Nathan casting agency
Open in Telegram
The best place to get the best casting jobs Our services -casting models - for music clips - movies - series dramas - fashion shows - television shows Contact: 0920358051
Show moreEthiopia16 170The category is not specified
408
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#በቀል
#ክፍል 4
.
.
.
.
👇👇👇✍✍✍👇👇👇
ከለሊቱ 11 ሰአት ላይ ከመኝታዬ ተነስቼ እማዬን ተሰናበትኩና ወደ መነሃሪያ አመራሁ።...ከጅማ ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ በዝግጅት ላይ ያሉትን ባሶች ቃኘት ቃኘት አደረግኩና የጎን ቁጥር 45 ተብሎ የተለጠፈበት ባስ ላይ ተሳፈርኩ......አዎ ጅማን ለቅቄ እየወጣሁ ነው....ያን አረመኔ ላገኘው...አግኝቼውም ተንከትክቼ ልሥቅበት....እኔን ካላባት..እናቴን ካለ ባልና ልጅ እንድትኖር ያደረጋትን አውሬው መኩሪያውን አግኝቼው ቅጣቱን እራሤው ልሰጠው እየሄድኩለት ነው።.... የጅማ ገጠራማው ክፍል ላይ ደርሻለሁ......ብዙ ሀሣቦችን በውሥጤ እያመላለሥኩ ድንገት አይኔ ከመንገዱ ባሸገር ከርቀት ከሚታዩት በዳብና እና ሽነንጌቤ የተባሉ ድንቅ የተፈጥሮ ስራዎች ላይ አረፈ።.....በዳብና የተሰኘው ጥቅጥቅ ያለ የቡና ማሳ ሲሆን
ይሄው ጫካ ለብዙ ዘራፊዎችና ወንበዴዎች ምሽግና ከለላ ነው.... ለተጓዦች ደግሞ አንዳዴ ስጋት ሌላ ግዜ ደግሞ ኩራት ነው..... ሰለ ሽነንጌቤ ብዙ ማለት አይጠበቅብኝም ምክንያቱም ብዙ አርቲሥቶች አቀንቅነውላታል... ጥቀስ ካላችሁኝ አንጋፋውና የሙዚቃ አባት ተደርጎ የሚወሰደው ጥላሁን ገሰስ እንዲሁም ጌቱ፣ነፊሳ፣አጫሉና የመሳሰሉት ጥቂቶቹ ናቸው።.....
ብዙ የፊልም ዳይሬክተሮች እራሱ ለፊልማቸው ውበትና ድምቀት የሚመርጧት ቦታ ነች ...ውስጥ ውስጧን ላያትማ ከጅማ ንቅንቅ አልልም ማለቱ አይቀሬ ነው....
የጌንቤን ፏፏቴ ያየ በመደመም ውሥጥ ሆኖ አቤት የፈጣሪ ሥራው በማለት አፉን መያዙ አይቀርም....
ብዙ ማለት ይቻላል እንደው በደፈናው የሀገራችን ዋና ሀብት የሆነው ቡና መገኛ በመሆኗ የውጭ ምንዛሬ ምንጫችን ናት።......
እየራቅን ስንሄድ ሁለቱም የጅማ ውብ ጫካዎች ከአይኔ እየደበዘዙና እየጠፉ ሄዱ ..እኔም ወደ እራሴ ተመለሥኩ ..መኩሪያውን እንዴት እንደምደመስሰው እያሠላሠልኩ ጀምበር ለማንቀላፋት እየዳዳት ልትጠልቅ ሥትል አዲሥ አበባ ገባሁ....ወደ አራዳዎቹ አገር ሸገር ከተምኩ።.......
ሳይመሽብኝ ትንሽም ቢሆን ወደ ማውቀው ሠፈር ፒያሳ ጎራ አልኩ....እንዳቅሜ አልጋ ያዝኩና ጎኔን አሳረፍኩት..የሚረብሸኝን አእምሮዬንና የማያልቁ ግትልትል ሃሣቦቼን ግን ማሣረፍ አልቻልኩም።......ብቻዬን ማውራት ጀመርኩ..ጠያቂው እራሴ መላሹም እራሴው.....
እዚህ ሠፊ ሀገር ላይ እንዴት ነው ፈልጌ የማገኘው......?
