ኡመተ ረሱል
Open in Telegram
የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይውረድ ውድ የአላህ ባሮች በዚህ #channel ላይ የተለያዩ ♥ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ♥ አስተማሪ ታሪኮች ♥ ቀልዶች እና ♥ ወቅታዊ አሳሳቢ ነገሮችን ወደናንተ እናደርሳለን ፨ ፨ ፨ ለማንኛውም አስተያየት @Ummate_resul_bot ይጠቀሙ
Show more1 977
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2930 days
Posts Archive
1 977
t.me/Quran_Mp3_Collection
1 @mishary_rashid_al_afasi
2 @Yassen_Al_Jazairi
3 @Sheikh_Abu_Bakr_Al_Shatri
4 @Sheikh_Muhammad_Al_Luhaidan
5 @Abdulbasit_Abdussamed1
6 @Sheikh_Abdul_Rahman_Al_Sudais
7 Ali_Al_Huzaifi
8 @Khalifah_At_Tonaeijy
9 Ahmad_Al_Ajmy
10 @Sheikh_Saad_Al_Gamidi
11 Emad_Al_Mansary
12 @Abdullah_ibn_Al_Basfar
13 @Sheikh_Nasser_Al_Qatami
14 @Abdulhadi_Kanakeri
15 @Sheikh_Maher_Al_Muaiqly
16 @Sheikh_Adel_Rayan
17 @Khalil_Al_Hussary
18 @Sheikh_Muhammad_Ayyub
19 @Abdullah_Awad_Al_Juhany
20 @Abdul_Rashid_Ali_Sufi
21 @Mohamed_Siddiq_El_Minshawi
22 @Abdul_Rahman_Al_Ossi
23 @Sheikh_Saud_Al_Shuraim
24 @Yasser_Al_Dosarii
25 @Muhammad_Al_Kurdi1
26 @Fares_Abbad1
27 @Sheikh_Salah_Bukhatir
28 @Imad_Zuhair_Hafez
29 @Muhammad_AbdulKareem
30 Ahmad_Misbahi
31 @Abdulaziz_Az_Zahrani
32 @Ibrahim_Al_Asirii
33 @Abdulbosit_Qobilov1
34 @Abdullah_al_Matrood1
35 @Afzal_Rafiqov1
36 Hani_Ar_Rifai
37 @Abdullah_Ali_Jaber
38 @Sheikh_Muhammad_Jibril
39 Jazza_Alswaileh
40 Bandar_Balila
41 @Mohammad_Al_Tablawi
42 Wadee_Al_Yamani
43 @Ghassan_Al_Shorbajyi
44 Zaki_Dagistan
45 Ahmad_Al_Lahdan
46 @Abdullah_Xalif
47 @Yasser_Al_Qureshi
48 Nabil_Al_Rifai
49 Salah_Al_Hashem
50 Shirazad_Taher
51 @Tawfeeq_As_Sayeghh
52 Rashid_Al_Arkani
53 @Sheikh_Mustafa_Ismail
54 Ali_Yakupov
55 Abdullah_Kamel
56 @Mahmud_Ali_Albanna
57 @Sheikh_Idris_Abkar
58 Hassen_Saleh
59 Moeedh_Al_Harthi
60 Ahmed_Naina
61 Waleed_Al_Naehi
62 Saber_AbdulHakam
63 @Mohammad_Saleh_Shah
64 @AbdulMuhsin_Qasim
65 Salah_Al_Budair
66 Akram_Alalaqimy
67 Jamaan_Alosaimii
68 @Abdulmohsen_Harty
69 @Abdul_Wadood_Haneef
70 @Mohammad_Al_Abdullah
71 Yahya_Hawwa
72 @Hasanxon_Yahyo_Abdulmajid
73 Khalid_Al_Jaleel
74 @Noreen_Muhammad_Siddique
75 @Ahmad_Al_Shalabii
76 @Alzain_Muhammad_Ahmad
77 @Abdulmohsin_Al_Obeikan
78 @Ibrahim_AlAkhdar
© @Quran_Mp3_Collection
1 977
አንብቧትማ..!
ሁለት የሚዋደዱ ጓደሞች ቁጭ ብለው ሳሉ አንደኛው ያማረ ቪላ ቤቶችን ያይና ለጓደኛዉ ፈጣሪ ይህን ሁሉ ሀብት ለእነዚህ ሰዎች ሲያድል እኛ የት ነበርን አለው። ጓደኛውም አጠገቡ ነበረና ና ብሎ ወደ ሆስፒታል ይዞት ሔዶ እንዲህ አለው...
