዓመታት በትጋት ያገለገሉና እጅግ የሚያስቀና የጸሎት ሕይወት የነበራቸው አባት ናቸው። በእርሳቸው ጉዳይ ከሰሞኑን መመላለሳችን አይቀርም። ዲያቆን አቤል ካሳሁን 🟢 @eotcy 🟢 🟡 @eotcy 🟡 🔴 @eotcy 🔴

አስተማሪ መልእክት ነው አንብቧት ልቦናውን ሰብሰቦ መጸለይ ያቃተው ወጣት አንድን አባት እንዲህ ሲሉ ይጠይቃቸዋል፣ አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ሳነብ ልብናዬ አይሰብልኝም። አፌ ቢያነብም ልቦናዬ አይተረጉምም አፌ ቃል ይናገራል አዕምሮየ ግን የጎደለኝን ያጣሁትን ነገር ያሰላስላል። እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው:- ቅዱሳን በፍጹም አሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የደረሱትን እኔ በልቤ ላይ የዚህን አለም እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደገደል ማሚቶ አፌ ላይ ብቻ እየነጠረ ይሄዳል እንጂ ጸሎት አይሆንልኝም። ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል? ብሎ ጠየቃቸው። አረጋዊ አባትም:- እንዲህ ሲሉ አስረዱት አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምፅ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጂ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም። ስለዚህም አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው። ........አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና። ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች። እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው። አሁን አንዱን ይዘህ ወደ ፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማግኘት መጣር ይኖርብሃል እንጂ አንተው በዳይ አንተው አኩራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫዎቻ እንዳትሆን ጸሎትህን አትተው አሉት። እኛም እኮ ብዙ መጸለይ ፈልገን በብዙ ሰበብ ሳንጸልይ እንቀራለን ፈጣሪ ግን የልባችንን ያውቃልና ሁሌም ሃሳባችንን ይሞናልናል እግዚአብሔር ሃሳባችንን ሕልማችንን እውን ያድርግልን "...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2 Https://t.me/eotcy

ክርስቲያናዊ አለባበስ          አንብቡት ይጠቅማቹሃን👇 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው፡፡” ዘዳ. 22፡5 ስለ አለባበሳችን እንወያያለን ዛሬም እህቶቻችን ላይ እናተኩራለን አበዛኸው ምነው እኛን ብቻ እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለው፡፡ ስለ አለባበስ መነጋገር ያስፈለገን እውነተኛ ክርስቲያን በአነጋገሩ፣ በአረማመዱ፣ በአመጋገቡ፣ በአለባበሱ፣ ብቻ በሁሉ ነገሩ የተለየ መሆን ስላለበት ነው ይኸውም ሁሉን በአግባብና በሥርዓት ስለማድረግ ነው እህቶቻችን ላይ ማተኮር ያስፈለገው ደግሞ በአብዛኛው በዚህ ረገድ ትችት የሚበዛው እነሱ ላይ ስለሆነ ነው፡፡ እነሆ ውድድሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረና እየከፋ ነው ለመልካም ነገር መወዳደር ባልከፋ ነገር ግን በከተማችን በተለይም በዋና ዋና መንገዶች ላይ የምናየው የእህቶቻችን አለባበስ አንዷ ከሌላዋ ልቃና በልጣ ለመታየት የሚደረግ ግብግብ እንደሆነ መገመት አያዳግትም፡፡ በእርግጥ እህቶቻችን በዚህ እንደማይስማሙ እናውቃለን አብዛኞቹም ስለተመቸኝና የምወደው አይነት አለባበስ ስለሆነ ነው እንዲህ የምለብሰው ይሉናል ይሁን እንጂ እውነታው ሌላ ይመስላል ምክንያቱም:- * ብርድልብስ ለብሰን እንኳን በማንቋቋመው የብርድ ወቅት ሰውነትን በቅጡ የማይሸፍን ብጣሽ ጨርቅ ጣል አድርጎ መውጣት እንዴት ያለ ምቾት ነው? *እጅግ አስጨናቂ ሙቀት ባለበት ሰዓት ሰውነት ላይ ተጣብቆ ሌላ ጭንቀት የሚፈጥር አለባበስ እንደምን ብሎ ያስደስታል? ዓላማችን ምንም ይሁን እሱ ላይ የመከራከር ፍላጎት የለንም ነገር ግን አለባበሳችንን እንደ ክርስቲያን እንፈትሸው ዘንድ ይገባልና ይህ ተፃፈ መሰልጠን ወይስ መሰይጠን? አብዛኞቹ ሴቶች ይህን ተግባር ስልጣኔ እንጂ ስህተት ነው ብለው አያምኑም፡፡ ለነዚህ ሴቶች ከኃይማኖት ብቻ ሳይሆን ከባህላችን ጭምር ያፈነገጠውን የምዕራባውያን አለባበስ መልበስ ዘመናዊነት ነው፡፡ ላንቺስ? መጽሐፍ ቅዱስስ ምን ይላል?     