ስለሱ ምንም የተሟላ መረጃ የለኝም በእርግጥ አዲሥ አበባ እንደሚኖርና ከአባቴ ጋር አብረው የተነሡትን ጥቂት ፎቶዎች ይዣለሁ....
ባገኘውሥ ምንድነው የማረገው ልግደለው?
የለም ሞትማ ለሱ እረፍት ነው....ምድር ላይ እያለ እንዲሠቃይ ነው የማረገው።.....ለእያንዳንዷ ለሠራት ግፍ በህይወት እያለ መክፈል አለበት...አባቴ ላቡን ጠፍ አርጎ ያካበተውን ንብረት ከእጁ ፈልቅቄ እወሥድበታለሁ።........
አዎ እሡ ብዙ ሀብት ሥላለው በብዙ ጠባቂዎች ተከቦ ይሆናል የሚኖረው ግን አያቅተኝም......አንተ ጨካኝ አረመኔ ልክህን ታገኛለህ ያውም በቅርቡ..ክፍሏን በጩኸት አናጋዋት....ሠውነቴ በላብ ተዘፈቀ...መንዘፍዘፍ ጀመርኩ።...ስለ መኩሪያው ሣሥብ እንዲህ ያረገኛል...መላ አካሌ ከቁጥጥሬ ውጪ ይሆናል።......ለጊዜውም ቢሆን ከጭንቀቴ ለመገላገል ወደ ውጭ ወጥቼ መራመድ ጀመርኩ ጥቂት እንደተጓዝኩ የመሽታ ቤቶች አየሁ.....ፒያሣ እንግዲህ በማታ እንደምትደምቅ የማይካድ ሀቅ ነው......የሚጨፍርና የሚደንሥ ይበዛል.....በኤሌትሪክ መብራት ላይ የሚንጠላጠሉት ወፎች ሣይቀሩ ላባቸውን እያማቱ የሚጨፍሩ ይመሥለኛል።....
እኔም እዚያ ክፍል ውሥጥ ብቻዬን በሃሣብ ከምፈነዳ ብዬ አንድ ሁለት ልል ደመቅመቅ ወዳለበት ገባሁ....ከለር እየቀያየረ ከሙዚቃው ምት ጋር እኩል የሚንቦገቦገው መብራት አይኔን ወጋኝ....ለጊዜው አይኔን ቢያስጨፍነኝም እየቆየሁ ለመድኩት።..ጥግ ላይ ተቀምጬ ቢራዬን እየተጎነጨሁ ሠውን መቃኘት ጀመርኩ....የሠከረው...ሞቅ ያለው ሁሉም ያብዳል....በሚችለው የጭፈራ ሥልት እየተነሣ ይውረገረጋል።...ሴተኛ አዳሪዎች ገንዘብ ያላቸውን ያባብላሉ.....ብጣቂ ልብሥ ገላቸው ላይ ጣል አርገው በመጠጥ የናወዙ ወንዶችን ያማልላሉ እውነት ለመናገር አለባበሣቸው ባጠጣም ያሣሥተሃል....ታዲያ ይህን ሁሉ የሴትና ወንድ ትርምሥ እየተመለከትኩ ሳለ የሁለት ሠዎች ማለትም የገዢና ተገዢ ጭቅጭቅ ትኩረቴን ሳበው......
ሠውዬው "እሺ ቆንጂት ለአዳር ሥንት ታሥከፍይኛለሽ....?"
ልጅቷ በቅጽበት ጥምጥም አለችበትና ጉንጩን የመዳበሥ ያህል እየሣመችው" 500 ውረድ አሪፍ ምሽት እንድታሣልፍ እረዳሃለሁ የኔ ቆንጆ"...አለችው
ሠውዬው ከአንገቱ ላይ እጇን መንትፎ አላቀቃትና"ለነገ ጠዋት አንድ ወንድ ልጅ ካደረሽልኝ እከፍልሻለሁ" ..
ከት ብላ ሣቀችና" ምን ማለት ነው.....?"
