9 059
Subscribers
No data24 hours
+457 days
-430 days
Posts Archive
9 059
አንዱ ድንግል ሌላዋ ድንግልና ባይኖራት ጋብቻው በምን ይፈጸማል❓
ተክሊልን በተመለከተ ከሚነሱ ጥያቄዎች መካከል ከተጣማሪዎቹ /ከተጋቢዎቹ/ መካከል ሴቷ ወይም ወንዱ ድንግል ባይሆኑ ጋብቻ እንዴት ባለሥርዓት ነው የሚፈጸመው የሚለው አንዱ ነው።
ሥርዓተ ጋብቻ ለመፈጸም ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጡ ሦስት አይነት ጥንዶች አሉ። የመጀመሪያዎቹ ሁለቱም ድንግልና የሌላቸው ሲሆኑ ሁለተኞቹ ደግሞ ሁለቱም ድንግልና ያላቸው ጥንዶች ይሆናሉ። የእነዚህ ከላይ ያነሳናቸው ሁለቱ ተጣማሪዎች የሚያስቸግር ነገር የለውም ድንግልና ለሌላቸውም በቅዱስ ቁርባን ያለ ተክሊል ድንግልና ላላቸውም የተክሊል ሥርዓት ይፈጸምላቸዋል። ለጥያቄ የሚያጋልጠው ከላይ የተነሳው ከሁለት አንዳቸው ድንግልና የሌላቸው ሁነው ወደ ቤተ ክርስቲያን ለሥርዓተ ጋብቻ ሲመጡ ነው።
እዚህ ላይ መረዳት ያለብን አንድ መሠረታዊ ጉዳይ አለ። እርሱም ተጋቢዎች የአንድነታቸው ምስጢር ማኅተሙ ሥጋ ወደሙ እንጂ ተክሊሉ አይደለም። ተክሊሉ አላማው ሽልማትና እውቅና መስጠት ነው። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን እስከ ጋብቻ ድረስ በንጽሕና በድንግልና ለጸኑት ልጆቿ የምትሰጠው የሰማያዊ አክሊል አምሳል የሆነ ሽልማት ነው ተክሊል። አንዳንድ ሰዎች ተክሊል በተጋቢዎች መካከል አንድነት የሚያመጣ እርሱ ነው ብለው ያስባሉ ይህ ግን ስህተት ነው። በተጋቢዎች መካከል የአንድነት ፀጋ የሚያሰጠው ተክሊል ከሆነ ያለ ተክሊል ጋብቻቸውን በመአስባን የሚፈጽሙ ክርስቲያኖች አንድነት ጸጋ አያገኙም እያልን ነው በተጋቢዎች መካከል የአንድነት ጸጋ የሚያሰጠው ሥጋ ወደሙ ነው።
ሰለዚህ ተጋቢዎች መካከል በድንግልና ልዩነት ቢኖር ድንግልና ላለው አካል ተክሊል ሥርዓቱ ይፈጸምለታል። የድንግልና ሽልማቱን ያገኛል። ድንግልና የሌለው አካልም ለደናግላን የሚፈጸመው ሥርዓት አይመለከተውም። ምክንያቱም የወጣትነትን ክፉ ፈተና ተቋቁሞ ድንግልናውን ጠብቆ እስከ ጋብቻ መዝለቅ አልቻለምና ። ተክሊል አይፈጸምለትም /ለሴት ከሆነ አይፈጸምላትም/ ። ተክሊል የሚደረግለት ድንግልናውን ለጠበቀ ድንግልናዋን ለጠበቀች ብቻ ነው። ፍትሃ ነገሥት ላይ ይሄንን በተመለከተ እንዲህ ይላል ፦ " የሚያገቡ ፈቶች ቢሆኑ ተክሊል አያድርጉላቸው። ይህ ተክሊል በጋብቻ ጊዜ ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ይገባቸዋልና። ከሚያገቡት አንዱ ድንግል ቢሆን ብቻውን ይባረክ።" 24:906
ይህ በግልጽ የተቀመጠ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ነው። ነገር ግን ተክሊል የሚፈጽመው አካል ራሱን ዝቅ በማድረግ ያለ ተክሊል ሥርዓተ ጋብቻውን መፈጸም ይችላል። ለምሳሌ ቄስ የዲያቆንን ቦታው ሸፍኖ መቀደስ ይችላል ዲያቆን ግን ቀና ብሎ እንደ ቄስ በመሆን ልቀድ ማለት እንደ ማይችል ሁሉ ድንግልና የሌለው አካል ልመሳሰል ብሎ ተክሊል ልፈጽም ማለት ትዕቢት ነው። ቄሱ የዲያቆንን ቦታው ሸፍኖ መቀደስ እንደሚችል ሁሉ ድንግልና ያለው አካልም ዝቅ ልበል ካለ ያለ ተክሊል መፈጸም ይችላል።
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
9 059
ለ2 ደቂቃ ቦታ ሰጥታችሁ አንብቡት
ከዕለታት አንድ ቀን ምድር የመሬት መንቀጥቀጥ ደረሰባት፤ መንቀጥቀጡ መሬት ላይ ያለውን ሁሉ ማነቃነቁ አይቀርምና ሁሉም ተናወጠ። በወቅቱ ከዛፍ ላይ አንድ የወፍ ጎጆ ነበረች፤
ይህች የወፍ ጎጆ በውስጧ እንቁላሎችን ይዛ ነበር። መሬቱ ሲንቀጠቀጥ ግን እንቁላሎቹን ይዛ ከነበረችው ጎጆ ውስጥ አንዱ እንቁላል ከዶሮዎች መንደር ወደቀ። ዶሮዎቹ እንቁላሉን እንደ እራሳቸው ተንከባክበውና ታቅፈው እንዲፈለፈል አደረጉ። ወፉ እንደ ዶሮ ዶሮዎቹ ጋር ተቀላቅሎ ማደግ ጀመረ። እነሱን መስሎ ዶሮነቱን አምኖ ኑሮውን መግፋቱን ቀጠለ። አንድ ቀን ከዶሮ ቤተሰቦቹ ጋር አንድ ላይ ሆነው በመሬት ሺንሸራሸሩ ወፎች በሰማይ ሲበሩ ተመለከቱ። ይሄኔ ወፉ, እኒህ በሰማይ በነፃነት የሚበሩት ወፎች ምንኛ የታደሉ ናቸው፤ ምናለ እኔም እንደነሱ መብረር ብችል "ሲል እራሱን እየተመለከተ ተናገረ። አብሮ አደጎቹ ዶሮዎች በወፉ ተሳለቁበት "አንተ እኮ ዶሮ ነህ እንደት እንደወፍ ለመብረር ታስባለህ ብለው ሃሳቡን አጣጣሉበት።
ወፉ ምንም እንኳን መብረር የሚችል ወፍ ቢሆንም እንደ ዶሮ ከዶሮ መሃል ስላደገ ዶሮ ነኝ ብሎ አምኗል። ማንነቱን ለውጦ አቅሙን አሳንሶ እራሱን ሳያውቅ ሌሎች ዶሮዎች በነገሩት ብቻ አለመብረሩን አምኖ ኖረ። ክንፎቹን ታቅፎ ሌሎች ወፎች ሲበሩ እየቀና እድሉን እያማረረ ኖሮ ሞተ።
መብረር ተፈጥሮው ሆኖ አልበርም ብሎ በማመኑ ብቻ ወፍ ሆኖ ተወልዶ ዶሮ ሆኖ ምድርን ተሰናበታት። የዚህ ወፍ ታሪክ የሁላችንም ታሪክ ነው። የምንመኘውን ነገር ለማድረግ ሁሉ ተሰጥቶን እያለ ሌሎች አይቻልም ስላሉን ብቻ አንችልም ብለን በማመን የፈለግነውን ኑሮ ሳንኖር እንሞታለን። እንደዛ ምስኪን ወፍ ከሌሎች መሃል ወድቀን ሌሎችን እንሆናለን። ማንነታችን ሌሎች እየነገሩን ራሳታችን ሳናውቅ እድሜያችን ይገፋል። አቅማችንን ሌሎች እየለኩት ችሎታችንን እና ተሰጥዖዋችንን ሳንጠቀምበት ህይወታችን ያልፋል። እስቲ እራሳችሁን ጠይቁት የወደቃችሁት ከማን መካከል ነው❓
ይቻላል ይሳካል ከሚሉት ወይስ አይቻልም አይሳካም ከሚሉት❓ ወፍ መብረር እየቻለ ከዶሮ መሃል ስላደገ እና ዶሮ ነኝ ብሎ ስላሰበ መብረር ምንም እንኳን ቢመኝ ሳይበር ቀረ።
የብዙዎቻችን ሕይወት ከዚህ ብዙም አይለይም። ሁሉ ነገር እያለን ሌሎች ሲሞክሩት ስላላየን ብቻ የማይቻል መስሎን ምኞታችን ምኞት ብቻ ይሆንብናል።
ይህን ነገር አስታውስ በባነነበት ሰዓት የሮጠ ሁሉ አረፈደ አይባልም። ነቅተን ዙሪያችንን እንመልከት፤ የከበቡንን እናስተውል። በዙሪያችን ያሉት አይቻልም ስላሉ ብቻ አይቻልም ብለን እራሳችንን ወደ ኋላ አናስቀረው። ከዶሮ መሃል እንደ ወደቀ ወፍ አትሁን። አቅምህን ተጠቀምበት፤ ፍላጎትህን ኑረው፤ ምኞትህን እውን አድርገው፤ ራስህን መመልከት ከቻልክ አንተ ከምታስበው በላይ ታላቅ ሰው መሆንህን ትደርስበታለህ። ማህበረሰብ ፣ ቤተሰብ ፣ ጓደኛ ባወጣልህ መስፈርት እና መመዘኛ እራስህን አትመዝን፤ ይልቁንም እራስህን በራስህ ፈትነው። ብዙዎች እንደ ወፍ ተወልደው እንደዶሮ ሞተዋል። ያ ክፉ እድልእኛን እንዳይገጥመን ሁላችንም የወደቅንበትን እንመልከት.....ሌሎች መብረር ካልቻሉ አንተ መብረር አትችልም ማለት እኮ አይደለም።