ለእነዚህ ሰዎች ሁሉ ፈጣሪ በሽታን ሲያድል እኛ የት ነበርን ? ከዚያም የታመመ ሰው በሆስፒታል ውስጥ የሞተውን ሰው ሬሳ ተመለከተ ... እርሱም እንዲህ አለ " ተመስገን አምላኬ እንኳ አልሞትኩኝ ምክንያቱም የሞተ ሰው ፈጣሪን አያመሰግንምና አለ"።
ዛሬ ስለ ሁሉም የፈጣሪን በረከቶች እና ምሕረት ለምን አናመሰግንም? ሕይወት ምንድን ነው ? ህይወትን በተሻለ መንገድ ለመረዳት ወደ 3 ቦታዎች መሄድ አለብህ:
*1. ሆስፒታል *2. እስር ቤት *3. መቃበር
በሆስፒታሉ ውስጥ ከጤና በላይ ምንም ነገር እንደሌለ ትገነዘባለህ። በእስር ቤት ነፃነት በጣም ውድ ነገር እንደሆነ ትገነዘባለህ። በመቃብር ውስጥ ሕይወት ምንም ዋጋ እንደሌለው ትገነዘባለህ።
የዛሬ የምንሄደው መንገድ የነገ የሕይወታችን መሰረት ነው። ስለዚህ ትሁት እና አመስጋኝ ሁን። ስለ ሁሉም ነገር ፈጣሪያችን የተመሰገነ ይሁን አልሀምዱ ሊላህ!!
#ሼር #share #join
Https://t.me/smithhk
1 977
በአላህ ፈጣሪነት፤
.....በእስልምና ሀይማኖት በሙሐመድ(ﷺ)ነብይነትና #መልእክተኛነት የተደሰተ ሰዉ የኢማንን ጥፍጥና ቀምሷል። ረሱል(ﷺ)
#ሼር #share #join
Https://t.me/smithhk
1 977
#ኳታር አልተቻለችም! ለምዕራባዊያን ቆምጠጥ ያለ ህግ አውጥታለች
በመጭው ህዳር ወር በኳታር አስተናጋጅነት የአለም ዋንጫ ይካሄዳል።ኳታርም #አጃኢብ የሚያሰኙ ህጎችን እያፀደቀች ትገኛለች።
1.ማንኛውም ተጫዋችም ሆነ ደጋፊ አሊያም አሰልጣኝ ወደ ሀገር ኳታር ሲገባ የኒካህ ወይም የጋብቻ የምስክር ወረቀት ከሌላው ከሴት ጋር አልጋ መያዝ አይችልም እንቢኝ ብሎ ይዞ ከተገኘ ወህኒ ይወረወራል።
2.የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚደግፍ መለያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ አይቻልም።በተለይ ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ግንኙነት ሲያደርጉ ከተያዙ የሞት ፍርድ ይጠብቃቸዋል።
3.የትኛውንም አይነት አልኮል መጠጥ መጣጣት አይታሰብም።በተለይ አንደዛዥ እፆችን ይዞ የተገኘ ሰው እስከ ሰባት አመት እስራት ይጠብቀዋል። እና መሰል ህጎችን ኳታር ያወጣች ሲሆን ህጎቹን ፊፋም አፅድቆታል።
"ለ28 ቀናት ብለን እምነታችንን አንፃረርም" ሲሉም ነው የኳታር እግርኳስ ፌደሬሺን ፕሬዘዳንት ጄነራል አብዱልአዚዝ አብደላ የተናገሩት።
#ኳታር 👏🙏
1 977
🌑የጀሀነም በሮች 7 ናቸው።
▰▰▰▰▰▰▰▰
1ኛው የጀሀነም በር (ሀነም) ይባላል፣
ሀነም ስያሜውን ያገኘው ሴቶችና ወንዶች በአንድ ላይ ስለሚቃጠሉበት እና ስጋዎችን ስለሚትበላ ነው በሌሎች
የጀሀነም በሮች አንጻር አነስተኛ ቅጣት የሚስተናገድበት ነው።
2ኛው የጀሀነም በር (ለዛ) ይባላል፣
ለዛ ሁለት እጆችንና እግሮች በመብላት ትታወቃለች ለተውሂድ ጀርባ የሰጡ ሰዎችና የመልእክተኛውን ጥሪ
ያልተቀበሉ ሰዎች መኖሪያ ነች
3ኛው የጀሀነም በር (ሰቀር ) ይባላል፣ ሰቀር ያገኘውን ሁሉ አያስቀርም ወደ ብናኝ አመድነት ይቀይራል
4ኛው የጀሀነም በር (ሁጠማ ) ይባላል ።
ሁጥማ አጥንት፣ ከአጥንት በማጣበቅ ትታወቃለች ልብ ውስጥ
ዘልቆ የሚገባ ቅጣት የሚስተናገድባት የጀሀነም በር ነች በውስጧ የገቡ ይረዱ ዘንድ ደም፣በደም በሆነ እንባ የታጀበ
ለቅሶ ያለቅሳሉ ነገር ግን የሚረዳቸው አያገኙም።
5ኛው የጀሀነም በር ( ጀሂም) ይባላል፣
