en
Feedback
ኡመተ ረሱል

ኡመተ ረሱል

Open in Telegram

የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይውረድ ውድ የአላህ ባሮች በዚህ #channel ላይ የተለያዩ ♥ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ♥ አስተማሪ ታሪኮች ♥ ቀልዶች እና ♥ ወቅታዊ አሳሳቢ ነገሮችን ወደናንተ እናደርሳለን ፨ ፨ ፨ ለማንኛውም አስተያየት @Ummate_resul_bot ይጠቀሙ

Show more
1 977
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2930 days
Posts Archive

የዙልሒጃ ወር ነገ ሰኞ  አንድ ብሎ ይጀምራል! የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል ሰኔ 21 ዕለተ ረቡዕ እንደሚከበር ታውቋል! ዛሬ እሁድ ሰኔ 11/Jun18/2023 በሂጅሪያ አቆጣጠር ደግሞ  ዙልቀይዳ 29  በሳዑዲ አረቢያ አዲስ ጨረቃ በመታየቷ የዙልሂጃ ወር  በነገው እለት ሰኞ  ሰኔ 12/june 19  አንድ ብሎ እንደሚጀመር  ታውቋል:: የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልም እሮብ ሰኔ 21/2015/June 28/2023 እለተ ረቡዕ እንደሚውል ታውቋል፡፡ ከነገ ሰኞ ሰኔ 12/June 19  ጀምሮ እስከ ሰኔ 21/june 28 ድረስ ያሉትን 10 ቀናት በኢባዳ ልናሳልፋቸው ይገባል፡፡ የዙልሂጃን ዘጠኙንም ቀናት ለመፆም ፍላጎት ያለው ከነገ ሰኞ ሰኔ  12 /2015  ጀምሮ መፆም ይችላል፡፡ ታላቅ ምንዳ የሚያስገኘውን የዙልሒጃ 9 (የአረፋን ቀንን) ለመፆም የሚፈልግም ሰኔ  20/june27/2023  እለት ማክሰኞ መፆም ይችላል:: ኡዱሂያ ለማረድ ኒያው ያላችሁ ካሁን ሰዓት ጀምሮ ጥፍራችሁን እና ፀጉራችሁን ከመቆረጥ ታቀቡ! ከነገ ሰኞ ጀምሮ ያሉትን ተከታታይ አስር ቀናቶች በኢባዳ እናሳልፋቸው!

+1

10ቱ የዙልሒጃ ቀናት.pdf3.33 KB

🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 #ምርጦች ኢብን መስኡድ እንዲህ ይላሉ አላህ ከቀናት አራት , ከወራት አራት ከሴቶች አራት, የጀነት ቀዳሚዎችን አራት, ጀነት የምትናፍቃቸውን አራት ሰዎች መርጧል 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 🗓ከቀናት 1— የጁምዐ እለት 2— የዐረፋ እለት 3— የውመ ነህር( የእርድ ቀን) 4— የውመል ፊጥር( የረመዳን ዒድ) 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 📆ከወራት 1—ረጀብ 2—ዙልቂዕዳ 3—ዙልሂጃ 4—ሙሀረም 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 🌷ከሴቶች 1—መርየም ቢንት ዒምራን 2— ኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ 3— አሲያ ቢንት ሙዛሂም 4— ፋጢመቱ ዛህራእ ቢንት ሙሀመድ 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 ⚡️የጀነት ቀዳሚዎች 1— ሀቢቢ ሙሀመድ (ሰዐወ) የአረቦች ቀዳሚ 2—ሰልማን የፋርስ ቀዳሚ 3—ሱሀይብ የሮም ቀዳሚ 4— ቢላል የሀበሻ ቀዳሚ 🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹 ጀነት የናፈቀቸቻቸው 1—ዐሊ ኢብን አቢጧሊብ 2—ሰልማነል ፋሪሲ 3—ዐማር ኢብን ያሲር 4—ሚቅዳድ ኢብን አስወድ ➖➖➖➖➖➖➖➖ 🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 #Share #ሼር #join Https://t.me/smithhk

🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 ሶላት የፍቅር ቦታ ! ❥❥❥❥❥❥❥❥❥❥     አይጥ ግመልን ወደደ ። ጓደኝነትም መሠረቱ ። አይጥም የግመሉን ልጓም በመያዝ በእንግድነት ወደ ቤቱ ወሰደው ።  አይጥ መኖርያው ግመሉን ሊያስገባ እንደማይችል ሲረዳ አዘነ፣ እፍረትም ተሰማው... ግመልም እንዲህ አለው ... " በልክህ ውደድ ። አሊያም በወደድከው ልክ ቤትህን አዘጋጅ !!     ኢብኑል ቀይም ይህን አንስተው አለቀሱና እንዲህ አሉ ... " አንተ ሰጋጅ ሆይ ! ሰላትህን የምትሰግድለትን ጌታ የሚመጥን አድርገህ ስገድ   ወይም በሰላትህ ልክ ምትገዛውን ጌታ ፈልግ  !" ኢብኑል ጀውዚ ... " አንዲት አሮጊት ከዙህር ወቅት በፊት ዉዱእ ስታደርግ ያዩአት ሰዎች ዙህር አላዘነም ቢሏት... " እኔኮ ሳይጠራኝ ነው ወደሱ ምሄደው አለች " አሉ ! #ፍቅር ጥሪ አይጠብቅም! ❤ጁምዐ❤ ❤ሱረቱል ከህፍ❤ ❤ሰሉ አለ ነቢ❤ ❤አላሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ነቢዪና ሙሀመድ❤ 🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 #share #ሼር #join Https://t.me/smithhk

¶ሉቅማን የቁርአንና የተጅዊድ ማእከል ማእከላችን በኦን- ላይን ከ አሊፍ ጀምሮ እስከ ተጅዊድ ትምህርት ድረስ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል። እርሶም ፈጥነው ይመዝገቡና ትልቁን የቁርዐን
¶ሉቅማን የቁርአንና የተጅዊድ ማእከል      ማእከላችን በኦን- ላይን ከ አሊፍ ጀምሮ እስከ ተጅዊድ ትምህርት ድረስ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል። እርሶም ፈጥነው ይመዝገቡና ትልቁን የቁርዐን እውቀት ይሸምቱ።     ✅ቃኢደቱ ኑራኒያ ለጀማሪዎች          ✅ነዝር ከመሰረታዊ ተጅዊድ ጋር          ✅ የተሟላ የተጅዊድ ትምህርት          ✅ቁርዐን ሂፍዝ (ፈተና አለው)   𒊹︎︎︎ የቁርዐን ትምህርት አሰጣጥ ሁኔታ አንድ ተማሪ ከተመዘገበ በኋላ የተመደበለት ኡስታዝ ጋር ↪️በቴሌግራም ↪️በዙም አፕልኬሽን እንዲሁም ↪️በዋትሳፕ   𒊹︎︎︎ የቁርአን ቂረአት የሚሰጥበት ጊዜ ↪️ በሳምንት 5 ቀን ↪️ ቅዳሜ እና እሁድ ብቻ ለሚመቻቸው ሰፋ ያለ        ሰዓት በመስጠት እናስቀራለን። 📜 ለመመዝገብ እነዚህን መንገዶች ይጠቀሙ                                  ☞︎︎︎  +251922094434                                    እንዲሁም በቴሌግራም መመዝገብ ለምትፈልጉ      @Luqmanmemzgebiya2      @Luqmanmemzgebiya3   ©ሉቅማን የቁርአንና የተጅዊድ ማዕከል 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/luqman1111111

🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 በደልን አሜን ብላችሁ በመቀበል የበታችነትን አትለማመዱ ታላቁ ሊቢያዊው ሙጃሂድ/ዑመር አል ሙኽታር ✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅ ወደ ሱዳን ከሚሄደው ቅፍለት ጋር አብረው ታላቁ ሊቢያዊው ሙጃሂድ/ዑመር አል ሙኽታር አየተጎዙ ሳለ በተለምዶ አንበሳ መንገደኞችን የሚያድንበት ቦታ ደረሱ ። አካባቢውን ጠንቅቀው የሚያውቁት:- " ከግመሎቻችን አንደኛውን አርደን ለአንበሳው ካልገበርን ተበልተን ማለቃችን ነው! " በማለት አንዱን ግመል እንረድ የሚል ሃሳብ አቀረቡ። ዑመር አል ሙኽታር ግን አልተዋጠላቸውም ፤በጽኑ ተቃወሙ። " በእኛ ላይ ድንበር አልፎ ለመጣ በሙሉ ማባበያ ማቅረብ የበታችነትን የሚያለማምድ ክፉ በሽታ ነው። በደልን አሜን ብላችሁ በመቀበል የበታችነትን አትለማመዱ። አንበሳውን ገድለን ማለፍ አለብን!" አሉ በጀግንነት። እንደተለመደው አንበሳው ድንገት ብቅ አለ። መንገደኞች ብርክ ብርክ አላቸው። "የኔን ግመል ለመሰዋት ዝግጁ ነኝ። አንበሳውን አትተናኮሉት። ዋናው መትረፋችን ነው!" አለ አንዱ መንገደኛ ። ዑመር አልሙኽታር የሰውየውን ተማጽኖ ከቁብ ሳይቆጥሩ መሳሪያቸውን ወደ አንበሳው አነጣጥረው ተኮሱ። አንበሳው ግን አልሞተም ፤ ወልገድ ወልገድ እያለ ወደ መንገደኞች መገስገሱን ቀጠለ። ሰዉ በፍርሀት ተውጧል ዑመር ግን እጅ አልሰጡም። አንበሳውን ሲደግሙት ተዘረገፈ ። ሞተም። ዑመር አል ሙኽታር የአንበሳውን ቆዳ በመግፈፍ መንገደኞችን ከፍርሀት ቆፈን አላቀቋቸው!። በዘመኑ ይህ ታላቅ ገድል የየመጃሊሱ መነጋገርያ ሆኖ ነበር። ሙሐመድ አል ጠይብ አል አሽሀብ ዑመርን "እንዴት ድፍረቱ መጣልህ?" ብሎ ለሰነዘረው ጥያቄ ከዑመር የተሰጠው ምላሽ ይህችን የቁርአን አንቀጽ በመጥቀስ ነበር :- "فَلَمْ تَقْتُلُوهُمْ وَلَٰكِنَّ ٱللَّهَ قَتَلَهُمْ ۚ وَمَا رَمَيْتَ إِذْ رَمَيْتَ وَلَٰكِنَّ ٱللَّهَ رَمَىٰ ۚ " / الأنفال:١٩/ "አልገደላችኋቸውም ግን አላህ ገደላቸው፡፡ (ጭብጥን ዐፈር) በወረወርክም ጊዜ አንተ አልወረወርክም፡፡ ግን አላህ ወረወረ (ወደ ዓይኖቻቸው አደረሰው)፡፡ " /አል አንፋል:19/ ዑመር አልሙኽታር ጀግንነት ሲደመር ጽኑ ኢማን እና ተወኩል የእውነተኛ ሙስሊም መገለጫ መሆኑን በተጨባጭ ያስመሰከሩ ተላቅ ሰው ነበሩ።-ረሂመሁላህ- ምንጭ: - 1- الأشهب ،عمر المختار 2- الصلابي، عمر المختار نشأته أعماله واستشهاده 🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 #share #ሼር #join Https://t.me/smithhk

🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 ከጠቢባን አንደበት 〰〰〰〰〰 🔜 « የአንተ መስተካከያና መታነጫ ዛሬ እንጅ ነገማ የፍፃሜህ ዕለት ሊሆን ይችላል ። » 🔜 « ራስህን ድል ሳታደርግ በሌላው ላይ አትዝመት ።» 🔜 « መታገስ ለራስ ጊዜ መስጠት ነው ። » 🔜 « ንደት ለችግሮች መፍትሔ ሳይሆን መንስኤ ነው ። » 🔜 « የውሸት እየኖርን የእውነት እንሞታለን ። » 🔜 « ደስታ ዱርዬ አይደለም ፤ ሰዎች ግን ዱርዬ እየመሰላቸው በየ መጠጥ ቤቱ ይፈልጉታል ። » 🔜 « ጠላቶችህን ባትወዳቸው እንኳን አድንቃቸው ፤ ስህተትህን ለመመልከት የመጀመሪያዎቹ ናቸውና ። » 🔜 « ጠላቶችህ ወደ አንተ ቢገሰግሱ ወደ ኋላ አታፈግፍግ ወደነሱም አትንደርደር ባለህበት ሆነህ ተዘጋጅና ጠብቃቸው ። » 🔜 « ብዙ ሰዎች ከአድማስ ማዶ የማይታያቸውን ቀን ይናፍቃሉ ። ዛሬን የሚንቋት በእጃቸው ስለገባች ነው ። » 🔜 « ዘልዓለም ለመኖር ዕድሉ ለሌላት ህይወትህ ሰላምን አትንፈጋት ። » 🔜 « ለሌሎች ይቅርታ የማያደርግ እራሱ የሚሸጋገርበትን ድልድይ የሚያፈርስ ነው ። » 🔜 « ቁጠኛ ጓደኛ የተረጋጋ ጠላት ነው ። » 🔜 « የቁጣ መድሀኒት ዝምታ ነው ። » 🔜 « ከመዝለልህ በፊት አስተውል ። » 🔜 « ገንዘብ መናገር ሲጀምር እውነት ዝም ትላለች ። » 🔜 « ትዕግስት ማለት ችግርህን ለአሏህ መንገር ማለት ነው ። » 🔜 « እምነት ማለት ግማሹ ትዕግስት ሲሆን ግማሹ ምስጋና ነው ። 🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀🌸🥀 #share #ሼር #join Https://t.me/smithhk