#ኦርቶዶክሳዊ_ትምህርቶች
አስተማሪ ሁኖ ካገኙት Like Share አስተያየትዎ
💚 https://t.me/eotcy 💚
💛 https://t.me/eotcy 💛
❤ https://t.me/eotcy ❤
ወሰብሐት ለእግዚአብሔር!
9 059
፨ በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ መጨረስ ፨
አንብብ ሲጨርሱ፡ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያዳርሱ❗️
ጌታችን በውኃ ላይ እየተራመደ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ተመልክቶ በእምነት " ጌታ ሆይ በውኃ ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ" አለው። ጌታም እምነቱን ተመልክቶ "ና" አለው። ቅዱስ ጴጥሮስ ከታንኳይቱ ወርዶ ወንድሞቹ ሐዋርያት እስኪደነቁ ውኃውን እንደ የብስ በመቁጠር በባህር ላይ እየተራመደ ወደ ጌታ ሄደ።
ልክ ጌታችን ጋር ሊደርስ ሲል የንፋሱ ኃይል ሲያናውጠው ባህሩ የሚያሰጥመው ስለመሰለው እምነቱ ጎደለ። አጠገቡ በባህሩ ላይ የቆመውን ና ያለውን ጌታ ማሰብ ትቶ በሥጋ ፈርቶ "እሰጥም ይሆን" አለ። በባህሩ ላይ ያስኬደው፣ ያቆመው እምነቱ ሲከዳው፣ ባህሩ አሰጠመው። ቅዱስ ጴጥሮስም በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ ጨረሰ።
አንተም በእምነት ጀምረህ እምነትህ ልክ ጌታህ ጋር ሊያደርስ ሲል በሥጋ ፍላጎት መናወጥ ከጀመርክ በኃጢአት ባህር ትሰጥማህ። ብዙዎች መንፈሳዊነትን በጽኑ እምነት ጀምረው፣ ልክ ጌታ ጋር ሊደርሱ ሲሉ፤ የሰይጣን የፈተና ንፋስ እያንገዳገዳቸው፣ ትዕግስት እያሳጣቸው ከመጽናት፤ በኃጢአት ባህር ሰጥመው መዋኘት ይጀምራሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ በእምነት የጀመረውን በሥጋ ቢጨርስም በባህሩ ሰጥሞ እንዳይቀር ጌታውን "ጌታ ሆይ አድነኝ" ብሎ ጮኸ። ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን "አንተ እምነት የጎደለህ፣ስለምን ተጠራጠርህ❓" ብሎ ወቅሶት እጁን፣ ዘርግቶለት ከባህሩ አውጥቶታል።
💚💛❤️
አንተም ምንም በኃጢአት ባሕር ብትሰጥምም፣ እምነት ቢጎድልህም ጌታህን "አድነኝ" ብለህ ብትጮህ ለቅዱስ ጴጥሮስ የተዘረጋ እጁም ላንተ ይዘረጋል፣ ከሰጠምክበትም ያወጣኃል። ብቻ አድነኝ ብለህ ጮህ። ማቴ 14÷25
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
9 059
ወንድም እህቶቼ ዛሬ እስኪ አንድ መንፈሳዊ ስራ እንስራ 🙏
በመጀመሪያ ይህ መንፈሳዊ ቻናል እየጠቀሞት ነው❓
አዎ ከሆነነ መልሱ ወደ ፊትም ብዙ ነገር ይጠብቀናል በእምነት የደከመውን ሰው ማጽናት፣ የተበተነውን መንጋ መሰብሰብ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን ማስፋፋት
ታዲያ እርሶም አላፊነቶን ይወጡ ቢያንስ 1 ሰው ብንጋብዝ እግዚአብሔርን ቃል በዛኑ ልክ እናስፋፋለን ታዲያ ያ ነገር ያቅተናል❓
ስልካችን ላይስ ስንት ዓለማዊ ቻናል አለ ❓ መንፈሳዊስ❓
ወዳጆቼ ከስጦታዎች ሁሉ ስጦታ የእግዚአብሔርን ቃል መጋበዝ ነው እርሶም ይህን ቻናልና ተመሳሳይ የኦርቶዶክስ አስተምህሮ የያዙትን ቻናሎችን ይቀላቀሉ🙏
ብዙ ስራ ይጠብቀናል
ቻናሉን ለመቀላቀል
☞︎︎︎ https://t.me/eotcy
☞︎︎︎ https://t.me/eotcy
☞︎︎︎ https://t.me/eotcy
9 059
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክትቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር:: ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ:: ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው:: አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው:: ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ:: እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው:: ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት:: የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ:: "ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ:: "እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ: እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል:: በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ:: ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል:: ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና ማለት ግብጽ ውስጥ የምትገኝ የቀድሞ አውራጃ ናት:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በከተማዋ በርካታ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የእንዴናው መኮንን መጥቶ "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" አላቸው:: ሕዝቡ በአንድ ድምጽ መለሱ:- "ይሕማ ፈጽሞ ሊደረግ አይችልም::" መኮንኑ ተቆጥቶ "ሁሉንም ግደሉ" አለ። ወታደሮቹ ሰው አልመረጡም። ከታዘለ ሕፃን አልጋ ላይ እስካለ ሽማግሌ: ከጤነኛ እስከ ሕመምተኛ: ሁሉንም ጨፈጨፏቸው። ከተማዋ በደም ተነከረች። ከከተማዋ ክርስቲያኖች ወሬ ለመንገር አንድ ሰው እንኳ አልተረፈም። ሁሉም ስለ ክርስትና ደማቸውን አፈሰሱ። ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ቅዱሱ ከአሕዛብ ወላጆቹ ተወልዶ: ያደገውም በጣዖት አምልኮ ነው:: በሙያው እጅግ የተመሠከረለት ሐኪም ነበር:: የሃገሩ ሰዎች "ጠቢብ" እያሉም ይጠሩታል:: በጥላን ምንም ጣዖት አምላኪ ቢሆን በተፈጥሮው ተመራማሪና ቅን ነበር:: አንድ ካህንም በጐረቤቱ ነበርና ዘወትር ስለ ሃይማኖት ይከራከሩ ነበር:: ካህኑ ሌሊት ሌሊት ስለ በጥላን ተግቶ ይጸልይ ነበርና ተሳክቶለት አሳመነው:: አንድ ቀን በጥላን መንገድ ሲሔድ እባብ ሰው ነድፎ ለሞት ደርሶ አየውና ጸሎት አድርሶ ስመ ክርስቶስን ቢጠራ የተነደፈው ድኖ እባቡ ሞተ:: በዚህ ተዓምር ደስ ብሎት ወደ ካህኑ ሒዶ ተጠመቀ:: ከዚያም ጾም ጸሎትን ጀመረ:: በየቦታው እየዞረ ሕሙማንን እንደ ቀድሞው በመድኃኒት ሳይሆን በጸሎት ያድናቸው ነበር:: ስላዳናቸውም በርካቶቹ ወደ ክርስትና መጡ:: የአካባቢው ሰው: ወላጆቹን ጨምሮ ክርስቲያኖች ሆኑ:: በመጨረሻም ቅዱስ በጥላን: ቤተሰቦቹ: ካህኑና ከደዌ የዳኑት ወገኖቹ በአካባቢው ጣዖት አምላኪ ንጉሥ ፊት ቀርበው ክርስቶስን ሰብከው በሰማዕትነት ዐርፈዋል። ጌታችን ስለ ሰማዕታቱ ብሎ: ደማቸውንም አስቦ በሃይማኖታችን ያጽናን:: ከመከራም ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያድለን
ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት 2.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ 3.አቡነ ስነ ኢየሱስ 4.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለምሐምሌ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ቂርቆስ ወእሙ ኢየሉጣ 3.ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ሰማዕት እና ማኅበሩ 4.ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና ወስብሐት ለእግዚአብሔር @eotcy @eotcy
9 059
ወዳጄ ሆይየትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን❓ እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን❓ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን❓ እንኪያስ ወደ ሰማያዊው መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን❓ እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን መንፈሳዊ መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ ቆሽሸሃልን❓ እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡” ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
9 059
"አንድ ሰው ቤተ ክርስቲያን ከኖኅ መርከብ ትበልጣለች ቢል አልተሳሳተም፡፡ የኖኅ መርከብ እንስሳትን ወደ ውስጥዋ ብታስገባም እንስሳት አድርጋ ጠበቀቻቸው እንጂ አልለወጠቻቸውም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን እንስሳትን ትቀበላለች፤ ትለውጣቸውማለች፡፡ ለምሳሌ ወደ ኖኅ መርከብ ቁራ ገባ፤ የወጣውም ግን ቁራ ኾኖ ነው፡፡ ተኵላ ገባ፤ የወጣውም ግን ያው ተኵላ ኾኖ ነው፡፡ እዚህ ቤተ ክርስቲያን ግን አንድ ሰው እንደ ቁራ ኾኖ ቢገባ የሚወጣው እንደ ርግብ ኾኖ ነው፡፡ ተኵላ ኾኖ ቢገባ የሚወጣው እንደ በግ ኾኖ ነው፡፡ እንደ እባብ ኾኖ ቢመጣ የሚወጣው እንደ ጠቦት በግ ኾኖ ነው፡፡ ተፈጥሮው ወደዚያ ስለሚለወጥ ግን አይደለም፤ ክፋቱ ስለሚርቅለት እንጂ፡፡ ስለ ንስሓ አብዝቼ የማስተምረውም ከዚህ የተነሣ ነው፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ንስሐና ምጽዋት)
✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟
"ኃጢአት ሠርተሃልን? ወደ ቤተ ክርስቲያን ግባ ኃጢአትህንም አርቃት፡፡ በአደባባይ የምትወድቀው ቊጥሩ ከምትነሣው ጋር እኩል ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ በደል ኃጢአት የምትሠራውን ያህልም ፍጹም ተስፋ ሳትቈርጥ ንስሐ ግባ፡፡ ኹለተኛ ብትበድል ኹለተኛ ንስሐ ግባ፡፡ በስንፍና ተይዘህ በፍጹም ምግባር ትሩፋት መሥራት አይቻለኝም አትበል፡፡ በእርግና ዘመን ብትኾንና ብትበድልም እንኳን ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተህ ንስሐ ግባ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሆስፒታል እንጂ ፍርድ ቤት አይደለችምና፡፡ እዚህ ስትመጣ ካህናት [“እግዚአብሔር ይፍታሕ” ብለው] ከኃጢአት እስራት ፈትተው ይቅርታ ይሰጡሃል እንጂ “ለምን በደልህ?” ብለው አይፈርዱብህምና፡፡ ስለዚህ፡- “አንተን ብቻ በደልሁ፤ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ” ብለህ ለእግዚአብሔር ንገረው፤ ኃጢአትህም ይቀርልሃል (መዝ.50፡4)፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2♡ ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ✉️ ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
9 059
. መስቀል ለምን እንሳለማለን❓
መስቀል ስንሳለም ምዕመኑ ይፍቱኝ ይባርኩኝ ብለን በፍጹም ትህትና በእምነት ሆኖ ወደ ካህኑ እንቀርባለን ካህኑም በመስቀሉ የላይኛው ክፍልና በታችኛው ክፍል ግንባራችንና አፋችንን አሳልመው ይባርኩናል።
@eotcy
ግንባሩን ማስነካታቸው በአዕምሮ የተሰራውን ከንፈሩን ማስነካታቸው በመናገር የተሰራውን ኃጥያት እግዚአብሔር ይተውላችሁ ማለታቸው ነው።ቀዳሲያኑ ለቅዳሴ መምህሩ ለማስተማር ዘማሪው ለመዘመር ሲነሱ በማዕረግ ከፍ ካሉት ካህን መስቀል የሚሳለሙት።
ኃጢያት በሶስት መንገድ ይሰራል
፩. በገቢር (በመስራት)
፪.በነቢር (በመናገር)
፫.በኅልዩ (በማሰብ)
@eotcy
ታዲያ በገቢር በመስራት የተፈጸመውን ኃጢአት ለማስተሰረይ ጊዜ ሰጥቶ ወደ ንስሐ አባት ቀርቦ በኑዛዜ ቀኖና መቀበልና ቀኖናውን መፈፀም ይገባል። ለዚህ ነው አሁን አሁን በከተሜው ዘንድ እምብዛም ባይታይም ወንጌሉ የገባቸው ክርስቲያኖች ካህን ባዩ ቁጥር መስቀል ለመሳለም የሚጓጉት። ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ማድረጋችሁን አትዘንጉ
እያወቅን በድፍረት ሳናውቅ በስሕተት የሰራነውን ኃጢአት ይቅር ይበለን
@eotcy
9 059
💠 የክርስትና ስም ለምን ያስፈልጋል ?