ጀሂም በትላልቅ የእሳት ፍሞች የተሞልቷል በጀሂም ውስጥ ያለው
አንዱፍም ትልቀቱ ብቻ ይቺን አለም ያክላል።
6ኛው የጀሀነም በር (ሰኢር) ይባላል፣
በሰኢር ውስጥ "300" ( ሶስት መቶ ) የእሳት ህንጻወች አሉ፣በያንዳዱ ህንጻዎች "300" (ሶስት መቶ) ቤቶች አሉ። በያንዳዱ ክፍል ውስጥ "300" (ሶስት መቶ) የቅጣት አይነቶች ይስተናገዱበታል
በእነዚህ ክፍሎች ውስጥ እባቦችና ጊንጦች በብዛት ይገኙበታል።
7ኛው (ሀዊያ ይባላል)፣ ሀዊያ ውስጥ የገባ ዝንትአለም አይወጣም!!! ሀዊያ በውስጧ ሀባባ የተባለ እንደ ወንዝ ጅረት የሚፈስ እሳት የሆነ ወንዝ አለ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ስድስትቱ የጀሀነም በሮች ሁሉ ሳይቀሩ ከዚህ ወንዝ አላህ ይጠብቃቸው ዘንድ ይማጸናሉ #ሰኡዳ የተባለ ተራራ በውስጧ የአላህ ጠላቶች እጆቻቸውና እግሮቻቸው ከፊቶቻቸው ጋር ታስሮ ከተራራው ጫፍ ላይ በአፍጡማቸው እንዲደፉ ይደረጋሉ !
የጀሀነም ዘበኞችም እነዚህን የአላህ ጠላቶች በከፍተኛ ሁኔታ ያሰቃዮቸዋል።
አላህ ከሁሉም የጀሀነም በሮች ቅጣት ይጠብቀን 🤲
@smithhk
1 977
عن أبي هريرة رضي الله عنه ،
عن النبي ﷺ قال :
((يَجِيءُ القُرْآنُ يَوْمَ القِيَامَةِ فَيَقُولُ : يَا رَبِّ حَلِّهِ. فَيُلْبَسُ تَاجَ الكَرَامَةِ ،
ثُمَّ يَقُولُ : يَا رَبِّ زِدْهُ. فَيُلْبَسُ حُلَّةَ الكَرَامَةِ ،
ثُمَّ يَقُولُ : يَا رَبِّ ارْضَ عَنْهُ. فَيَرْضَى عَنْهُ ،
فَيُقَالُ لَهُ : اقْرَأ وَارْقَ ، وَتُزَادُ بِكُلِّ آيَةٍ حَسَنَةً))
رواه الترمذي.
1 977
የአገር መሪ ናቸው። ፍትህን ያነገሱ የሐቅ ሰው። በእውነት ብርሀን ስር የዳኙ መሪ። አንድ ምሽት ላይ በመኖሪያ ቤታቸው በሻማ ብርሃን እየታገዙ የአስተዳደራቸውን የግምጃ ቤት የገቢና ወጪ ሂሳብ በመስራት ላይ ናቸው። በር ተንኳኳ። እሳቸውን ለማነጋገር የሚፈልጉ ሁለት ሰዎች ነበሩ። በአስተዳደሩ ስልጣን ውስጥ ሁነኛ ቦታ የማግኘት ምኞት ነበራቸው። የመጡትም ይህንን ህልማቸውን ያሳካልናል ያሉትን አንድ ሃሳብ ይዘው ነው። ይህንን ሃሳባቸውን በመቀበል በመንግስታቸው ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን የሚስጧቸው ከሆነ እነርሱ በፊናቸው ሙሉ ድጋፍ ለመስጠት ቃል እንደሚገቡ በመግለፅ ለመደራደር ነበር።
ሰዎቹ እንደተቀመጡ የበራው ሻማ ጠፋና ሌላ ሻማ ተለኮሰ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ሰዎች በመገረም ሰሜት እርስ በእርሳቸው ተያዩ። ምክንያቱን ለማወቅ የበለጠ ጉጉት ያደረበት አንደኛው ሰው የመጣበትን ጉዳይ ከማንሳቱ ቀደም ብሎ የሚበራውን ሻማ አጥፍተው ሌላ ሻማ የለኮሱበት ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቀ። እሳቸውም "እናንተ ወደቤት ስትገቡ ይበራ የነበረውን ሻማ ከመንግስት ግምጃ ቤት ገንዘብ ወጪ ተደርጎ የተገዛ የህዝብ ሀብት ነው። ይህ የምትመለከቱትን የግምጃ ቤት የወጪና ገቢ ሂሳብ ለመስራት ስል ነበር ያበራሁት አሁን እናንተ የመጣችሁበት ጉዳይ የግል ጉዳያችሁ በመሆኑ የበፊቱን ሻማ በማጥፋት ይህንን ከራሴ ገንዘብ ወጪ አድርጌ የገዛሁትን