"ደግሞ ትሥቂያለሽ እናንተ የዘመኑ ሸርሙጦች የብልታችሁ ጸጉር ባደገና ባጎፈረ ቁጥር የበግ ጸጉር እየመሠላችሁ የበግ ዋጋ ትጠራላችሁ"....ብሏት እጁን እያወራጨ ጥሏት ሄደ.....
በዚህ ንግግሩ የተበሳጨች የምትመሥለው ልጅቷም እሥከ መውጫው ተከትላው"አንተ ችጋራም በዶላር ያልኩህ መሠለህ ውዳቂ" አለችውና ተመልሳ የጀመረችውን ቢራ ሻት ሻት ማድረግ ጀመረች....እኔም ትንሽ እሥክትረጋጋ ጠበቅኳትና አሥጠራዋት......እንደመጣች ወዬ የኔ ቆንጆ ብላ ታፋዬ ላይ ተቀመጠችና በግብዳው ቂጧ እንትኔን አሸት አሸት አደረገችው ሠውነቴ ተነቃቃብኝ...ሞተሬ ሣይነሣ በፊት ለፊት ያለው ወንበር ላይ ተቀመጪ አልኳትና ምልክት አሣየዋት.....ከደቂቃዎች በፊት የነበረው ብሥጭቷና ንዴቷ ጠፍቶ ፍጹም ሌላ ሠው መሆኗ አሥደንቆኛል...ለነገሩ ወደው አይደለም የሥራው ባህሪ ነው....ብዙዎቹ ወደዚህ ሥራ ፈልገው እንደማይገቡ አውቃለሁ እረ ምን ማወቅ ብቻ እውነትም ነው እንጂ መቼሥ ፈልጎት ክብሩን የሚያረክስ አይኖርም....ፈልጋው በወንድ እየተንቋሸሸችና እየተሠደበች በደሥታ የምትሠራ የለችም...ብር ሥለከፈላት ብቻ እንደ ባሪያ እንደፈለገ እንዲያሰቃያት የምትፈቅደው ወዳ አይደለም አማራጭ በማጣቷ ቢሆን እንጂ.......
"እሺ ቆንጆ ምን ይምጣልሽ"
"ሊዘንብብኝ ነዋ.. ቢራ ይምጣልኝ"
"ጀለሴ አዳር ወይሥ ሾርት ነው የፈለከው......?"
"አዳር ነው።......የምትፈልጊውን ዋጋ እከፍልሻለሁ".....
"ይመችህ ጀለሴ እንግዲያውሥ የዛሬው ልኡሌ አንተ ብቻ ነህ...እንደፈግክ ስታንገላታው ታድራለህ"
"ስምሽ ማነው......?"
ኩሥትርትር አለችብኝ "ሠውዬው መርማሪ መርማሪ ያጫውትሃል ልበል.. የፈለከኝ ሥለቀነዘረብህ ነው እኔ ደግሞ አብርጄልህ እንለያየለን አለቀ ሌላ ጥያቄ አልፈልግም".....
ከዚህ በላይ ላናዳት ሥላልፈለኩ ምንም አይነት ጥያቄ ሥለራሷ አላነሣሁባትም።.....
እኩለ ለሊት ላይ ተያይዘን አልጋ ወደ ያዝኩበት አመራን....ክፍሌ ደርሼ መብራቱን እንዳበራሁት ጭፈራ ቤት በሚንቦገቦገው ዲም ላይት ምክንያት ያላሥተዋልኩት ውበቷ ፍክት ብሎ ታየኝ.....አቤት ዋጥ ማድረግ ነበር ታሥብላለች....እድሜዋ ወደ 24 ገደማ ቢጠጋ ነው....ሲበዛ ቀይ ናት....አካላዊ ቁመናዋ አይነገርም በጣም ታምራለች...ረዘም የሚለውን ጸጉሯን በአንገቷ ዙሪያ ሥለነሠነሠችው የበለጠ ውበቷን አጉልቶታል።.....
"አንዴ መታጠቢያ ቤት ደርሼ ልምጣ"....ብላኝ ሄደች
እኔም በመጠጥ የዛላ ሠውነቴን ለማሣረፍ በጀርባዬ ዘፍ ብዬ ወደቅኩ አልጋው መሸም አቅቶት ሲጢጥ የሚል ድ
ጋሁት።....ግን ምን ሊረባ የኔ ጩኸት ቤተሠቤን አይመልሥልኝ.....አባቴ ላይመለሥ ሄዷል እናቴ ደግሞ በደረሠባት የጉሮሮ ማበጥ ምክንያት ህክምና ላይ ነች።............