ጥቂት የማንባል ሰዎች ከነ መሰየሙም የክርስትና ስማችንንም የማናስታውስ ልንኖር እንችላለን፡፡ የክርስትና ስም አንድ የሚጠመቅ
ሰው በሚያጠምቀው ካህን የሚሰጠው ወይም የሚጸድቅለት ስያሜ ነው፡፡ ይህንን ስም ቤ/ክ ዝም ብላ ለህጻናቱ የምትለጥፍ የሚመስላቸው ሰዎች ቀላል አይደሉም፡፡ በጥምቀት ግዜ ቤ/ክን ልጆቿን ስትቀበል እንዲሁ አይደለም ተገቢ ስም አውጥታ ከመንፈስ ቅዱስ በጥምቀት
ዳግመኛ ወልዳ ቅበዐ ሜሮን ቀብታ የሚንከባከብ የክርስትና አባት እናት ሰይማ በመስቀሉ ቃል አስገብታ ቅዱስ ስጋና ደሙን መግባ ነው፡፡ የክርስትና ስም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና ክርስቲያናዊ ትውፊት አለው፡፡ ብዙ ነብያት እና ቅዱሳን ካላቸው መጠሪያ ሰም በተጨማሪ እራሱ አምላካችን አዳዲስ ስም ሲያወጣላቸው እናያለን
ለምሳሌ፡-
አብራምን 👉 አብርሃም
ያይቆብን 👉 እስራኤል
ስምዖንንን 👉 ጴጥሮስ
ሳኦልን 👉 ጳውሎስ እያለ ሲጠራቸው
ለምን በአዲስ ስም መጥራት እንደፈለገ አንዳች ነገር ልንገነዘብ ይገባል፡፡
✝ ...ዓላማውስ ምንድን ነው?
#1ኛ .ቋሚ የቅዱሳን መታሰቢያ እንዲሆን፡- በት.ኢሳ 56:5 አምላክ ለቅዱሳን የማይጠፋ ስም እና የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሰጣቸው እናነባለን፡፡ስለዚህ በተለያዩ ቅዱሳን ላይ የነበረውን ፀጋ እና በረከት ለመካፈልና እንዲሁም እንደነሱ የበረታን እንድንሆን በስማቸው እንሰየማለን የጌታችንንም ስሙን ዘርፍ በማድረግ እንዲሁ እንጠቀምበታለን፡፡
#2ኛ .ለተጠማቂውም በረከት እንዲሆንለት፡- በምሳ 10:6 የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ይላል፡፡ ስለዚህ በስማቸው በመሰየም ከላይ እንደገለጽነው መታሰቢያቸውን እና በረከታቸውን ለመካፈል ሲረዳን ይህን ጸጋ ለማግኘት በቅዱሳን ስም በመሰየም የክርስትና ስም ይወጣልናል፡፡
#3ኛ .መጠሪያ ስም ነው፡-ላለመሰደድ
በቀድሞው ስርአት የክርስትና ስም ለሁልጊዜውም መጠሪያ ነበር፡፡ ከግራኝ መሐመድ መነሳት አስቀድሞ የነበሩ ምዕመናን በክርስትና ስማቸው ነበር የሚጠሩት፡፡ ነገር ግን
መከራው ሲበዛባቸው ከርስታቸው ሲሉ ተለዋጭ ስም በማውጣት መጠቀም ጀመሩ ከዛን ግዜ ጀምሮ ይህ ነገር እየተስፋፋ መጥቶ ከነ ጭራሹ ለመለወጥ በቃ፡፡
🛑 የማይገባ የክርስትና ስም
በአምላክ ስም በቀጥታ መጠራት አይገባም አማኑኤል፣ ኤልሻዳይ፣ ኢየሱስ እነዚህ ስሞች ለሠው ልጆች መጠናችን ስላልሆኑ መጠቀም የለብንም፡፡ በዚህ ምትክ ገብረ አምላክ፣ሣህለ ሥላሴ፣ ፍቅርተ ክርስቶስ፣ ዘአማኑኤል በማለት መሰየም ይቻላል፡፡
💠 በቅዱሳንም ስም በቀጥታም ሆነ ዘርፍ እየተደረለት መሰየም ይቻላል፡፡ ለምሳሌ፡- ዘማርያም፣ ዘሚካኤል፣ አጸደ ማርያም፣ ተክለ
ሐይማኖት ወዘተ... ስለዚህ ስርአቱን በመጠቀም ከሚገኘው በረከት ተሳታፊዎች እንድንሆን አምላክ ይርዳን፡፡
#ተንሥዑ_ለጸሎት
💚💚💚💚💚💚💚
💚💚💚💚💚💚💚
💛💛 @eotcy 💛💛
💛💛 @eotcy 💛💛
💛💛 @eotcy 💛💛
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
9 059
የቱን እንምረጥ ❓ዕለተ ሰንበትን የት ነው ምታሳልፋት❓ በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ወይስ ቅዳሴ በማስቀደስ❓ አመሻሻቹስ❓ ኳስ ጨዋታን በማየት ወይስ በሰርክ ጉባኤ ወንጌል በመማርን❓ የኳስ ጨዋታ ለማየት የሚሰለፈው ወጣት ቅዳሴ ላይ የለም ለትያትር የሚሰለፈው ወጣት ወንጌል ላይ የታለ❓ ለኮንሰርት የሚሰለፈው ወጣት መዝሙር ላይ የታለ❓ ወጣቶች ሆይ ምርጫችን የዘላለሙን ይሁን🙏 እንደ ማርያም ወንጌል እንማር መልካም እድል ነውና🙏 ቅዳሴ እናስቀድስ ከመላእክት ጋር አንድ እንሆናለንና🙏 ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቅርብ የተፈጠርንበት አላማ ነውና🙏 ከመቅደሱ አንለይ እንቀደሳለንና ኳሱ ለጊዜው ነው አንተ የምትደግፈው ክለብ ቢያሸንፍ ከጊዜያዊ ደስታ ያለፈ ነገር የለውም ሙዚቃው የኀጢአት በር መክፈቻ ነው❗ መጽሐፍ ቅዱስ ዘፋኝ መንግስተ ሰማያትን አይወርስም ይላልና❗ከዘፈኑ መንግስተ ሰማያት አይሻልህም❓ ትያትሩ አስመሳይነት ነው ወጣቶች ሆይ ምርጫችሁን አስተካክሉ ከዘፈን ይልቅ መዝሙርን ከኳስ ጨዋታ ይልቅ ቅዳሴን ከትያትር ይልቅ ወንጌል መማርን ምረጡ እግዚአብሔር ለትውልዱ አስተዋይ ልቡና ይስጠን🙏
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
9 059
ለልጆች ስም ለማውጣት ተቸግረዋል❓
እነሆ የመጽሐፍ ቅዱስ ስሞች
ሼር! ሼር! ሼር!