ሻማ ለኮስኩት" በማለት ለቀረበው ጥያቄ ማብራሪያ ሰጡ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ሰዎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት እርስ በእርሳቸው ተያዩ የመጡበትን ዓላማ ማንሳት ቀርቶ አንዲት ሌላ ቃል እንኳ መተንፈስ ተሰኗቸው ወጥተው ሄዱ። ሰውየው አሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ነበሩ። አላህ መልካም ስራቸውን ይቀበላቸው።
ኢስላም አለምን ሲመራ እንዲህ ነበር ፍትህ የነገሰው
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
1 977
على هامان يا فرعون؟؟
ፈገግታ ከፊርዓውን ጅልነት ጋ…
«ፊርዓውን ከነበረበት ድንበር ያለፈ ጥመት ጋ ጅል (ፋራ) ነገር ነበር አሉ። አማካሪው ሃማን ደግሞ እንደ የትኛውም የንጉሶች አማካሪ ብልጣብልጥ ነበር አሉ። እናም ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት በፊርዓው “የጌትነት ሙገታ” ያመነች አሮጊት ፍየልዋ ይሞትባትና ወደ ፊርዓውን ቤት ትመጣለች።
ስትመጣ ፊርዓውን አልነበረም ሃማንን አገኘችው።
"ጉዳይሽ ምን ነበር?" ሲላት
"ፍየሌ ሞታብኝ ፊርዓውን ሕያው እንዲያደርጋት ነበር የመጣሁት።" ትለዋለች
ሃማን ብልጥ ነበር; ብለን የለ?
"ነይ በቃ ፊርዓውን አሁን ግመል እየፈጠረ ስለ ሆነ ይቆይብሻል። ስለዚህ ሌላ ፍየል ልስጥሽ።" ይላትና ሌላ ፍየል ሰጥቷት ትሄዳለች።
ፊርዓውን ወደ ቤቱ ሲመለስ ሃማን "አንዷ አሮጊት ፍየሏ ሙቶባት ሕያው እንድታደርግላት መጥታ ነበር።" ሲለው ፊርዓውን ደነገጠ።
ሃማን "አይዞህ! ፊርዓውን ግመል እየፈጠረ ነው። ብያት ሌላ ፍየል ሰጥቻት ሄዳለች። አትመጣም።" አለው።
በዚህ ጊዜ ፊርዓውን እንደ መረጋጋት አለና በረጅሙ ተንፍሶ…………
«ግመል መፍጠር እኮ እንዴት እንደ ሚያደክም ብታይ» አለው።
ሃማን ፈገግ አለና… …
على هامان يا فرعون
ኧረ ፊርዓውን! በሃማን ላይ❓አለው
በሃማን ላይ ሙድ ትይዛለህ ወይ እንዴ ጭራሽ ልትሸውደኝ ያምርሃል ማለቱ ነው።
ከዛኔ ጀምሮ ሰዎች በሚያውቁት ነገር ላይ ሊሸውዳቸው ለሞከረ ሰው
على هامان يا فرعون
ኧረ ፊርዓውን! በሃማን ላይ❓አለው
እያሉ አባባል አድርገው ይዘውታል።»
@smithhk
1 977
ሙስሊሞችን ሰልቅጠው ሊበሉ አሰፍስፈዋ። በሙስሊሞች ከተማ መግቢያ በራፍ ላይ ጦራቸውን ሰብቀው ቆመዋል። ሰራዊቱ ተቀዳሚ ከፊል ጦሩን ወደፊት ለፊት አስጠግቷል። አንድ ሽማግሌ ከትንታጉ ጨቅላ ልጃቸው ጋር በመጥረቢያ እንጨት እየፈለጡ ነበር የመስቀላዊያኑ የጦር መሪ የተመለከታቸው። ሶስት ወታደሮቹን ይዞ ወደ እነርሱ ተጠጋ። "ስለ ሀገራችሁ መረጃን እንድትሰጡን እጠይቃችኋለው ስንት ሰራዊት እንዳለ የከተማዋንም መግቢያና መውጫ እንድትጠቁሙን" እንፈልጋለን አለ።
ሽማግሌው መጥረቢያቸውን በትከሻቸው ላይ እንደሸከፉ ካቀረቀሩበት ተነሱ
"ሁሉንም ነገር ከመንገሬ በፊት ምስክር እንዳይሆንብኝ ይህ ከአጠገቤ የቆመውን ልጅ ግደ*ሉል*ኝ" ሲሉ ተናገሩ።
ከመካከላቸው አንዱ ሠይፉን መዞ የልጁን አንገት በጠሰው። ደ*ሙ የምድሩን አፈር አራሰ። የብላቴናውን ታዳጊ ነፍስ ወደመጠጠችው መሬት ሸኹ ተመለከቱና እንዲህ አሉ
"ይህ እንድትገድሉት ያዘዝኳችሁ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ?"