የመስጂድ ሚንበሮች ስለኛ ተርገፈገፉ። ዓለም ዓቀፍ ዳዒዎች ደም ስራቸው ተገታትሮ በቁጭት ስለሐበሻ ሙስሊሞች ለፈፉ። ከታዋቂው ዳዒ መህሙድ አልሀሰናት እስከ ጀምስ ሁሉም ልሳናቸው ስለኢትዮጵያ ሆነ። "ወንድሞቻችሁ መስጂዶቻቸው ፈርሰውባቸው በመርዛማ ኬሚካል ጥይት ተመተው ከመሬት ተዘረሩ" እያሉ እንባ ተናነቃቸው። ጅማታቸው ተገታትሮ ንዴትና ቁጭት ልባቸውን ደለቃቸው። ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ያሉ ታዋቂ ሰዎች በአካልም ሆነ በጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ለማያውቁን ለኛ እሳት ጎርሰው እሳት ልሰው ስለመደፈራችን አነቡልን። አዎ ከጀሰዲን ዋሂድ ይሉሀል ይህ ነው። አንደኛው አካል ሲታመም መላው የሰውነት ክፍል በትኩሳትና በእንቅልፍ እጦት ይሰቃያል። የሆነውም ይህ ነው። በአስፈሪ ጥይት እሩምታ መሀል በሞት አፋፍ ላይ አይተውት ጥለውት ሳይሸሹ ከወደቀበት አንስተው ሸሃዳ በል እያሉ የሚያስታውሱ ወንድሞች የጀሰዲን ዋሂድ አስኳሎች ነበሩ። አላህ አንድነታችንን ያጠንክርልን Https/t.me//smithhk