@eotcy
1 ባሮክ ፡ ብሩክ
2 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ
3 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
4 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ቶሎ ና
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት ማለት
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል
9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ ውሃ
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር
17 ዲና፦ እግዚአብሔር ፈረደ
18 ማኑሄ፦እረፍት
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ፦ከፍታ
21ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ
22 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ ምርጥ
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ
25 ቶማስ፦ፀሐይ
26 ታዴዎስ፦እሸቱ (ግብራዊ ትርጓሜ)
27 ማትያስ፦ፀሐይ ወይም ምትክ
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ
29 አቤል፦ የዋህ ፣ እርግብ
30 ኖኅ፦ደስታ
31 ሴም፦ ተሾመ
32 ይሥሐቅ፦ ደስታ አንድም ይሳቅ
33 ሙሴ፦ የውሃ ልጅ (ከውሃ የተገኘ)
34 አሮን፦ የእግዚአብሔር ተራራ
35 ጌዴዎን፦ እግዚአብሔር ኃያል
36 እሴይ፦ ዋጋየ ማለት ነው።
37 አሚናዳብ፦ መንፈስቅዱስ ማለት ነው።
38 ዳዊት፦ የተወደደ ልበ አምላክ ማለት ነው፣
39 ዕንባቆም፦ ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ
40 ሄኤሜን፦ ምኞቴን አገኘሁ
41 አሞጽ፦ እግዚአብሔር ጽኑ ነው
42 ዮናስ፦ርግብ
43 ሐጌ፦ የእግዚአብሔር መልእክተኛ
44 ራኄል፦ በግዕት
45 ዕዝራ፦ ረዳቴ
46 ሔርሜላ፦ ከክብር ዘመድ የተገኘች
47 መርቆሬዎስ፦ የአባት ወዳጅ
48 ኤጲፋንዮስ፦ ምስጢር ገላጭ
49 ሜሮን፦ የተባረከ ሽቱ
50 ሱላማጢስ፦ ሰላማዊት
@eotcy
51 ሶምሶን፦ ፀሐይ
52 ብንያም፦ የቀኝ እጄ ልጅ
53 ማርታ፦ እመቤት
54 ሊዲያ፦ ፈራሂተ እግዚአብሔር
55 ኤፍሬም፦ ፍሬያማ ፍሬው
56 ኤፍራታ፦ ክብርት የተከበረች
57 ታዴዎስ፦ ተወዳጅ ወይም ፍቁር(ቃላዊ ትርጓሜው)
58 ኢየሩሳሌም፦ የሰላም ሀገር
59 ሄኖስ፦ ሰው
60 ሰሎሜ፦ ሰላም
61 በንያስ:- እግዚአብሔር አዳነኝ
62 ቤንኦኒ:- የጭንቅ ጊዜዬ ልጅ
63 ጴጥሮስ:- አለት
64 ጳውሎስ:- ምርጥ እቃ
65 ሆሴዕ:- እግዚአብሔር ያድናል
66 ሐና :- ጸጋ፣ ስጦታ
67 ሔዋን:- የብዙሐን እናት
68 ሕዝቅኤል:- እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል
69 ሕዝቂያስ:- እግዚአብሔር ኃይል ነው
70 መልከ ጼዲቅ:- የጽድቅ ንጉሥ
71 ሚልኪያስ :- መልክተኛዬ
72 ሚኪያስ :- እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው
73 "ምናሴ:- ማስረሻ
74 ሣራ :- ልዕልት
75 ሩሐማ :- ምሕረት
76 ሮቤል :- እነሆ ወንድ ልጅ
77 ሰሎሞን :- ሰላማዊ
78 ሳሙኤል :- እግዚአብሔር ሰማኝ
79 ኢየሱስ ፦ አዳኝ (መድኀኒት )
80 ሶፎንያስ ፦ እግዚአብሔር ሰውሯል
81 ኢዮኤል፦ እግዚአብሔር አምላክ ነው
82 ቃዴስ ፦ ቅዱስ
83 በርተሚዮስ ፦ የተለሜዎስ ልጅ
84 ቤተልሔም ፦ የእንጀራ ቤት
85 ቶማስ ፦ መንታ
86 ናሆም መጽናኛ
87 ናታን :- እግዚአብሔር ሰጥቷል
88 አልአዛር ፦ እግዚአብሔር ረድቷል
89 አማኑኤል ፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ( ይሔስም ላይ ከፊት"ዘ" ወይም"የ" ጨምረን ብንጠቀም)
90 አርኤል ፦ የእግዚአብሔር ምድጃ
91 አሴር ፦ደስተኛ
92 አስቴር ፦ ኮከብ
93 አቡ ፦ አባት
94 አብዱዩ ፦ የእግዚአብሔር አገልጋይ
95 አኪያ፦ እግዚአብሔር ወንድሜ ነው
96 ኢሳያስ ፦ እግዚአብሔር ደህንነት ነው
97 ኢያሱ ፦ እግዚአብሔር አዳኝ ነው(መድኀኒት) ማለት ነው።
98 ኢይዝራኤል ፦ እግዚአብሔር የዘራት
99 ኢዮሳፍጥ፦ እግዚአብሔር ፈርዷል
100 ኢዮራም ፦ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ
@eotcy
101 ኤልሳዕ ፦ እግዚአብሔር ደህንነት ነው
102 ኢዮስያስ ፦ እግዚአብሔር ይደግፋል
103 ኢዮአታም፦ እግዚአብሔር ፍጹም ነው
104 ኢያቄም፦ እግዚአብሔር አቆመ
105 ኢዮአብ፦ እግዚአብሔር አባቴ ነው
106 ኢዮአታም፦ እግዚአብሔር ፍጹም ነው
104 ኢዮአካዝ፦ እግዚአብሔር ይዟል
105 ኤልዔዘር ፦ እግዚአብሔር ረዳት ነው
106 ኤልያስ፦ እግዚአብሔር አምላክ ነው
107 እስማኤል፦ እግዚአብሔር ይሰማል
108 ኬልቅያስ፦ እድል ፈንታ እግዚአብሔር ነው
109 ኤደን፦ ደስታ
110 ኬብሮን ፦ ህብረት
111 ዘካሪያስ፦ እግዚአብሔር ያስታውቃል
112 ኢሳኮር ፦ ዋጋዬ
113 ይዲዲያ ፦ በእግዚአብሔር የተወደደ
114 ዮሐናን፦ እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ
115 ዮናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል
116 ዮሐኬን፦ እግዚአብሔር ያቆማል
117 ዮካብድ፦ እግዚአብሔር ክብር ነው
118 ዮዳሔ፦ እግዚአብሔር ያውቃል
119 ዮፍታሔ ፦እግዚአብሔር ይከፍታል
120 ጎዶልያስ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው
121 ማሪያ ፦ ቆንጆ ማለት ነው
122 ዳራ :- በጥበብ የተሞላች ሴት
123 ኢዛኤል፦ የጌታ ተስፋ
124 አቤል ፦ የዋህ ማለት ነው
125 አቢጊያ ፦ አባቴ ደስተኛ ነው
126 ናታኔም ፦ የእግዚአብሔር አገልጋይ
126 ጌርሳም፦ ከሌላ ምድር ደስተኛ ነኝ
127 ዳንኤል፦ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
128 ዮሐንስ ፦ እግዚአብሔር ጸጋ ነው
129 አሞን፦ የወገኔ ልጅ
130 እስራኤል፦ የእግዚአብሔር ሀገር
131 ኢዮአም :- አዳኝ
132 ኤልሳቤት :- እግዚአብሔር መሐላዪ ነው
133 አብርሐም ፦ የብዙሐን አባት
134 አዶኒያስ ፦ እግዚአብሔር ጌታዬ ነው
135 አዶኒራም፦ ጌታዬ ከፍ ያለ ነው