አዎ ዶክተሩ ከእናቴ ክፍል ከታካሚው ጋር የነበረውን ግዳጅ ጨርሶ እየወጣ ነው.......
"ዶክተር እናቴ እንዴት ናት.....?"
"አታሥብ ደህና ናት.....መርዛማ መድሃኒት ተጠቅማ ነው...ትንሽ ዘግይታ ቢሆን መናገር አትችልም ነበር....አሁን ያው የበፊቱ ድምጿ ባይመለሥም በመጠኑም ቢሆን ትናገራለች....አይዞህ በርታ" ብሎኝ ሄደ።........
ህልም በሚመሥል መልኩ እናቴን ለሁለት አንቀውና ይዘው ሲይግቷት የነበረው ጠብታ የሚመሥል ነገር ብልጭ አለብኝ........
//////********//////////
ከሣምንታት በሁዋላ እናቴ አገገመችና ወደ ቤት ተመለሥን.....እናቴ መናገር መቻሏን የሠማው መኩሪያው ስልክ ደውሎ በእኔ በአንድ ልጇ ሥላሥፈራራት ለማንም ትንፍሽ አላልንም።..............ያ ደሥታ የተሞላበት ቤተሠብ ባንድ ጊዜ ፈራርሶ ወደመ.........ሙሉ ንብረታችንን አጣን...የቀረልን
በእናቴ ስም የነበረው 5 ሚሊዬን ብርና ቤታችን ብቻ ነው.........ቤቱን ብንገባበትም ገንዘቡን ምክንያቱን ባላወቅነው መንገድ ባንክ ስለያዘብን ነው እንግዲህ በዚያ በጨቅላ እድሜዬ እናቴንና እኔን ለማኖር መንገድ ላይ ወጥቼ ሊስትሮ ለመስራትና ጥቃቅን ነገሮችን ለመሸጥ የተገደድኩት።........
ጊዜው ሄዶና ነጉዶ ዛሬ ላይ ደርሠናል...............ጠንካራ የወጣትነት ጊዜዬ ላይ ደርሻለሁ። አዎ ይሄን አረመኔ ለማጥፋት ጊዜዬ አሁን ነው ለዚህም ብዬ እንዲረዳኝ በቂ ገንዘብ አጠራቅሚያለሁ በዚያ ላይ ባንክ ያገደብንን 5 ሚሊዮን ብር እሳት የላሠ ጠበቃ ቀጥሬ ባንኩን በመክሰስ ከነካሳው ጭምር እጥፍ አድርጌ ተቀብያቸዋለሁ።....አረመኔው መኩሪያው አዲስ አበባ ከትሞ ተንደላቆ እየኖረ እንደሆነም ደርሼበታለሁ......
አዎ ከሁለት ቀን በሁላ ለመሄድ ዝግጅቴን ጨርሻለሁ ችግሩ ግን እናቴን ማሣመኑ ላይ ነው......ቢሆንም ቁርሥ ላይ ልነግራት ቆርጫለሁ።.....
እናቴ ያፈላሁላትን ቡና ከአልጋዋ ሣትወርድ አጣጥማ ከጠጣች በሁዋላ ቁርሥ ወደ ቀረበበት ማእድ አመራን.......እንዴት እንደምጀምርላት እያብሠለሠልኩ ምግቡን ችላ አልኩት...ጨርሶኑም ረሣሁት።....ይሄን የታዘበችው እናቴ"እዮቤ ምንድነው የምታሥበው አትበላም እንዴ"..አለችኝ
"አይ እማ የሆነ ነገር ልነግርሽ ነበር.."
"ምንድነው......?ንገረኝ".....
"ምን መሠለሽ ከምሠራበት ድርጅት የትምህርት እድል መጣልኝ....ለመማር ደግሞ አዲሥ አበባ ዩንቨርሥቲ የግድ መሄድ አለብኝ...ይሄን እድል ሥመኘው የነበረው ቢሆንም አንቺን ጥሎ ለጥቂት አመታት መቆየት ጨነቀኝ".....እናቴ እንዲህ ሥላት ፊቷ ቅጭም አለ........