"አቧራ የነካው ልብሴ አላህ ዘንድ ምስክር ይሆነኝ ዘንድ ሳላራግፍ አጣጥፌ ከቁምሳጥኔ አኖረዋለሁ" ጌታዬ ሆይ! ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑልወሊድ ሠይፍ የሰላ አድርግልኝ Mahi Mahisho ስካቫተሩ በፀጥታ ኃይሎች ታጅቦ ከመስጂዱ ፊት ለፊት ቆሟል። ህዝቡ ጥጋ ጥጉን ይዞ ይታዘባል። መዳፋቸውን አፋቸው ላይ በሻርብ ሸፍነው በሀዘን የምፀት ድምፃቸውን የሚያሰሙ እናቶች ይስተዋላሉ። "አይ ጊዜ ...." እያሉ ያላዝናሉ። ብሶት፣ ቁጭት፣ መገፋት፣ ህመምና ብቸኝነት ከፊቶች ላይ ይነበባሉ። ክስተቱን በዓይን መመልከት በእጅጉ ያማል ውስጥን እየናጠ ሐዘንን ያላብሳል። በስሜት አጡዞ የሚሆኑትን ያሳጣል ይህን የውርደት ጥግ ከማየት ፊትን ዘወር አሊያም በለቅሶ ቦታውን ለቆ መሄድ ይሻላል ብዬ ብዞር ከኋላዬ ከዘራቸውን ተደግፈው የቆሙት አዛውንት በድንገት ትኩረቴን ሳቡት። ፀጉራቸው ሸብቶ ግንባራቸው ተሸብሽቧል። ከአንድ ፖሊስ ጋር ግብ ግብ ፈጥረው ሲገፈትራቸው ወድቀው ልብሳቸው አቧራ ቅሟል። ከዓይናቸው ዕንባ ኩልል ብሎ ይፈሳል። ድክም ባለ ጉልበታቸው ከዘራቸውን ተደግፈው ከፍርስራሹ ጥግ አረፍ አሉ። እኔም ከጎናቸው ተቀመጥኩ። በተሰበረ ልብ አንገታቸውን ወደመሬት አቀረቀሩ። ዓይናችን እንባ እንዳቀረረ እርስ በርስ ተያየን "ሙስሊሞች ከአንደሉስ ተባረው መስጂዶች ወደ ቤተክርስቲያንነት የመቀየራቸውን ታሪክ ሰምተህ ይሆን?" አሉኝና ወደሰማዩ አንጋጠጡ። እንባ ባደበዘዘው እይታ ሰማዩን እየቃኘሁ የተሰማኝን ሁሉ አወራሁ። ታሪኮችን ከወቅቱ ጋር እያዋጀሁ የሙስሊሞችን ሁኔታ አወጋሁ። ከእስልምናው ስንርቅ አላህ ፍርሀትን በልባችን አንግሶ በተታሮች እንዴት እንደቀጣን አስታወስኩ "በወቅቱ የዓባሲያው ኸሊፋ የሙስሊሙን ኡማ ችግር ከመቅረፍ ይልቅ በጥቅማጥቅም ተጠምደው የየራሳቸውን ስልጣን ኃብትና ዝና ክብርና ስም ለማስጠበቅ እርስ በርስ የሚናቆሩ ስለነበሩ የሙስሊሙን ኡማ ኃይልና ክብር አዳክመው በሆድ ውስጥ ያለ ሽል ሳይቀር በጩቤ እየተሞሸለቀ ሲገደል ግድ አይሰጣቸውም ነበር ልክ እንደዛሬው" አልኳቸው። እንግዲያውስ አንድ ታሪክ ልጨምርልህ በማለት ንግግራቸውን ጀመሩ። በዕንባ የራሰውን ዓይናቸውን እየጠረጉ ታላቁ ሙአሪኽ ኢብኑ ከሲር አልቢዳያ ወንኒሀያ በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ትርክቱን እንዲህ ዘግበውታል "የኢስላም ጠላቶች ባግዳድን ከበው በቀስት እያስወነጨፉ ባለበት ወቅት አንድ ቀስት በመስኮት በኩል ሾልኮ እየደነሰች ኸሊፋውን በማዝናናት ላይ የነበረችን ዐረፋ የተባለች ሴት ባሪያን ገደለ" አሉኝና ተከዙ። ከዚያም አስከትለው ለምን እንደመጣሁ ልንገርህ አሉኝ። ለማወቅ በእጅጉ እየጓጓሁ አይኖቼን አፈጠጥኩ። "ወደዚህ ቦታ ያመጣኝን ታሪክ ላካፍልህ አሉኝ አቀማመጣቸውን እያስተካከሉ "ከቀድሞ ደጋግ ሰዎች መካከል አንዱ በግዞት ተጠፍረው በታሰሩበት እስር ቤት ውስጥ የአዛንን ድምፅ ሲሰሙ ወደ እስር ቤቱ በር ይራመዳሉ። ጠባቂው በያዘው ዱላ ቸብ አድርጎ ሲመልሳቸው ጌታዬ ሆይ! ለአዛን ጥሪህ ምላሽ ሰጥቼ ከጀመዓ ሰላት መሐል እንዳልጣድ በአንባገነኖች ተከልክያለሁ። ከቤትህ ለመገኘት የአቅሜን ጥሬያለሁ የቻልኩትን አድርጌያለሁ ምስክር ሁነኝ እያሉ ክፍላቸው ገብተው ለብቻቸው ይሰግዳሉ። ይህ የሁልጊዜ ተግባራቸው ነው። እኔም ዛሬ እዚህ ተገኝቼ ለምን ታፈርሳላችሁ መስጂዳችን ህልውናችን ናቸው ብዬ ስጠይቅ በያዙት ዱላ እየገረፉ ገና ምን አይተህ እያሉ ሲገፈትሩም ከመሬቱ ወደቅኩ ጌታዬ ሆይ! መስጂድህ እንዳይፈርስ የአቅሜን ታግያለሁ ምስክር ሁነኝ እያልኩ ለአላህ ተናገርኩ። አቧራ የነካው ልብሴ አላህ ዘንድ ምስክር ይሆነኝ ዘንድ ሳላራግፍ አጣጥፌ ከቁምሳጥኔ አኖረዋለሁ" አሉኝና እጃቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው "ያፈረሱትን ሁሉ አፍርሳቸው" እያሉ ዱዓ ሲያደርጉ እኔም በሁኔታው እየተገረምኩ "አሚን" እልኩ..... እንደ ሁኔታው ይቀጥላል