"ስለ እሱ ከኛ የበለጠ አንተ ታውቃለህ" ሲሉ መለሱላቸው።
"አዎ በእርግጥም ይህ ልጄ ነው። እኔን ገድላችሁ ከሱ መረጃን እንዳታገኙ ፈርቼ ቀድሜ ልጄን ሰዋሁት። ሀገሬን ወራችሁ ሙስሊም ወንድሞቼን እንድትገድሉ የሚረዳችሁን አንድ መረጃ ከምናገር ሞቴን እመርጣለሁ። ይሄው ፊታችሁ ቆሜያለሁ ቢሻችሁ በገመድ ቢሻችሁም በሰይፍ ነፍሴን ከሩሔ ጋር ነጥሏት እንጂ አንድ መረጃ ከኔ አታገኙም" አሏቸው።
ወታደሮቹ የልጁን ጀናዛ ተሸክመው ወደ ንጉሳቸው ይዘውት አቀኑ። ክስተቱንም አወጉት።
ንጉሡም እንዲህ አለ:-
"ሙስሊሞች ልጆቻቸውን የሚሠውባትን ከተማ በእርግጥም መቆጣጠር አንችልም። ብንወራቸው እንኳ ድልን አንጎናፀፍምና ሠራዊቱን ይይዛችሁ ወደ ኋላ ተመለሱ" ሲል አዘዘ።
በእርግጥም ንጉሱ እውነትን ተናገረ
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
1 977
እንዲህ አይነትም ሰዋዊ ሰይጣኖች አሉና ሰሞኑን ተጠንቀቁ።
«Aselam Aleykum werahmetullahi weberekatu
ትላንት አመሻሽ ላይ ከቤት ሱቅ የተላከች ወጣት መንገድ ላይ መታወቂያ አሳይ ፍተሻ ነው ትባላለች::እንዳልያዘች እና ቤት ነው ስትል ትፈለጊያለሽ ተብላ አንዱ እያዋከበ ነጥሎ ይወስዳታል:: እሷም ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሚወስዳት መስሏት ሳታንገራግር ትሄዳለች አሳቻ ቦታ ሲደርሱ ምት ይከተላታል መጨረሻ እራሷን ስታ ስትነቃ በደም ተጨማልቃ ተደፍራ ስውነቷ ቆሳስሎ ፊቷ አባብጦ በልዞ እሯሷን አገኘችው::
ማታ ተረኛ ሆኜ ማክምበት ሆስፒታል ወላጆቿ ደም እንባ እያነቡ የነገሩኝ አስነዋሪ ድርጊት ነው::
ይህንን ቀውጢ ጊዜ እንደ አጋጣሚ ተጠቅሞ እንዲህ አይነት የእንስሳ ተግባር ሚፈፅሙ የሰው ህሊና የሌላቸው አረመኔዎች አሉና ሁሉም ጥንቃቄ ያድርግ::
አገራችንን ፈጣሪ ሰላም ያድርግልን::»
አንድ ወንድም በውስጥ የላከልኝ መልዕክት ነው። ምን አይነት እንስሳዎች ናቸው በአላህ!
እና ደግሞ መታወቂያ (የቀበሌ፣ መንጃ ፈቃድ፣ ፓስፖርት) እየያዛችሁ ጓዶች!
1 977
عن أوس بن أوس رضي الله عنه قال :
سمعت رسول الله ﷺ يقول :
((مَنْ غَسَّلَ يَوْمَ الجُمُعَةِ وَاغْتَسَلَ ، ثُمَّ بَكَّرَ وَابْتَكَرَ ، وَمَشَى وَلَمْ يَرْكَبْ ، وَدَنَا مِنَ الإمَامِ فَاسْتَمَعَ وَلَمْ يَلْغُ ، كَانَ لَهُ بِكُلِّ خُطْوَةٍ عَمَلُ سَنَةٍ أجْرُ صِيَامِهَا وَقِيَامِهَا))
رواه أبو داود.
1 977
عن أوس بن أوس رضي الله عنه قال :
قال النبي ﷺ :
((إنَّ مِنْ أفْضَلِ أيَّامِكُمْ يَوْمَ الجُمُعَةِ فَأكْثِرُوا عَلَيَّ مِنَ الصَّلَاةِ فِيهِ ؛ فَإنَّ صَلَاتَكُمْ مَعْرُوضَةٌ عَلَيَّ))
رواه أبو داود.