136 ሴት ፦ ምትክ
137 ማቴዎስ :- ሞገስ
138 ፌቨን :- የእግዚአብሔር አገልጋይ
139 ወንጌል ፦ የምስራች፣ አዲስ
140 ኢዩኤል ፦ እግዚአብሔር አምላክ ነው
141 ሶፈኒያስ ፦ እግዚአብሔር ጠብቋል (ሰውሯል)
142 አዛርያስ፦ እግዚአብሔር ረድቷል
143 አቤኔዘር ፦ ማመስገኛዬ
145 ስምዖን ፦ እግዚአብሔር ሰማኝ
146 ሚካኤል ፦ ማን እንደ እግዚአብሔር( ይሔስም ላይ ከፊት"ዘ" ወይም"የ" ጨምረን ብንጠቀም)
147 ገብርኤል፦ የእግዚአብሔር አገልጋይ ( ይሔስም ላይ ከፊት"ዘ" ወይም"የ" ጨምረን ብንጠቀም)
148 መክብብ ፦ ሰባኪ
149 ኢሳያስ፦ መድኃኒት ቀቡህ (የተቀባ)
150 ዮሴፍ :- ይጨምር
@eotcy
151ቴዎፍሎስ፦ የእግዚአብሔር ወዳጅ
152 ኑኃሚን፦ ደስታዬ
153 ናትናኤል ፦ የእግዚአብሔር ስጦታ
154 አዛኤል፦ እግዚአብሔር ያያል
155 በርናባስ፦ የመጽናናት ልጅ
156 አቤሜሎክ፦ የንጉስ አገልጋይ
157 አቤሴሎም፦ አባቴ ሠላም ነው
158 አብራም፦ ታላቅ አባት
159 አክዓብብ፦ የአባት ወንድም
160 አዳም፦ መልካም
161ኢይርብርዓም፦ የእግዚአብሔር ህዝብ እየበዛ ሔደ
162 ኤዶም፦ ቀይ
163 ዖዝያን፦ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
164 ዮፍታሔ፦ እግዚአብሔር ይከፍታል
165 ዲቦራ፦ ንብ
166 ዳንኤል፦ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
167 ጽዮን፦ አንባ፤ መጠጊያ
167 እመቤት፦ የቤት እናት
168 ሔኖክ፦ አዲስ ሆነ፤ ታደሰ
169 ሔራኒ፦ ሰላም ፍቅር
170 ማራናታ፦ ጌታ ሆይ ቶሎ ና
#ማስታወሻ፦ ከላይ ከጻፍኳቸው ውስጥ አንዳንድ ስሞች ከ81ዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኙ ከሌሎች የታሪክ እና የገድል መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ስሞች መሆናቸውን ማሳወቅ እፈልጋለሁ።
#ሼር
https://t.me/eotcy
9 059
አባቶች ስለ እመቤታችን ካስተማሯቸው ❗❗
"ሴጣን በአንዳንዶች መስቀሉን ይክዱ ዘንድ በእነርሱ ዘንድ ስራውን ይሰራል የጌታችንን ሕማማቱን እና ሞቱን እንዲያፍሩበት እና ምትሐት ነው እንዲሉ በውስጣቸው ይሰራባቸዋል፣ ከድንግል መወለዱን እና ስጋ መልበሱን ፣ እንዲሁ ም የእኛን ባሕርይ እርኩስ እንደሆነ አድርጎ ይነቅፍል። ከአይሁድ ጋር ደግሞ ሰዎች መስቀሉን እንዲክዱ ቤተ ክርስቲያንን ይዋጋታል፣ ከአሕዛብ ጋር ደግሞ ድንግል ማርያምን ይነቅፍሉ ፣ ክርስቶስ ከእርሷ ባሕርይዋን ገንዘብ አድርጎ እንዳልተወለደ አድርገው ይናገራሉ ። የክፍት ሁሉ መሪ ፊት አውራሪ የሆነው ዲያብሎስ አሰራሩ ብዙ አይነት ነውና ። እርሱ የሰዎች ፈታኝ እና አታላይ እንደ መሆኑ ሰዎችን በተለያየ መንገዶች ከእውነት ይለያቸው ዘንድ ይፈትናቸዋል ። (ቅዱስ አግናጥዮስ ፣ መልእክት ኅበ ፈልጵስዮስ ፣ ምዕ.4)
"የሁላችን መሰረት አዳም የተገኘው ካልታረሰችና ድንግል መሬት እንደ ነበር ( እግዚአብሔር አምላክ በምድር ላይ አላዘነበም ነበርና፣ ምድርንም የሚሰራበት ሰው አልነበረም ፣ ዘፍ 2፥5) እንዲሁም በእግዚአብሔር እጅ ፣ ማለትም በእግዚአብሔር ቃል የተፈጠረ እንደ ነበር ሁሉ ፣ ሁሉ የሆነው በእርሱ ነውና ፤ እግዚአብሔር ከምድር አፈር ወስዶ እንዳበጀው ሁሉ ፣ ያው የእግዚአብሔር ቃል ዳግማዊ አዳም ሆኖ ሲወለድም ድንግል ከሆነች ከቅድስት ማርያም ተወለደ ። ( ቅዱስ ሄሬኔዎስ ፣ በእንተ መናፍቃን መጽሐፈ 3፣ ምዕ ፣ ቁ. 10)
👇👇 👇👇
https://t.me/eotcy
https://t.me/eotcy
9 059
ልባችን ወዴት ይሆን❓አንድ ሰው በጣም የሚወደው ልጅ ነበረው። ለዚህ ልጁ ሕይወትን ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብሮ እንዴት መኖር እንደሚችል ሊያስተምረው ይጥር ነበር። ነገር ግን ብዙም የተሳካለት አልመሰለኝም። ልጁ በፊቱ የመጣለትን ነገር በማድረግ የሚነዳና ምንም አይነት መንፈሳዊነትና ጥበብ የሞላው ሕይወት እንዳላዳበረ ገባው። በአካባቢው በጥበቡ የታወቀ አንድ አባት ነበረና የሕይወትን ጥበብ እንዲማር ወደዚያ ጠቢብ አባት ላከው። ልጁ ወደ ጠቢቡ አባት በመሄድ እንዲህ አለው፣ ሕይወቴን መንፈሳዊነትና ጥበብ በተሞላው ሁኔታ እንዴት መምራት እንዳለብኝ ለመማር ነው የመጣሁት። ጠቢቡ አሁን ትንሽ ስራ አለብኝ ፣ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ቆይተህ ተመለስ። እስከዚያው ግን አንድን ነገር እንድታደርግ ስራ ልስጥህ በማለት ፣ በእጁ አንድን የሻይ ማንኪያ ሰጠውና በማንኪያው ላይ ዘይትን ሞላበት። ከዚያም እንዲህ አለው በቤተክርስቲያን ውስጥ እየተዘዋወርክ ያሉትን ድንቅ ቅርሶች በመመልከት ሁለት መጠበቅ ያለብህን ሰዓታት አሳልፍ። አንድ ነገር ግን ተጠንቀቅ በፍፁም ይህ በማንኪያ ላይ ያለው ዘይት መፍሰስ የለበትም። ልጁ አደራውን ተቀብሎ ስንት ሰዓት እንደሆነ ከቃኘ በኋላ ቤተክርስቲያኑን ለመጎብኘት በእጁ ዘይት የሞላበትን ማንኪያ ይዞ በቀስታ በመራመድ ወጣ። ልጁ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ወደ ጠቢቡ አባት ተመለሰ። ጠቢቡ ካስገባው በኋላ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ በግርግዳው ላይ የተሰቀለውን የጥንት ስእል አየኸው❓ የታወቁ የገዳም አባቶች አስር ዓመት የፈጀባቸው የአትክልት ስፍራስ አየኸው❓ የአለምን እውቀት በሙሉ የያዘውንስ የመጽሐፍ ቤት አየኸው❓ ልጁ አፍሮ አንገቱን አቀረቀረ። ለካስ ለሁለት ሰዓታት ሲዘዋወር ትኩረቱ ሁሉ በእጁ የያዘው ማንኪያ ላይ የተቀመጠው ዘይት እንዳይፈስ ነበር። ጠቢቡ ሊያስተምረው የፈለገው ነገር እንደተሳካለት ገባውና እንደገና በማንኪያ ያለውን ዘይት ይዘህ ሂድና እነዚህ የነገርኩህንና ሌሎችም አስገራሚ ቅርሶች እንደገና ተመልክተህ ተመለስ አለው ሁለተኛ እድል ስላገኘ ትንሽ ተንፈስ ያለው ወጣት ተመልሶ ወጣ። ለሁለት ሰዓታት ጉብኝቱን ካጧጧፈ በኋላ በፈገግታ ተመለሰ ያየውን ሁሉ ለጠቢቡ ነገረው። እስኪጨርስ ጠብቆ ጠቢቡ እንዳይፈስ ያልኩህ ዘይት የት አለ❓ አለው። ልጁ ጎንበስ ብሎ በእጁ የያዘውን ማንኪያ ሲያየው ለካ ዙሪያውን በመመልከት ሲደነቅ ዘይቱን ችላ ስላለው ዘይቱ ሙልጪ ብሎ ፈሷል። ጠቢቡ አባትም እንዲህ አለው፣ ስኬታማ ሕይወት ማለት እምነትና ምግባት የተሞላውን ሕይወት መኖር ማለት ነው። እምነትና ጥበብ የተሞላው