ማንኛዋም ሴት የሰውነቷን ቅርፅ የሚያሳይ ወይም ክፍትፍት ልብስ ለብሳ መሄዷ የሁሉንም ወንዶች ስሜት መፈታተኗ እርግጥ ከመሆኑም በላይ በመንፈሳዊ ህይወት ደካማ የሆኑትን ደግሞ ለኃጢያት አጋልጦ ይሰጣል፡፡ እዚህ ላይ የተሳሳተው በራሱ ደካማነት ነው ብሎ ምክንያት መስጠት አይቻልም እግዚአብሔር የሚጠይቀው በማን ተሰናከለ የሚለውን ጭምር ነውና በክርስትና ደግሞ ሰውን ማሰናከል እጅግ የከፋ ኃጢያት ነው፡- “ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባህር መስጠም ይሻለው ነበር፡፡” ማቴ. 18፡6 አንዳንድ ሴቶች እግዚአብሔር ምን ሰራሽ እንጂ ምን ለበስሽ አይለኝም ይላሉ እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል “እንግዳ ልብስ የሚለብሱትንም ሁሉ እቀጣለው፡፡” ትን.ሶፎ. 1፡18 እንግዲህ የሴቶቹን እንቀበል ወይስ የእግዚአብሔርን ምርጫው ያንቺው ነው እህቴ መጽሐፍ ግን እንዲህ ይላል፡- “ከስው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል፡፡” የሐዋ. 5፡29 በሴቶችና በወንዶች መካከል የአለባበስ ልዩነት ሊኖር ይገባል “ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው፡፡” ዘዳ. 22፡5 ታዲያ ቀሚስን የወንድ ሱሪን የሴት ማን አደረገው? ይህ የሰነፍና ለስህተታቸው ምክንያትን የሚሹ ሴቶች የሚያነሱት ጥያቄ ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ እኛ ኦርቶዶክሳውያን የእግዚአብሔርን ቃል አውቀን ልንፈፅመው እንጂ በቃሉ ላይ የምንፍቅና ጥያቄ እናነሳ ዘንድ ተገቢ አይደለም ግን ደግሞ ተፈጥሯችንን ብቻ በማየት ህሊናችን እራሱ ቢናገር ሱሪ የሴት ነውን? ቀሚስስ የወንድ ነው እንዴ “ተፈጥሮ እንኳን አያስተምራችሁምን? 1ኛ ቆሮ. 11፡14 ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም፡፡” 1ኛ. ቆሮ. 11፡16 ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ስህተት መሆኑን መናገር እንጂ መከራከር አያስፈልግም ክርስትና በምርጫ ነውና፡፡ በፊትህ እሳትና ውሃን አኑሬአለው ወደ ወደድከው እጅህ ክተት፡፡” ሲራ. 15፡15 እዚህ ላይ ግን ቀሚስ ሲባል ከውስጥ ሱሪ የማይሻለውን ብጣሽ ጨርቅ እንዲሁም ቁመቱ ረዥም ሆኖ ከሰውነት ጋር የሚጣበቀውን አይነት አለባበስ ማለት እንዳልሆነ ልብ እንበል፡፡ https://t.me/eotcy እህቶቻችን ሆይ ማስተዋልን ትላበሱ ዘንድ እንለምናችኋለን መሰልጠንና መሰይጠንም ትለዩ ዘንድ ይሁን ሰውነትሽ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ነውና ሁሉን በአግባብና በሥርዓት አድርጊለት፡፡ ደግሞም ክርስትና ራስ ወዳድነትን አብዝታ ትጠላለች ምንም ነገር ስናደርግ ስለ ሌላው ሰው ልናስብ ያስፈልገናል እኛስ ሰውን ወደ ዝሙት ሊያመራው ስለሚችል አለባበሳችን እጅግ ተጨነቅን ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ ወንድማችንን ስለማሰናከል ምን አለ “መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘላለም ከቶ ሥጋ አልበላም፡፡” 1ኛ.ቆሮ 8፡13 https://t.me/eotcy እንግዲህ ክርስትና እዚህ ድረስ ነው ስለራሳችን ብቻ ሳይሆን ስለ ወንድሞችና እህቶቻችን የምናስብባት ለእነሱም መሰናከያ እንዳንሆን እየተጠነቀቅን ሁሉን በአግባብና በሥርዓት የምናደርግባት፤ እምነታችንን በምግባር የምንገልጽባት ናት፡፡ በእውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር ዝንጉርጉርነቱን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን፡፡ ትን.