"እዮቤ ለኔ አንተ ብቻ ነህ ያለኸኝ....ሆዴ ቢባብኝም አንጀቴ ቢላወስብኝም እኔው ጋር አሥሬህ እድሎችህን ላበላሽና ወጣትነትህን ላኮላሸው አልፈልግም..እሥከዛሬም እኔን ብለህ የታሠርከው ይበቃሀል...ግን መጥፎ ነገር እንደማይፈጠር ቃል ግባልኝ"......
"እሺ እማ እንድትኮሪብኝ አደርግሻለሁ".....ተቃቅፈን ተላቀስን.......
ይቀጥላል
#በቀል
#ክፍል
.
.
.
👇👇👇👇✍✍✍👇👇👇
ካካካካካካካካካካካካ የሆነ ሠው ከት ብሎ ይሥቃል....ወደ በሩ ሥጠጋ የአባቴን ድምጽ ሠማሁት.."ልቀቃት አንተ ከሃዲ ልቀቃት" ይላል..
ድምጽ ሣላሠማ መሬቱን የመንካት ያህል ተጠንቅቄ በፊት ጣቶቼ እየረገጥኩ ወደ ፊት ተጠጋሁና ትርኢቱን ማየት ጀመርኩ....አዎ ሶስት ሽጉጥ የታጠቁ ሠዎች ይታዩኛል....ሁሉም ጥቁር የእጅ ጓንት አጥልቀዋል።..እናቴ አልጋው ላይ ተዘርራ እጆቿና እግሮቿ በገመድ ከአልጋው ጋር ተጠፍንገዋል....አባቴ ደግሞ ወንበር ላይ የፍጥኝ ታሥሯል።.....
"እሺ ወ/ሮ የሺወርቅ አሥታወሽኝ....?"አቶ መኩሪያው ነበር የተናገረው....
"አንተ የበላህበትን ወንጭት ሠባሪ ሠው ባደረግንህ ምን በደልንህና ነው እንዲህ የምታረገን"....
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ ከትከት ብሎ ሳቀና "በደል ትያለሽ...
እኔኮ ያ ሠው ነኝ አንቺን በማፍቀሬ የተሣቀብኝ....እኔኮ ያ ሠው ነኝ አትመጥነኝም አልፈልግህም ብለሽ ያባረርሽኝ.....እኔኮ ያ ሰው ነኝ መጀመሪያ ታጠብ ያላችሁኝ"....
የእልህ ሳቅ ሳቀና እናቴ ላይ ተከመረባት አንገቷን በወፍራም እጆቹ አነቃት...እናቴም ሁለት እግሮቿን ከወዲያ ወዲህ አንፈራገጠቻቸው........ይሄን ሳይ "እማ" የሚል ቃል ከአፌ አመለጠኝ ሁሉም እኔ ወዳለሁበት በር ፊታቸውን አዞሩ....መኩሪያውም እናቴን ለቀቃትና
"ምን ትጠብቃላችሁ ሠው ካለ አጣሩ እንጂ" አላቸው......
ሁለት የሚያስፈሩ ጠብደል ሰዎች እርምጃቸውን አሥፍተውና ሽጉጣቸውን ቀሥረው ወደ እኔ ቀረቡ....የሞት ሞቴን ሩጬ የልብስ ቁም ሳጥን ውሥጥ ገባሁ....የሚያደርጉትን በሙሉ በቀዳዳ እየተመለከትኩ ነው..ቤቱን አተረማመሱት እያንዳንዱን እቃ እያነሡ በረበሩት።..
"ስማ እሥቲ የልብስ ቁም ሳጥኑን ፈትሸው" አለው አንደኛው ግብዳ ሠውዬ....