ተወዳጁ ቃሪዕ ዓፊፍ ሙሀመድ ታጅ ዛሬ(08/08/15) በተቅዋ መስጂድ የተራዊህ ሰላትን ያሰግዳል።
ተወዳጁ ቃሪዕ ዓፊፍ ሙሀመድ ታጅ ዛሬ(08/08/15) በተቅዋ መስጂድ የተራዊህ ሰላትን ያሰግዳል።

📚 كتاب رياض الصّالحين للإمام أبي زكريا يحي بن شرف النووي الدّمشقي «رحمه الله تعالى» 📚ኪታብ ሪያዱ አስ-ሷሊሂን የኢማም አቢ ዘከሪያ የህያ ቢን ሸረፍ አን-ነወዊይ አድ-ዲመሽቂይ «ረሒመሁሏህ» ◀ الدرس الثّاني ▶ ክፍል 2 🎙 الشيخ أول بن أحمد الخميسي «حفظه الله» 🎙 በሸይኽ አወል አህመድ አል ከሚሴ «ሐፊዘሁሏህ» #share #ሼር #Join Https://t.me/smithhk

📌درس كتاب جــديـــد 📌 አዲስ የኪታብ ደርስ 📚 كتاب رياض الصّالحين للإمام أبي زكريا يحي بن شرف النووي الدّمشقي «رحمه الله تعالى» 📚ኪታብ ሪያዱ አስ-ሷሊሂን የኢማም አቢ ዘከሪያ የህያ ቢን ሸረፍ አን-ነወዊይ አድ-ዲመሽቂይ «ረሒመሁሏህ» ◀ الدرس الأول ▶ ክፍል 1 🎙 الشيخ أول بن أحمد الخميسي «حفظه الله» 🎙 በሸይኽ አወል አህመድ አል ከሚሴ #share #ሼር #Join Https://t.me/smithhk

photo content

ረመዳን ሙባረክ ይቅርታ! በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አሊያም በቸልተኝነት፣ በድርጊት ፣በምግባር ወይንም በቃላት ያስቀየምኳችሁ ካላችሁ ሁላችሁንም ይቅርታ እጠይቃለሁ። አፈይቱ' ሊላህ። የአላህን ፀጋ ምህረትና በረከት የምናገኝበት የረመዳን የፆም ወር እንዲሆንልን እመኛለሁ "ረመዳን ሙባረክ"  ☪❤❤

እርግጥ ነው የረመዳን ወር ሲገባ እመስጂዶች ላይ አዳዲስ ፊቶች ለጀመዐ ሰላተረ ይመጣሉ። ግና በአላህ! ረመዳን መጣላቹ እያልን አናሸማቅቃቸው። ሰንቀዋት የመጡትን ተስፋቸውን አንቀማቸው። አንግበው የመ
እርግጥ ነው የረመዳን ወር ሲገባ እመስጂዶች ላይ አዳዲስ ፊቶች ለጀመዐ ሰላተረ ይመጣሉ። ግና በአላህ! ረመዳን መጣላቹ እያልን አናሸማቅቃቸው። ሰንቀዋት የመጡትን ተስፋቸውን አንቀማቸው። አንግበው የመጡትን ሞራላቸውንም አንከሽክሽባቸው።    መልካም ፈገግታ ሰደቃ ነውና ፈገግ ብለን እንቀበላቸው። አህለን ወመርሃበን ፤ እንኳን ደህና መጣቹልን የአላህ ቤት እናንተን ናፍቃ ነበር ብለን እንቀፋቸው። ከምን አይነት ኸይር ነገር እርቀን ነበር ብለው እስኪሰማቸው ድረስ እናቅርባቸው።    በፍቅር ተንከባክበን መስጂድ ውስጥ ያለውን ሰላም፣ ፍቅር እና ደስታ እንዲያወቁ ያረግን ጊዜ ፤ መስጅድ ለመምጣት ረመዳንን አይጠባበቁም ፤ አወለ ሰፍ ሙአዚኑን ቀድመው የሚገኙ ቢሆን እንጂ። ከሁሉም በላይ አላህ አዋቂ ነው። ✍ አቡ ዑመይር