ኤር. 13፡27 እህቴ ሆይ አንቺም ኤርሚያስ እንዳለው ኢትዮጵያዊነትሽን ጠብቂ የምዕራባውያን በዓል ከሆነው አለባበስም ሆነ የምንዝር ጌጥ ራስሽን አርቀሽ በሚያኮራው ኢትየጵያዊ ባህላችን ትዋቢ ዘንድ እግዚአብሔር ይርዳሽ፡፡ ለሁላችንም አስተዋይ ልቦና ይስጠን፡፡ አሜን!!!! ሁላችን ምግባር ያለው እምነት እንዲኖረን እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ አሜን!!! ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የቀደመችው እውነተኛይቱ መንገድ!!!       የቅዱሳን አምላክ ማስተዋል ይስጠን 🤲 ወ ስ ብ ሐ ት   ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ   ድ ን ግ ል ወ ለ መ ስ ቀ ሉ   ክ ብ ር   አ ሜ ን  🤲

እውነተኛ ማንነታችን በስም ፣ በማዕረግ በዕውቀት ፣ በዕድሜ....ተሸፍኖ ሊኖር ይችላል፣ ዛሬ ብዙዎቻችን ጋር ያለው ከልብ ያልኾነ የማስመሰል ክርስትና ነው። ቤተ ክርስቲያን ሄደን ስለ ተሳለምን ስለ ተማርን ስላስተማርን ስላስቀደስን ስላነበብን ስለ ዘመርን ገዳማት ስለጎበኘን ስላደነቅን ክርስትናን እየኖርን ከመሰለን ተሳስተናል። ይኽ የሥርዓተ አምልኮ ክፍል እንጂ ፣ በራሱ ብቻውን ክርስትናዊ ሕይወት መገለጫ አይደለም። የተክል ፍሬ እንዲያፈራ ውሃ፣ አፈር የፀሐይ ብርሐን እንደሚያስፈልገው፣ ከላይ የተዘረዘሩትን (መሳለሙ ፣ ማገልገሉ) መንፈሳዊ ፍሬ እንዲናፈራ የሚያደርገን ናቸው እንጂ በራሳቸው ግብ አይደሉም። አብዛኞቻችን ግን በእነዚህ ብቻ ታጥረን (ረክተን) ቆመናል) የክርስትና / የመንፈሳዊ ሕይወት መገለጫው ፍቅር፣ ቅድስና፣ ንጽሕና፣ ትሕትና፣ ትዕግስት፣ ቅንነት፣ ይቅር ባይነት፣ በሌላ አለመፍረድ፣ .....የመሳሰሉት ናቸው። በመመላለሳችን እነዚህ ኹሉ ከሌሉ (ቢያንስ ለመተግበር ካልቀረብን) የክርስትና ጭምብልን አጥብቀን እየተወንን እንጂ ክርስትናን እየኖርነው አይደለም። ብርሃን ከጨለማ በቀላሉ እንደሚለይ ክርስትናንም በግብሩ (በምግባሩ) በሥራው ከአሕዛብ በቀላሉ ይለያል። መለያው ደግሞ "ሕይወቱ" እንጂ የአገልግሎት ተሳትፎው አይደለም። ይሄን ለይተን ክርስትናን የምንተገብርበት ጥበብ ያድለን ብርሃን "...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

#በዓለ_ጰራቅሊጦስ፤ (#በዓለ_ሃምሳ ) በዓለ ጳራቅሊጦስ ከ፱ኙ ዐበይት በዓላተ እግዚእ አንዱ እንደመኾኑ #ሰኔ 16 #ቅዳሜ_ለእሑድ_አጥቢያ_በኹሉም_ገዳማትና_አድባራት_ይከበራል፤ ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በሐዋርያትና በመንፈስ ቅዱስ ስም በተሰየሙ አብያተ ክርስቲያናት ይከበራል፤ በአዲስ አበባ #በብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ፣(ዊንጌት) #በጽርሐ_ጽዮን_ሐዋርያት_መንፈስ_ቅዱስ_/ኋላ/#ጎላ_ሚካኤል_ (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ) ና በምሁር አክሊል ፤ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ #በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤ.ክ ንም ይከበራል ፡ ተጨማሪ ከታች...... ፠ ጰራቅሊጦስ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፥ መጽንዒ (የሚያጸና)፥ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኀጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጕምን ይሰጣል /መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት፣ ገጽ ፪፻፹፫/፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ በኀጢአት ጭቃ የወደቁትንና የሚወድቁትን እንደሚያነጻቸው፤ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ላሉት ኹሉ በፈተናቸውና በመከራቸው ኹሉ እንደሚያበረታቸው (እንደሚያጸናቸው)፤ የሚነዋወፁትን እንደሚያረጋጋቸው፤ ያዘኑትን እንደሚያጽናናቸው፤ የሚደክሙትን እንደሚያበረታቸው፤ የተከዙትንም ሐሴትን እንደሚሰጣቸው የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ጻድቃንን ወደ ተጋድሎ፤ ሰማዕታትን ወደ ደም፣ መነኰሳትን ወደ ገዳም፣ ማኅበረ ክርስቶስን ምዕመናንንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ልቡናቸውን የሚያነሣሣና የሚመራ እርሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ /ዮሐ.