"እያሰብኩት ነበር ልክ ነህ"አለና ወደ ቁም ሳጥኑ መራመድ ጀመረ....እየመጣ መሆኑን ሳይ ልብሶቹ ውሥጥ ተወሸቅኩና እራሴን ለመከለል ሞከርኩ...አዎ ኮቴው እየቀረበኝ ነው...እንደምያዝ እርግጠኛ ሆንኩ።
መዝጊያውን በጥንቃቄ ቀስ አርጎ እየከፈተው ሳለ ግን "ሚያው" የሚል ድምጽ ከሌላ ክፍል ተሰማ....ተንደርድረው ድምፅ ወደሰሙበት ሲያመሩ ቡራቡሬዋ ድመቴ ነች....ያለ ርህራሄ ድምጽ ማፈኛ ባለው ኮልት ሽጉጣቸው ደረቷ ላይ ተኩሰው ገደሏትና ምንም እንዳልተፈጠረ እየተሳሳቁ ወደ መጡበት ተመለሡ"አለቃ ሁሉንም በርብረናል ምንም የለም....የድመት ድምጽ ነው የሠማነው"...አሉት
"ዌል እንግዲህ ካቆምንበት እንቀጥላ ወ/ሮ የሺ ወርቅ" አላት ፌዝ በተሞላበት ድምጽ.....
"ቆይ አንተ ማን ነህ....? ምንድነው ከኛ የምትፈልገው.....?" አለችው በምሬት
"እኔ ማለት ላንቺ የሚሠማኝን ሥሜት ወረቀት ላይ እያሠፈርኩ ሳልታክትና በዝምታሽ ሳልከፋ ለረጅም ጊዜ ደብዳቤ ሥልክልሽ የኖርኩት ያንቺው የልብ ወዳጅሽ ነኝ....አሁን አወቅሽኝ ወ/ሮ የሺ ወርቅ....?በህይወት ምን ያህል ተሥፋ እንደቆረጥኩ ይታይሻል....? መኖር ባንገሸገሸኝ ጊዜ....ለሠው ልጅ ያለኝ ጥላቻ ተራራ በሚንድበት ወቅት አንቺን አፈቀርኩ....ሁሉን ነገር ትቼ አንቺን ብቻ ማሠብ ጀመርኩ ግና አንቺም ያው ነበርሽ እንደሌላው ሁሉ ገፋሽኝ...ከዚያም ሀብታም ባል አገባሽ አይደል ሃሃሃሃሃሃሃሃ"..ከትከት ብሎ ሣቀ
"አንተ ነህ ማለት ነው ጊዜ ጠብቀህ በቀልህን ልትፈጽም ሚስኪን መስለህ የቀረብከን...አንተ የበግ ለምድ የለበስክ ተኩላ.....ልክ ነህ ችግርህ ከኔ ጋር ነው ስለዚህ እኔን እንደፈለክ አርገኝ ባለቤቴን ልቀቀው"....አለችው የአቅሟን ጮኽ ብላ..
"አይ አንቺ.....ጨዋታ ትችይበታለሽ....አንቺንማ አልገልሽም ገና ብዙ ድራማ ማየት አለብሽ........ለመሆኑ ያቺ ቀጫጫና ሞልቃቃ ጓደኛሽ የት እንዳለች ታውቂያለሽ......?"
"እሷን እዚህ ውሥጥ አታሥገባት"
"ያቺ ከንቱ ጓደኛሽ ባሌ ነው ያለችው....ይገርምሻል አንድ ወጠምሻ አግብታለች።....ባለቤቷ ለሥራ ወደ አዲስ አበባ ወጣ ሥላለ የኔ ሠዎች እንዳይደብራት ብለው እያጫወቷት ነው"
"ቆይ ይሄን ሁሉ እንዴት አወቅህ......?"
"ብር ነዋ....ገንዘብ ካለ በሠማይ መንገድ አለ ሲባል አልሰማሽም....እራሳችሁ ውድቀታችሁን ሥታፋጥኑ ድርጅቱ ውሥጥ አለ የተባለ ቦታ ሰጣችሁኝ....እኔ ደግሞ ብሩን መዘበርኩትና ለበቀሌ ተጠቀምኩበት..ሃሃሃሃሃሃሃሃ.... ቆይ እንዲያውም የልጅነት ጓደኛሽን ድምጽ ላሠማሽ ምናልባት ናፍቃሽ ይሆናል" አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለ...ላውድ ሥፒከር ላይ አድርጎት ትንሽ ጠራ....
"ሄሎ አለቃ ትእዛዝህን እየጠበቅን ነው" ከወዲያኛው የስልክ ጫፍ የተሠማው ነው....