ሕይወት ማለት ዙሪያህን እያየህ በማድነቅ ስትኖር በእጅህ ላይ ያለውን አደራ አለ መዘንጋት ነው። በሕይወታችን ልክ እንደ ዘይቱ በጥንቃቄ መያዝ ያለብን አደራዎች አሉን። ከዚያው ጋር ደግሞ ልክ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ እንዳሉት አስደሳች ጥንታዊ ቦታዎች የመደሰትን እድል የሚሰጡን ሁኔታዎች አሉ። እውነተኛ ሰው እነዚህን ሁለቱን በሚዛናዊነት የያዘ ሰው ነው። ስንጫዎት ፣ስንዝናና ፣ ስንዴሰትና በማሕበራዊ ግንኙነታችን ውስጥ ያለውን ደስ የሚያሰኝ ሁኔታ ስንፈነድቅበት ፣ ከዚያ የተነሳ በእጃችን ላይ ያለውን አደራ ችላ እንዳይባልና ዘይቱ እንዳይፈስ መጠንቀቅ የጥበብ ሁሉ ጥበብ ነው። ልክ ይህ ወጣት በእጁ ያለውን ዘይት ዙሪያው ካለው ታላላቅ ነገርን የማየት እድል ጋር አስታርቆና ሚዛናዊ አድርጎ መውጣትና መግባት እንደነበረበት እኛም እንዲሁ❗️ በዙሪያችን ካለው ጨዋታና መዝናናት ብዛት የተነሳ የተለመዱ ችላ በማለት ማፍሰስ የማይገቡን የአደራ ዘይቶች" ልባችን ወዴት ይሆን❓ "ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር በማሰሮአቸው ዘይት ያዙ" (የማቴዎስ ወንጌል 25:4) የቅዱሳን አምላክ ሙሽራው ሲመጣ ዘይትን በማዘሮአቸው ከያዙት ከተመረጡት ጋር ያድርገን
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
9 059
✨✨✨✨✨✨
ስንት ኦርቶዶክሳዊ ተረፈልን . . .❓
📌 ይነበብ
☞ማዕተብ ካሠረው 50-60? ሚሊየን፦
➊ከእግዚአብሔር ይልቅ ለራሱ አመለካከት የሚገዛ፤
➋በተለያየ ሱስ የታሠረ፤
➌ ቅዱስ ሥጋ ወደሙን ከሕጻንነቱ በቀር የማያውቅ፤
➍ስለ ቅድስና (ክርስትና) ተግባራዊ ሕይወትን ያላወቀ፤
➎ቤተ ክርስቲያን በመንገድ መሳለም (ብቻውን) እንደሚያጸድቀው የሚያስብ፤
➏ንስሃ መግባት ይቅርና የነፍስ አባት የሌለው፤
➐እኖራለሁ እንጂ እሞታለሁን (ኩነኔን) ያልፈራ . . .
ብለን ስናስበው፥ እውነቱን ተረድቶ ትክክለኛ ክርስቲያን የሆነ ስንት ኦርቶዶክሳዊ ይቀረናል . . .?
☞ከዚህ ተርፎ ወደ ደጁ የመጣውን ደግሞ፦
👉አጥማቂ
👉ባሕታውያን
👉ሰባኪ
👉ዘማሪ
👉Artist
ቀላጤ (Activist)
👉 ካድሬ፥ ጸሐፊ ፥ ለጣፊ፥ . . . ነን የሚሉ ዘርፈው ተከታይ አድርገውታል!
✍ ከእግዚአብሔር ይልቅ የነርሱን ድምጽ ይስቀድማል❗
✍ ከቤተክርስቲያን ይልቅ ለነርሱ ክብር ጥብቅናን ይቆማል❗
እስመ በልዕዎ ለያዕቆብ"(መዝ. ፸፰)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እንዲህ የተዋረደችበት፥ ቅድስና እንኳን ግብሩ ስሙ የተረሳበት ጊዜ መኖሩን እጠራጠራለሁ፡፡
ጊዜው ደግሞ እንዳያያዛችን ታሪካዊ ጥፋት ላይ አድርሶናል
ከታላቁ ውርደት የመጨረሻ አፋፍ ላይም አቁሞናል።
በዚህ መንገድ መጨረሻን "ነበረ" ተብሎ በታሪክ እንደሚነገርላቸው አብያተክርስቲያናት እንዳያደርሰን ያስፈራል፡፡
አውቃለሁ፤ "ሐሳቡ" በራሱ ትልቅ ርዕስ ሆኖ አይሰማን ይሆናል፤
ከግል፥ ከቤተዘመድ፥ ከጓደኛ፥ ከጎሳና ከፖለቲካ ጉዳይ በላይ ገዝፎ ላያስጨንቀንም ይችላል፡፡ ግን እውነቱን መካድ አይቻለንም።
"አኃዊነ ምንተ ንግበር፤ ወንድሞቻችን ሆይ፥ ምን እናድርግ?" (ሐዋ. ፪:፴፯)
https://t.me/eotcy
9 059
ከኪነጥበባዊ ብፌ ለቁርስ የምትሆን ነገር ልጋብዛቹ እርሷም ለወዳጆቾ ጋብዙ
✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍
አንድ ብልህ ተማሪ በፈተና አዳራሽ ገብቶ ሁለት ጥያቄዎችን እንዲሠራ ተሰጠው። ጥያቄዎቹ እነዚህ ናቸው።
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ።
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
ወንድም እህቶቼ ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑረን።
ጊዜያቹን በሙሉ ለእግዚአብሔር ስጡ በጸሎት ሰዓት እሱን አስቡት፣ በስራ ሰአት፣ እግዘብሔርን እያሰባቹ ዋሉ፣ በመንገዳቹ ከእግዚአብሔር ጋር እያወራቹ ተጓዙ በነገራቹ ሁሉ እግዚአብሔርን አስቀድሙ🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ትምህርታዊ ቻናላችንን ለመላቀል👇👇👇
https://t.me/eotcy
9 059
የዓለማችን ድንቅ ሚስጢር❗❗❗
#ሼር
ስለ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያኔ ሳስብ ሁሌ የምደመምበትና የምደነቅበት አንድ ነገር አለ
ምን መሠላችሁ
ሁላችሁም እንደምታውቁት በተለምዶ Oriental Orthodox ተብለው የሚጠሩት ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባህርይ ነው ብለው የሚያምኑ አብያተክርስቲያናት የሚገኙት ( መንበረ ፕትርክናቸው የሚገኝበት ) በአምስት የተለያዩ ሐገራት ውስጥ ነው
አስቡት
👉 አምስቱም በተለያዩ ሀገራት ባህል ቋንቋና ማኀበረሰብ ውስጥ ነው ያሉት
👉 አምስቱም የየራሳቸው ፓትርያሪክና ቅዱስ ሲኖዶስ አላቸው
👉 አምስቱም ራሳቸውን የቻሉ Independent አብያተክርስቲያናት ናቸው አንዱ በአንዱ ጣልቃ አይገባም
👉 አምስቱም የየራሳቸው ቀኖናና አምልኮ ስርዓት አላቸው
👉 አምስቱም በየራሳቸው የጊዜ አቆጣጠር ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያቸውን ያደርጋሉ
በአጠቃላይ አምስቱም አብዛኛውን እንቅስቃሴያቸውን በግላቸው ወይንም እነርሱን በሚመለከት ነገር ላይ ብቻ ትኩረት ያደረገ ነው
💝 እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ ግን በአንድ አይነት ዶግማ ያምናሉ !!!
👉 የውላችሁ 👈
በአንድ አይነት ዶግማ ያምናሉ ሲባል ቀለል አድርጋችሁ በፍጹም እንዳታዩት ‼️❗️
Imagine
እነኚ አብያተክርስቲያናት በጋራ ለመጨረሻ ጊዜ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ያደረጉት በኤፌሶን ላይ በ425 ዓ.ም ላይ ነበር
ከዛ በኋላ 1600 አመታት በጋራ ያደረጉት Official ጉባዔ የለም ‼️❗️
ነገር ግን በያሉበት አካባቢ በየጊዜው Local Synod በማድረግ
ቤተክርስቲያናቸውን ይመራሉ ፣ በቤተክርስቲያናቸው ላይ ለሚነሡ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ፣ የተለያዩ አስተዳደራዊና ሐይማኖታዊ ውሳኔዎችን ያሳልፋሉ ፣ ሐይማኖታቸውን አስጠብቀው ይጓዛሉ ...