፲፮፥፲፪/፡፡ #በዓለ_ሃምሳ_በብሉይ  በዓሃምሳ በብሉይ እስራኤል ዘሥጋ በዓለ ኃምሳን የሚያከብሩት ስለ ብዙ ምክንያት ነው፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያኽልም፤ ፩ኛ) ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ ምድረ ከነዓን ገብተው ለመዠመርያ ጊዜ እሸት የበሉበትን የሚዘክሩበት ነው፡፡ ዳግመኛም በበረኻ ሳሉ እግዚአብሔር ከሰማያት ኅብስተ መናን አውርዶ፥ ከጭንጫ ውኃን አመንጭቶ እንደመገባቸው ይዘክሩበታል፡፡ በመኾኑም በዚኽ በዓል ቀዳምያት፥ ዐሥራትና በኵራት እያወጡ፣ በየዓመቱ ከሚዘሩት እኽል እሸት (በብዛት ስንዴ) እየበሉ እግዚአብሔርን ስለ ምድር ፍሬ የሚያመሰግኑበት በዓል ነው፡፡ ፪ኛ) እግዚአብሔር ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ በሃምሳኛው ቀን በደብረ ሲና ሕገ ኦሪትን ስለተቀበሉበት ይኽን ያስቡበታል፡፡ ፫ኛ) እግዚአብሔር ከምድረ ግብጽ በታላላቅ ገቢረ ተአምራት ስላወጣቸው ይኽን ያስቡበታል፡፡ ፠ ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው ይኽ በዓል እኽል በሚታጨድበት በመከር ወቅት የሚከበር በዓል ነው፡፡ መከር ሲገባ መጀመርያ ከሚሰበስቡት እኽል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ታዝዘው ነበር /ዘጸ. ፳፫፡፲፮/፡፡ በመኾኑም ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሰባት ሳምንታት (፵፱ ቀናት) በየዕለቱ አንድ መስፈርያ እኽል ይሰጡ ነበር፡፡ በ፶ኛው ቀን ደግሞ ሊቀ ካህኑ ከተሰበሰበው እኽል በትልቅ መስፈርያ አድርጎ ካቀረበ በኋላ መሥዋዕተ በግ ይሠዋ ስለነበር ታላቅ በዓል ኾኖ ይከበር ነበር /ዘሌ. ፳፫፥፲-፲፯፣ ዘዳ. ፲፪፥፭-፯/፡፡ #አማናዊ_ትርጓሜ_በሐዲስ ( አማናዊ ትርጓሜ በሐዲስ) ፠ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ድኅነተ ዓለምን በፈጸመበት ዓመት ግን፥ እስራኤል ዘሥጋ ከላይ በገለጥነው መንገድ ከያሉበት ተሰባስበው በዓሉን በኢየሩሳሌም ሲያከበሩ፤ ለእሥራኤል ዘሥጋና ለእሥራኤል ዘነፍስ ብርሃን እንዲኾኑ የመረጣቸው ሐዋርያትም ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራቸውን ተስፋ እየተጠባበቁ በደብረ ጽዮን በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት ተሰባስበው ነበር /ሉቃ. ፳፬፡፵፱/፡፡ በዓለ ሃምሳ የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜም ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፤ መንፈስ ቅዱስ ነበር፡፡ በዚኽም ብሉይና ሐዲስ ተገናኙ፤ ተተካኩ፡፡ ፠ የነቢያት ትንቢታቸው፥ የሐዋርያትም ስብከታቸው የኾነው ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በደብረ ታቦር ተራራ እንዳገናኛቸው፥ በዚያም ክብረ መንግሥቱን፥ ብርሃነ መለኮቱን እንደገለጸላቸው የሚታወስ ነው /ማቴ. ፲፮፡፩-፯/፡፡ በምሴተ ኀሙስም በቤተ አልዓኣዛር የብሉይ ፋሲካን እንዳዘጋጁና እርሱም መሥዋዕተ ብሉይን በመሥዋዕተ ሐዲስ እንደተካው የተጻፈ ነው /ማቴ. ፳፮፡፲፯-፳፱/፡፡ በበዓለ ኃምሳ የኾነውም ልክ እንደዚኹ ነው /ሐዋ. ፪/፡፡ ይኽ ኹሉ በኢየሩሳሌም፣ በመዠመርያዪቱ ቤተ ክርስቲያን በተሰየመች በቤተ ማርያም (የማርቆስ እናት) ተፈጸመ፡፡  ቤተ ክርስቲያን ለፊተኞችም ለኋለኞችም እናታቸው እንደኾነችም ታወቀ፤ ተረዳ፡፡ ፠ ቅዱሳን