«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ»
1 977
እኚህ ሰው ማን ናቸው?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከሕፃን እስከ አዋቂ፣ ወጣትም ሆነ አዛውንት ስለ እሳቸው ሲወራ "ጆሮ ዳባ ልበስ" የሚል የለም። ሁሉ ስለ እሳቸው ሲወራ አዳሜ ሆነ ሔዋኔ ጆሮውን አስግጎ ይሰማል፥ ከሁሉም ከሁሉም የሚገርመው ደግሞ የሚጠሏቸው ሳይቀር እንኳን ቢሆን ስለ እሳቸው ለመስማት እና ስለ እሳቸው ለማወቅ ይፈልጋሉ። ዝም ብለህ ሰው የተሰበሰበበት መሀል ገብተህ እና ድምጽክን ከፍ አድርገህ፦ "እከሌ" ብለህ ወይም "እከሊት" ብለህ ብትጣራ ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ የሚያዞረው የጠራከውን ስም ባለቤት ብቻ ነው፥ ከሌለም ደግሞ ማንም ፊት እና ትኩረት የሚሰጥክ አይኖርም። ነገር ግን ሰው የተሰበሰበበት ስፍራ ሄደህ የእሳቸውን ስም ጠርተህ ንግግር ብትጀምር ሁሉም ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ ያደርጋል፥ ትኩረት የማይሰጥህ የለም ቢባል ማጋነን እና ማበል አይሆንም። ስለ እሳቸው ለማወቅ የማይሰለፍ አይኖርም፥ እኚህ ሰው፦
1ኛ. የእልፍ አእላፋት መጻሕፍት ርእስ በመሆን ብዙ ጸሐፊያን የከተቡላቸው ናቸው፣
2ኛ. በሁሉም ልብ ውስጥ በአሉታዊ ሆነ በአንታዊ በሁለት ወገን እንደተሳለ ሰይፍ ሰርስረው የገቡ ናቸው፣
3ኛ. አስተምህሮታቸው የተሟላ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ የሕይወት ዘይቤ በመሆኑ የዓለማችን ተግዳሮት ነው የተባለላቸው ናቸው፣
4ኛ. "የዓለማችን ቁጥር አንድ አውንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ" ተብለዋል፥ ለሕሩያን አውንታ ተጽዕኖ እንዲሁ ለእኵያን አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ ናቸው፣
5ኛ. ስለ እርሳቸው ማንነት የገባው ሰው፦ "ሕይወትህን መስዋዕት አርግ" ቢባል ያለ አንዳች ማቅማማት ሕይወቱን እስከ ሞት የሚያደርግላቸው ናቸው።
6ኛ. በታሪክ ውስጥ እሳቸውን ለማነወር፣ ለማበሻቀጥ፣ ለማብጠልጠል ብዙ ጦማሪያን ጦምረዋል፣ ብዙ ኃያሲያን ኃይሰዋል፤ ብዙ ተቺዎች ተችተዋል፣ ብዙ ተሳላቂዎች ተሳልቀዋል። ቅሉ ግን የጦማሪያን ጦማር፣ የኃያሲያን ኂስ፣ የተቺዎች ትችት፣ የተሳላቂዎች ስላቅ ከሟቾች ጋር ሲያልፍ የእሳቸው ስም እና የሰዎችን ሕይወት የቀየሩበት መጽሐፍ እስካሁን አለ የተባለላቸው ናቸው።
እኚህ ሰው ማን ናቸው? አዎ! የዓለማቱ ጌታ የአሏህ መልእክተኛ እና የነቢያት መደምደሚያ ነቢዩ ሙሐመድ"ﷺ" ናቸው። በእርሳቸው ላይ የወረደው ሐቅ ለሰዎች የሚጠቅም ስለሆነ በምድር 1400 ዓመት ቆይቷል፥ ባጢል ቢሆን ኖሮ በእንጭጩ ኮረፋት ሆኖ ተግበስብሶ ይጠፋ ነበር፦
13፥17 *"እንደዚሁ አላህ ለእውነት እና ለውሸት ምሳሌን ያደርጋል። ኮረፋቱማ ግብስብስ ኾኖ ይጠፋል፥ ለሰዎች የሚጠቅመውማ በምድር ላይ ይቆያል፡፡ እንደዚሁ አላህ ምሳሌዎችን ይገልፃል"*፡፡ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْحَقَّ وَالْبَاطِلَ ۚ فَأَمَّا الزَّبَدُ فَيَذْهَبُ جُفَاءً ۖ وَأَمَّا مَا يَنفَعُ النَّاسَ فَيَمْكُثُ فِي الْأَرْضِ ۚ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْأَمْثَالَ
ሐዋ. ሥራ 5፥38-39 አሁንም እላችኋለሁ፦ ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም! *ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና፥ ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም። በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ"*።