👉 እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ ግን
አምስቱም በየራሳቸው በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ እርስ በርሱ የሚጣረስ አስተምህሮ አላመጡም
አንደኛው ያጸደቀው አንደኛው ያልተቀበለው ኃይማኖታዊ ውሳኔም ( ዶግማ ) የለም ‼️❗️
አምስቱም ሲኖዶሳት
በ325 በኒቂያ ጉባዔ
በ381 በቁስጥንጥንያ ጉባዔና
በ425 ኤፌሶን ጉባዔ ከተደነገገው ውሳኔና ና ቀደምት ሐዋርያነ አበው ካስተማሩት ትምህርት ላይ የጨመሩትም ሆነ የቀነሱት አንድም አስተምህሮ የለም !!!
በሚገርም መከራና ሂደትም ከጌታ ከሐዋርያትና ከሐዋርያነ አበው ያገኙትን ትምህርትና ስልጣንም በ Apostolic Succsition እኛ ዘመን ላይ እንዲደርስ አድርገውታል !!!
እናም ይሄንንና መሠል ጉዳዮችን በሚጥጥዬ የአስተሳሰብ አድማሴ ለመመርመር አስባለሁ እንዴት እንደዚህ ሊሆን ይችላል ብዬ እጠይቃለሁ ???
በተለያዩ ሐገራት በተለያየ ቋንቋና ባሕል ውስጥ ያሉ ሰዎች ሳይገናኙ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ቃል መካሪ ሆነው እርስ በርስ ሳይጣረሱ ለሺህ አመታት እንዴት በአንዲት ሐይማኖት በአንዲት ዶግማ አምነው ሊኖሩ ቻሉ ????
እውን ይሄ በሰው ሰውኛ አመለካከት የሚቻል የሚታሰብ ነው ብዬም ደጋግሜ እጠይቃለሁ ???
እንኳንስ የተለያየ ሐገርና የተለያየ ቋንቋ ላይ ሆኖ ይቅርና በአንድ ሐገር እየኖሩ በአንድ ቋንቋ እየተናገሩ ለሺህ አመታት ተመሳሳይ አመለካከት ተመሳሳይ እምነት ማራመድ ምን ያህል ቀላል ነው ???
ብዬም አለማችን አሁን ላይ ካለችበት ሁኔታ አንጻርም ለመመዘን ሞክራለሁ
በመጨረሻም አውጥቼ አውርጄ ለራሴ ይሄንን ምላሽ እሰጠውና መመራመሬን እደመድማለሁ
ይሄ ሁሉ የሚሆነው ነብያት በተለያየ ሐገር ላይ ሆነው ተመሳሳይ መልእክትን ተመሳሳይ ሐሳብን ባናገረና ባጻፈው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መሪነት ብቻ ነው !!!!
ለቤተክርስቲያኗ ራስ በሆነላት በክርስቶስ ኢየሱስ መለኮታዊ ጥበቃ ብቻ የሚመነጭ ነው !!!
ለዚያም ነው ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ
" እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” በማለት ቃል የገባው
— ማቴዎስ 28፥19-20
https://t.me/eotcy
9 059
Repost from ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
ሥላሴ የራሴ አክሊል ናቸው። ሥላሴ የአንጻረ ገጽታዬ ማማተቢያ ናቸው። ሥላሴ የዐይኖቼ ብርሃን ናቸው። ሥላሴ የጆሮዬ መስሚያ። ሥላሴ የጉንጮቼ ወዝ። ሥላሴ አፍ መክፈቻዬ ናቸው። ሥላሴ የከናፍሬን የአነጋገር አልጫነት የሚያጣፍጡ መለኮታዊ ጨው ናቸው።
ሥ ላ ሴ የአንገቴ ማዕተብ ነው❗
ሥላሴ ከድካሜ ያፀናኛል ፣ ሥላሴ ኃይሌና መጠጊያዬ ነው። ሥላሴ መታመኛዬ ነው። ከእናቴ ማሕጸን ጀምሮ በሥላሴ ፀንቼ እኖራለሁ! ይህን ላደረገልኝ ለሥላሴ ምን ወሮታ እከፍላለሁ❓
በልዩ ችሎታው ለፈጠረኝ ሥላሴ ምስጋና ይገባል። በቸርነቱ ለአሳደገኝ ሥላሴ ምስጋና ይገባል። በመሐሪነቱ ጠብቆ እስከዚህች ሰዓት ለአደረሰኝ ሥላሴ ምስጋና ይገባል። እንደ በደሌ ላልፈረደብኝ ሥላሴ ምስጋና ይገባል። ለጌታዬ ለሥላሴ ምስጋና ይገባል። ለንጉሤ ለሥላሴ ምስጋና ይገባል። ለአምላኬ ለሥላሴ ምስጋና ይገባል። ለአለቃዬ ለሥላሴ ምስጋና ይገባል። . . .
በሥላሴነትህ እታመናለሁ - በሦስትነትህም እመካለሁ!🤲🤲🤲
📖 የዓርብ ሰይፈ ሥላሴ
https://t.me/eotcy
https://t.me/eotcy
https://t.me/eotcy
9 059
+++ የአንድ ኃጢአተኛ ሰው ጸሎት ++
አቤቱ “በጎውን ነገር ማን ያሳየናል?” የምንልበት ዘመን አይደለም፤ እንኳን በእኛ ዘንድ ይቅርና ወንጌል በአሕዛብ ዘንድ ሳይቀር የተሰበከበት ዘመን ነውና። ነገር ግን የተሰበከውን ቃል በልቤ አኑሬ ሕይወቴን ሳልለውጥበት ብዙ ዘመናትና ዓመታት አለፉ። ቃልህን ሰምቶ አለማድረግ በአንተ መዘባበት መሆኑን አውቃለሁ፤ ቃልህን የምሰማ እንጅ የምፈጽም ባለመሆኔም ምክንያት በድቡሽት ላይ እንደተሠራ ቤት ሆኛለሁ።
ጥልቀት በሌለው አኗኗር ላይ የተገነባው መንፈሳዊነቴ ጎርፍ በጎረፈ፣ ነፋስ ባለፈ ጊዜ የሚናወጥ ደካማ ሆኖብኛል።
ዓለምን ለማሳለፍ ዳግመኛ መምጣትህን ባሰብሁ ጊዜ እደነግጣለሁ።
ጻድቃን “አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና” እያሉ የምትመጣበትን ቀን ሙሽራዋን እንደምትጠብቅ ሴት በተስፋ ይጠባበቃሉ፤ እኔ ግን አሁንም ለንስሐ ዕድሜ እንድትጨምርልኝ እለምናለሁ።
በተራራው ስብከት ጊዜ ተገኝቼ ስታስተምር ባልሰማህም፤ በደብረ ታቦር በተገለጥህ ጊዜ ክብርህን ካዩት መካከል ባልሆንም፤ በደብረ ዘይት እጅህን ጭነህ ከሾምኻቸው ውስጥ ባልመደብም አንተ ግን ለእኔ ምሕረት ማድረግን አትሰለችም። ወደ አንተ ባልመጣ እንኳን በተኛሁበት መጥተህ “ልትድን ትወዳለህ?” ማለትህ አይቀርም።
ከሰማይ የወረድህልኝ ሆይ! ኢያሱ ለእስራኤል ርስታቸውን እስኪያወርሳቸው ፀሐይን እንዳቆምህለት በምድር ላይ ያለን ኃጥአን ልጆችህ ሰማያዊት ርስትህን ሳንወርሳት ፀሐይ አትጥለቅብን፤ ዕድሜአችን አይለቅብን። አሜን!
( ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ )
꧁ ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂
https://t.me/eotcy