ሐዋርያት በዲድስቅልያ ፴፩ ላይ፤ ‹‹ከዕርገቱ ቀን በኋላ ታላቅ በዓል ይደረግ፤ በዚኽች ቀን በሦስተኛው ሰዓት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና እኛም በርሱ ስጦታዎች ተሞላን፤ አዳዲስ ቋንቋም ተናገርን›› በማለት በዓሉን በቤተ ክርስቲያን ልናከብረው እንዲገባ ሥርዐት ሐዋርያት የሠሩልንም ስለዚኹ ነው፡፡ በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት የታነጸችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንም ይኽንኑ በዓል ከጌታችን ዘጠኝ ዐበይት በዓላት አንዱ በማድረግ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ @eotcy #ርደተ_መንፈስ_ቅዱስ ፠ ጌታችን እንደነገራቸው መቶ ሃያው ቤተ ሰብእ በቤተ ማርያም ኀይልን ከአርያም እስኪለብሱ ድረስ ተሰብስበው ነበር፡፡ በትዕግሥት ከመጠበቅ ውጪ መንፈስ ቅዱስ መቼ እንደሚወርድም አያውቁም ነበር /ሐዋ. ፪፥፪/፡፡ ጌታችን ባረገ በዐሥረኛው ቀን ግን እኔና እናንተ እንደምንሰማው ዓይነት ያይደለ፥ ነገር ግን ከወደ ሰማይ እንደ ዓውሎ ነፋስ ድምፅ ያለ ድምፅ ነጕዶ ተሰማ፡፡ ያሉበትን ቤት ሞላው፡፡ ላንቃ ላንቃ ያለው እሳት ኾኖ ታያቸው፡፡ በበደልን ጊዜ ከእኛ ርቆ ነበርና አኹን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ስለታረቅን በኹሉም አደረባቸው:  /ማቴ. ፫፡፲፩/፡፡ ኀይል የሚኾናቸው ሀብትን፣ ሀብት የሚኾናቸው ዕውቀትን ገንዘብ አደረጉ፡፡ @eotcy #መንፈስ_ቅዱስ ፠ መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር የሚሠለስ፥ የሚቀደስ፥ የሚወደስ የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ እንደ አብና ወልድ ፍጹም ገጽ፥ ፍጹም መልክዕ፥ ፍጹም አካል አለው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ እንጂ ሕጹጽ (ብትን፣ ዝርው) አይደለም፡፡ በተለየ አካላዊ ግብሩም መሥረፅ (መውጣት) ነው፤ መሥረጹም ከአብ ብቻ እንጂ አንዳንዶች (ካቶሊኮችና መካነ ኢየሱሶች) እንደሚሉት ከወልድም ጭምር አይደለም /ዮሐ.፲፭፡፳፮/፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢሠርፅ እንጂ አያሠርጽም፥ አይወልድም፥ አይወለድም፡፡ @eotcy በባሕርይ፥ በመለኮት፥ በሥልጣን፥ በሕልውና፥ በአገዛዝ፥ ዓለማትን በመፍጠርና በማሳለፍ ከአብና ከወልድ ጋራ የተካከለ ነው  /ጸሎተ ሃይማኖት/፡፡ ቀዳሚነትም ኾነ ተቀዳሚነት የሌለው ይልቁንም ከአብና ከወልድ ጋር የተካከለ (ዕሩይ) ነው፡፡ ከአብና ከወልድ ጋር ዓለም ሳይፈጠር ፥ ዘመን ሳይቈጠር፥ ይህ ነው በማይበል ዘመን የነበረ ቀዳማዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አሁንም ያለ ማዕከላዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አብ ዓለም ሳይፈጠር ፥ ዘመን ሳይቈጠር ይህ ነው በማይበል ዘመን የነበረ ቀዳማዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አሁንም ያለ ማዕከላዊ፤ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮ ተካክሎ ይህ ነው ለማይባል ዘመን ወደፊት የሚኖር ደኃራዊ ነው፡፡ @eotcy

አሻግረን
ወዳጄ ሆይ ከታገሥህ ሁሉም ያልፋል ፣ በሕይወትህ ከወሰንህ ግን አለማለፍ ዘላለማዊ ይሆናል ። ሞት ወዳንተ መምጣቱ አይቀርምና አንተ ወደ ሞት አትሂድ ። ወደዚህ ዓለም ተመልሰህ አትመጣምና ሕይወትህን ተንከባከባት ። ብረት ብታገላብጥ ፣ ድንጋይ ብታንከባልል የቆምከው ግን በአፍንጫ እስትንፋስ ነውና በማስተዋልና በጥንቃቄ ኑር ። አለመሳካት ማለት አለመኖር ማለት አይደለም ። ራእይ አልባ ሰው ካርታውን የጣለ መንገደኛ ነው ። ውጤቱም ተንከራታች መሆን ነው ። ወዳጄ ሆይ❗ ሰዎች የዘሩትን ሲያጭዱ ስታይ አንተም ዛሬ እየዘራህ ነገ ደግሞ የምታጭድ መሆኑን አስብ ። የዕድሜ ጀምበር የሚጠልቀው አንዱ ባንዱ ሲስቅ ነው ። ዕድልን ዕድል ተሰጥቷቸው ካመለጣቸው ሰዎች ተምረሃት አክብረህ ያዛት ። የወደደም ይጠላል ፣ ያከበረም ያዋርዳል ። ሳትዋዥቅ የምትኖር ግን እውነት ብቻ ናት ። ወዳጄ ሆይ ❗ በየዋህነቴ ተጎዳሁ ብለህ ጨካኝ አትሁን ፣ ነገር ግን ብልህ ሁን ። የደስታ ጊዜ ረጅም ቢሆን አጭር ፣ የመከራ ጊዜ አጭር ቢሆንም ረጅም ነው ። ጓደኛን አለማመን ሁልጊዜ በሥቃይ ውስጥ መኖር ነው ። የምትሠራው የሚጠፋህ ራስህን ማድነቅ ስትጀምር ነው ። መልካም ሰውን በውድ ገዝተን በርካሽ መሸጣችን ትልቁ ኪሣራችን ነው ። ወዳጄ ሆይ ❗ ሰው ስልክ ሲያወራ ሣንቲሜ ቆጠረ እንጂ ዕድሜዬ ቆጠረ አይልምና ከዕድሜው ይልቅ ለሣንቲም ዋጋ እንደ ሰጠ ያሳያል ። በሽተኛ በሌለበት እንፈውሳለን የሚሉ ፣ በሽተኛ ሲመጣ ግን የሚጠፉ ናቸው ። ፈውስ በፕሮግራም ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ። ማስታወቂያ የበዛበት አገልግሎት ከእውነት ይልቅ የዝና ፍቅር ያለበት ነው ። ነቢያት ስላልመጣው ዘመን ያውቁ ነበር ፤ እኛ የምንኖርበት ዘመን ተሰውሮብናል ። ሐዋርያት ሄደው ይሰብኩ ነበር ፣ እኛ ግን መጥታችሁ ተሰበኩ እንላለን ። ሰማዕታት ለክርስቶስ ፍቅር ሞቱ ፣ እኛ ግን ለጥቅማችን እንገድላለን ። ጻድቃን ጣዕመ ዓለምን ንቀው መነኑ ፣ እኛ ግን ዓለም መራራ ሆናብንም ገና እንፈልጋታለን ። ቅዱሳን ከሕግ አልፈው በትሩፋት ኖሩ ፣ እኛ ግን የታዘዝነውን መፈጸም ተስኖናል ። ደናግል መነኮሳት የክርስቶስ ሙሽሮች ሆኑ ፣ እኛ ግን በአሚናችን/በአንድ መጽናት አቅቶናል ። ሊቃውንት አህያ የማትሸከመውን መጽሐፍ በቃላቸው አጠኑ ፣ እኛ ግን በአንድ ጥቅስ ያዙኝ ልቀቁኝ እንላለን ። ጌታ ሆይ ከዘመን ማዕበል እባክህ አሻግረን !
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
https//t.me/eotcy

ምክረ አበው የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።(መጽሐፈ ምክር) "አንደበቱን ከቧልት ያየውን ሚስጥር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኅልዮ ኃጢአት ያርቀዋል። (አረጋዊ መንፈሳዊ) ጸጋ ቢሰጥህ  በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እዳታጣ " (ማር ይስሃቅ) ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው  ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/ ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል❓›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/ ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/ ‹‹በማንም ላይ ክፈትን አትስሩ አትፍረዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/ ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/ ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/ ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ንጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/ ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ ‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ ‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ጸሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትጸልይ እደር።›› /ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/ ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል  ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።