ገማሊያ እንደተናገረው ይህ የነቢያችን"ﷺ" እሳቦት ከሰው ከሆነ ይጠፋ ነበር፥ ግን የነቢያችን"ﷺ" ግልጠተ-መለኮት ከፈጣሪ ስለሆነ ገና በእንጭጭነቱ የመካህ ቁሬይሾች፣ የመዲና በኑ ቁሬይዛህ፣ የሮሙ ባዛንታይን በዕውቀት መሞገት ሲያቅታቸው በጉልበት ሊጠፉት ሞክረው አልተሳካላቸው። ከርሞም ሆነ ዘንድሮም እሳቸው ላይ ለሚሳለቁን ተሳላቂዎች አሏህ በቅቶላቸዋል፥ በእርሳቸው ላይ የወረደውን የአሏህን ብርሃን በአፎቻቸው ለማጥፋት ቢፈልጉ እና ቢጠሉም አሏህ ብርሃኑን ገላጭ ነው፦
15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ
61፥8 *"የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ፥ ከሓዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ አላህ ብርሃኑን ገላጭ ነው"*፡፡ يُرِيدُونَ لِيُطْفِئُوا نُورَ اللَّهِ بِأَفْوَاهِهِمْ وَاللَّهُ مُتِمُّ نُورِهِ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ
ይህንን ብርሃን ለማጥፋት እፍ ባሉ ቁጥር እያነደዱት መሆኑን ይዘነጋሉ፥ ኢሥላም በፍጥነት መጠነ-ሰፊ የእድገት መርሓ-ግብር እየታየበት ያለው በምዕራባውያን መሆኑ እፍ ባሉ ቁጥር የሚያነዱበት ውጤት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።
“ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሡሉሏህ” فِدَاكَ أَبِي وَأُمِّي يَا رَسُول اللَّه
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
ወሠላሙ ዐለይኩም
1 977
ያ ረሱለላህ! እንወድዎታለን። ይቀበሉናል?
እኛ እርሶን ስንወድ
በእርግጥ የፊትዎን ፍካት ለመመልከት እድል አግኝኝተን አይደለም። ወይም የድምፅዎን መስረቅረቅ በጆሮዎቻችን አዳምጠን አይደለም።
እኛ እርስዎን ስንወድ
ከጎንዎ ሰይፍ አንግተን ከሙሽሪኮች የመፋለም እድል ኖሮን አይደለም። አልያም በኡሑድ ዘመቻ ከእርስዎ ጎን ተሰልፈን ተዋግተንም አይደለም።
እኛ እርስዎን ስንወድ
ቤት ንብረታችንን ትተን በረሀ ለበረሀ ተሰደን አይደለም። እርስዎ ሲሰደዱ ስንቅ አመላልሰንም አይደለም። ወይም እርስዎ ሲሰደዱ ለርሶ መከታ ሆነን ተቀብለንዎትም አይደለም።
ነገር ግን ያ ረሱለላህ! እኛ ወላሂ እንወድዎታለሁ።
ምን እናድርግ! ፍቃዱ የኛ ባልሆነበት ጉዳይ ላይ ከርሶ ዘመን ዘግይተን ተፈጠርን። በወላጆቻችን ላይ አላህ በዋለው የእስልምና ፀጋ እኛም ተቋደስን፤ ስለ እርስዎም እየሰማን አድገን ጎረመስን፤ ስለ እርስዎ እያሰብንም በናፍቆት አነባን።
ዘመንዎን ደርሰን ሳናይ በዘመንዎ የኖርንበት ያህል እየናፈቀን ያልኖርንበትን ዘመን ዳግም በተመለሰ ብለን ተመኘን።
እርስዎ በዘመንዎ ሁነው የኛን ዘመን ናፍቀው እንዳነቡት ሁላ እኛም በዘመናችን ሁነን የእርስዎን ዘመን እየናፈቅን በማንባት የመገናኛ ቀጠሮአችንን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን።
ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
1 977
የፈረንሳይን ዙፋን ያናወጠችው ሶፊ ፔትሮናን
ፈረንሳዊ ናት በማሊ ሙጃሂዶች ቁጥጥር ስር ውላ ለአራት አመታት መድረሻዋ ሳይታወቅ ከርማለች። አዎ ታግታ ነበር ከተለቀቀች በኋላ ግን የህይወት እስትንፋሷ ወደ ፈረንሳይ ምድር እያምዘገዘገ ጠቅላይ ሚኒስትር ማክሮን ፊት አቆማት። ሊቀበላት ኤርፖርት ድረስ መጣ። ያሳለፈችውን ጊዜ ለመስማት በእጅጉ ጓጓ። በሀገረ ማሊ ስላገቷት ሙጃሂዶች ማንነት ከአንደበቷ ሊያዳምጥ ጆሮውን ቀስሮ ተጠባበቀ።
"አዎ በእርግጥም እነሱ ዘንድ ምርኮኛ ነበርኩ" ብላ ንግግሯን ትጀምራለች
"ለኔ የነበራቸው አያያዝ በአክብሮት የተሞላ ነበር። ምግብ እና መጠጥ ያቀርቡልኛል። ፍላጎቴንም ያሟሉልኛል። ከመሐከላቸው ማንም በቃላትም ሆነ በአካል ትንኮሳ ፈፅሞብኝ አያውቅም። እስልምናን እንድቀበል አላስገደዱኝም። ግና ኢስላምን በሥነ ምግባራቸው ውስጥ አይቼዋለሁ። በአምስት ወቅቶች ወደ ጌታቸው ይዋደቃሉ። ለጌታቸው ያደሩ አልቃሾች። አላህን የሚወዱ ባሮች፣ ለእሱ ኩምሽሽ ብለው የሚያነጉ ፍፁም የጌታቸው ታዛዦች ናቸው .....