"ስልኩን ለልጅቱ ስጧት!"
"እባካችሁ አትግደሉኝ...እባካችሁ ልቀቁኝ" የሚል የደከመ ድምጽ በሥልኩ ውሥጥ በስሱ ይሠማል።..
"የምን ልቀቁኝ ነው ደግሞ ሳልሰቃይ ቶሎ አሠናብቱኝ....ሞቴን አፋጥኑት ነው ማለት ያለብሽ የኔ ሞልቃቃ...ትሠሚኛለሽ ለእያንዳንዷ ሳቅሽ ዛሬ ትከፍያለሽ አንቺ ከንቱ....
ስሙ እናንተ እንዳልኳችሁ አሠቃይታችሁና ሞቷን እንድትናፍቅ አድርጋችሁ ጨርሷት...ደግሞ ወንድ አይደላችሁ ከመሞቷ በፊት በየተራ አንድ ሁለት አጫውቷት"....ብሎ ስልኩን ዘጋው...
እናቴ ምንም ማድረግ እንደማትችል ሥለተረዳችው በዝምታ ታለቅሳለች...
ወንበሩን እያንፏቀቀ ወሠደና ከአባቴ ፊት ለፊት በቄንጥ ተቀመጠ.."አይ ሚስኪኑ ወዳጄ..ትሰማለህ ሚሥትህንና በሆዷ የያዘችውን ሚጢጢዬ ልጅህን በህይወት እንድታገኛቸው ከፈለግክ እነዚህን ሠነዶች መፈረም አለብህ።.... ምን መሰለህ ሙሉ ንብረትህ የኔ ይሆናል ማለት ነው".....አለው በከፍተኛ መኮፈስ
አባቴ ተንጠራርቶ ምራቁን ተፋበት.....አቶ መኩሪያው በንዴት አንዴ በቦክሥ ከነረተው በሁዋላ ምራቁን ከፊቱ ላይ በሶፍት እየጠረገ አንዱን ጠባቂ እናቴን እንዲያሠቃያት በምልክት ትእዛዝ አሥተላለፈለት.....
ጠባቂውም ጩቤውን መዞ በእናቴ ፊት ላይ ማሽከርከር ሲጀምር...አባቴ ተሸነፈ....."እሺ እፈርማለሁ ሚሥቴንና ልጄን አትጉዳብኝ እባክህ" አለው እያለቀሠ...
አቶ መኩሪያው በድጋሚ ከት ከት ብሎ ሳቀና ሠነዱን አቀበለው...አባቴ ሁሉንም ፈራርሞ ቢያሥረክበውም አቶ መኩሪያው ግን ቃሉን አላከበረም
"ያኔ ደብዳቤ ሥጽፍልሽ መልሥ ባትሠጪኝም አሁን ትሠጪኛለሽ...አይ ጊዜ ደጉ" እያለ ቀበቶውን ፈታታና እላዪዋ ላይ ጉብ አለባት......አባቴ እያየ እናቴን እንደ እንሥሣት ደፈራት....አባቴ ባለበት ሆኖ ያቅሙን ያህል ቢንፈራገጥም የታሠረበት ገመድ ውልፍች አላረገውም....እኔም አንደበቴ ተዘግቶ ቃላቶች ከጉሮሮዬ ሾልከው መውጣት አቅቷቸው.....እንባዬ ልብሤን እያራሠው በፍርሃት ተውጬ እመለከታለሁ......
አቶ መኩሪያው እናቴን ተገናኝቷት እንደጨረሠ..."ሠውዬውን ጨርሡት"የሚል ቀጭን ትእዛዝ አሥተላለፈ....
ከመቅጽበት አንገቱን አጋድመው እንደ በሬ አረዱት... ቤቱ በደም ተጨማለቀ።....እናቴን ይዘው ጠብታ የሚመሥል ነገር ጋቷት.....
እየወጡ ሳለ መኩሪያው ገልመጥ ብሎ አያትና"አሁን አንቺ የተደፈርሽና የተጠላሽ ደሃ ሤት ነሽ...እርካሽ" አለና ምራቁን ተፍቶባት ሄደ....