››  /ቅዱስ እንጦስ/ "አንደበቱን ከቧልት ያየውን ሚስጥር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኅልዮ ኃጢአት ያርቀዋል። (አረጋዊ መንፈሳዊ) ጸጋ ቢሰጥህ  በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እዳታጣ " (ማር ይስሃቅ) ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው  ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/ ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል።›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/ ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ጸጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/ ‹‹በማንም ላይ ክፋትን አትስሩ አትፍርዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/ ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/ ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/ ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/ ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል  ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።››  /ቅዱስ እንጦስ/ 🟢 @eotcy 🟢 🟡 @eotcy 🟡 🔴 @eotcy 🔴

ምክረ አበው የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።(መጽሐፈ ምክር) "አንደበቱን ከቧልት ያየውን ሚስጥር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኅልዮ ኃጢአት ያርቀዋል። (አረጋዊ መንፈሳዊ) ጸጋ ቢሰጥህ  በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እዳታጣ " (ማር ይስሃቅ) ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው  ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/ ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል❓›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/ ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/ ‹‹በማንም ላይ ክፈትን አትስሩ አትፍረዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/ ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/ ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/ ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ንጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/ ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ ‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ ‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ጸሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትጸልይ እደር።›› /ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/ ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል  ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።››  /ቅዱስ እንጦስ/ "አንደበቱን ከቧልት ያየውን ሚስጥር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኅልዮ ኃጢአት ያርቀዋል። (አረጋዊ መንፈሳዊ) ጸጋ ቢሰጥህ  በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እዳታጣ " (ማር ይስሃቅ) ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው  ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/ ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል።›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/ ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ጸጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/ ‹‹በማንም ላይ ክፋትን አትስሩ አትፍርዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/ ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/ ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/ ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/ ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/ ‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ፀሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትፀልይ እደር።›› /ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/ ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል  ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።››  /ቅዱስ እንጦስ/ 🟢 @eotcy 🟢 🟡 @eotcy 🟡 🔴 @eotcy🔴

ቃለ ሕይወት ያሰማልን ማለት ምን ማለት ነው? ይህ አባባል በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከወንጌል ስብከት፣ ከመዝሙር ከምክር ተግሳጽ በኋላ ምእመናን በአንድነት ላቀረበው አካል ቃለ ሕይወት ያሰማልን፣ መንግስተ ሰማያት ያውርስልን አገልግሎት ዘመንዎትን ያርዝምልን በእድሜ እና በጸጋ ይጠብቅልን ፣ ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን .... ወዘተ እያልን መንፈሳዊ ምርቃን እንመርቃለን! ምን ማለት ነው ቃለ ህይወት ያሰማልን? ቃለ ሕይወትስ ምንድን ነው?? በወንጌል በመዋዕለ ሥጋዌው፣ ለሥም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብትወዱኝ ትዕዛዜን ጠብቁ (ዮሐ.14:15) እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ በእኔ እመኑ በአባቴም እመኑ በሃይማኖት ኑሩ ጎልምሱም.....(1ኛቆሮ 16:13) በሃይማኖት ጤናማ (ቲቶ 1:13-14) ሆናችሁ እኔ የዋህ በልቤም ትሁት እንደሆንኩ በእኔ አምናችሁ ለነፍሳችሁ እረፍት አግኙ (ማቴ.11:29)..... ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ... እስክመጣ ድረስ ትእዛዜን ጠብቁ ያለውን ይዘው በሃይማኖት ኖረው መልካም ተጋድሎን አድርገው  በጌታ ለኖሩ በእሱና በቃሉ ላላፈሩ (ሉቃ.9:26) ንስሀ ገብተው ሥጋውን በልተው ደሙን ጠጥተው ለዘለዓለም ሕይወት ራሳቸውን ላዘጋጁ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ እንዳለ (ዮሐ.15:10) በፍቅሩ ለኖሩ በመጨረሻም ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ ለእያንዳንዳችሁ እንደ ሥራችሁ ለመክፈል (ራዕ.23:32) እስክመጣ ድረስ በፍቅር ኑሩ ያለውን ለፈፀሙ ...በአጠቃላይ በጌታ ለኖሩ ፍሬዎች የሰው ልጅ በክብር በሚመጣበት ጊዜ (ማቴ.25:31) በጎቹን ፍየሎቹን በሚለይበት ጊዜ (ማቴ.25:34) ኑ እናንተ የአባቴ ቡሩካን ኑ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ብሎ ጌታ የሚፈርደው ፍርድ የሕይወት ቃል ይባላል። ሥለዚህ ቃለ ሕይወት ያሰማልን ማለት ይህን የተወደደ ለዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚሰጥ ቃል ያሰማልን፤ በቀኙ ከሚቆሙት ቅዱሳን ይደምርልን እንደማለት ነው፤ ግሩም ምርቃት! አሜን እኛንም የጥምቀት ልጆቹን በመንግሥቱ በመጣ ጊዜ ኑ የአባቴ ብሩካን ከሚላቸው ጋር ይደምረን። https://t.me/eotcy