አዎ ማክሮን
ሀገራቸው በድህነት የተሞላ ቢሆንም እነርሱ ግን ለሰዎች አዛኝና ተናናሾች ናቸው። የፈረንሳይን ሽቶ አይቀቡም። ነገር ግን ሰውነታችን ንፁህ ልባቸውም ፅዱ ነው። የቅንጦት መኪናዎችን አይነዱም። በረጅም ፎቆች ላይም አይኖሩም። ዓላማቸው ግን ከደመና በላይ፣ እምነታቸውም ከተራራ የጸና ነው" የአንደበቷ አገላለፅ ይጣፍጣል። ንግግሯ ይማርካል። ቀጠለች ...
ማክሮን
"ቁርኣን ሲነበብ ሰምተህ ታውቃለህን? የሚያወሩት ባይገባህም ድምፃቸው ልብን ይሰረስራል። ቀልብህን ያረሰርሳል። ጭንቀትህን ረስተህ አለምን የጨበጥክ ይመስልሀል።
ሴቶቻቸው ጥቁር ኒቃብ ይለብሳሉ። ልባቸው ግን እንደ ወተት ነጭ ነው። ውበት የሌለው ልብሶቻቸው በወንዶቻቸው ዘንድ አያስንቃቸውም። እንደ ጀነቷ እንስት ማታ ማታ ሊያገኟቸው ይጓጉላቸዋል። ከወንዶች ጋር አይቀላቀሉም። ባሏ በሌለበትም ቤቷ ወንድ አይደርስም። አልኮል መጠጥ አይጋቱም። ቁማር አይጫወቱም። ዝሙትም በየጎዳናው አይፈጽሙም።
ከእኛ በላይ የአላህ ነቢይ ኢየሱስንም ይወዱታል ማክሮን ሆይ! ለምን ይመስልሀል?! ሀገራችን በክርስቶስ ስም የንጹሃንን ደም እያፈሰሰች ሀብታቸውን ስለተቀራመተች?! በአገራቸው ሀብት እየቦረቅን ስለክብራቸው ስለተፋለሙ ብቻ አሸባሪዎች እንላቸዋለን።
እነርሱ ግን አለችና .... ሲቃ ተናነቃት እንባዋ በጉንጮቿ በኩል ኩልል ብሎ ፈሰሰ .... "እነርሱ ግን ... እኔም ሆንኩ ሌሎች ታጋቾች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተማርነው መሰረት እንደ ጭራቅ የተሳሉበትን ገፅታቸውን አላገኘነውም።
ሐዘን ባጠለለው ገፅታዋ እየተመለከተችው
"በመጨረሻም ማክሮን ሌት ተቀን የምትታገለው የልቤን ምት አንቀሳቅሶ ውስጤን በሐሴት የሞላው እስልምና ይህ ነው። ከአሁን በኋላ ፈረንሳይን ውብ አድርጌ አላያትም። አባጣና ጎርባጣዋ የማሊ ገፅታ እኔ ዘንድ የበለጠች ቆንጆ ናት። እንደገና ወደ ማሊ ለመመለስ ወስኛለሁ። በገዛ ፈቃድ ለዘልዓለም ምርኳ ልሆን እሻለሁ። አሁን ግን ቤተሰቦቼንና ዘመዶቼን ወደ እስልምና ልጋብዛቸው መጥቻለሁ። እኔ የቀመስኩትን ጣፋጭ ጣዕም እንዲቀምሱ እፈልጋለሁና።
እናንተንም ከዚህ ታላቅ ሀይማኖት ጋር ያላችሁን ሂሣብ እንድታጤኑት እመክራችኋለው" ንግግሯን ጨረሰች ወሬዋ ውስጤን ሰርስሮት ገብቷል እስልምናን ከፊል ሰዎች ብቻ ለምን ይኖሩታል እኛስ? ስል ራሴን እንድጠይቅ አድርጎኛል። አላህ ይሁነን ወስ-ሰላም።
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