እንደወጡ ከተደበቅኩበት ወጥቼ አባትና እናቴ ወደ ተዘረጉበት ክፍል ገባሁ እማዬ...አባዬ እያልኩ ጮህኲ....አበድኩ።.....ግን ጩኸቴ ብዙም አልዘለቀም አጥወለወለኝና ወደቅኩ.....
ከሠአታት በሁላ እራሤን ሆሥፒታል አገኘሁት....የተፈጠረው ነገር ውልብ ሲልብኝ ሆሥፒታሉን በጩኸት አና
#በቀል
#ክፍል 2
r#ድርሰት nahi
.
.
.
👇👇👇✍✍✍👇👇👇
.........ወንበሩና መሥታወቱ ጋር እሥክላተም ድረሥ መኪናው ሲጢጥጥጥጥ የሚል ድምጽ አውጥቶ ቆመ....አባቴ በመደናገጥ ሁላችንንም ቃኘት አድርጎ ደህንነታችንን ካረጋገጠ በሁዋላ ብርክ እንደያዘው ሠው እየተርበተበተ ከመኪናው ወርዶ ግራ እግሩን እያንቀራፈፈ መሬት ላይ ወደ ወደቀው ነገር አመራ....እኛም ተከተልነው....ያየነው ነገር ግን ይዘገንናል የተበጫጨቀና አሮጌ የሚመሥል ልብሥ የለበሠ ሠው በደም ተጨማልቆ ተዘርግቷል.....አባቴ እንደምንም እራሡን አረጋግቶ የልብ ምቱን አዳመጠ ..እንደ እድል ሆኖ ሠውዬው አልሞተም.......በሞትና ጣር መካከል የምትዋልለውን ነፍሡን ለማዳን አቅራቢያችን ወደሚገኘው ሆሥፒታል ከነፍን.....ዶክተሮቹ ባደረጉት ርብርብና እልህ አሥጨራሽ ትግል ደህና ሆነ.....ወደ ሰማይ ቤት ጉዞ ልትጀምር ያኮበኮበችው ነፍሱ በስጋው ውስጥ ተረጋግታ ተቀመጠች.....በጣም ይገርማል ጉዳቱን ያየ ሠው ሞቷል ብሎ መደምደሙ የማይቀር ነው.....ግን በፈጣሪ ተአምር ተረፈ።..
"አንቺ ነፍስ ሆይ ሂጂ ተመለሺ..ጊዜሽ አሁን አይደለም ሥፈልግሽና የተቆረጠልሽ ቀን ሲደርስ ከጉሮሮው ላይ በግድ መንጭቄም ቢሆን እወሥድሻለሁ" የሚል ነጎድጓዳዊ ቁጣና የማያዳግም ትእዛዝ ከፈጣሪ ደርሷትም ይሆናል ኩስስ ብላ መጥታ ከስጋው የተቀላቀለችው......
ለማንኛውም ሠውዬው ከ25 አሠልቺ ቀናቶች በሁዋላ ነቃ.........እናቴም እጇን ከፍ አድርጋ ፈጣሪዋን አመሠገነች።.......
አባቴ ወደ ውሥጥ ገብቶ "እግዜር እንኳን አተረፈህ...እኔንም ከዘላለም ጸጸት አዳንከኝ"...አለው
"አሜን አመሠግናለሁ....ደግሞ የምን ጸጸት ነው..ይሄኮ ያጋጥማል አደጋ ነው....መቼስ ሠው ሠውን አውቆ አይጎዳውም....አየህ አንተ ህሊና ሥላለህ ነው ሆሥፒታል አምጥተህ ነፍሤን የታደግሃት እንጂ እዚያው ጥለኸኝ ብትሄድ ማን ከልካይ አለህ.. ማንሥ ይይዝሃል"....
"እሺ እኔ ቃሌን ለፓሊሥ ሰጥቻለሁ...አንተ ፍላጎትህ ከሆነ ልትከሠኝ ትችላለህ...በነጻነት ወሥን ምንም ሣትፈራ"...
"የለም... የምን ክሥ ነው እንዲያውም እርሶን ማመሥገን ነው ያለብኝ".....
"እንግዲያውሥ ካልክ ይሁን....እሥቲ አሁን የቤተሠብህን ሥልክ ሥጠኝ ሥለ ሁኔታህ ላሣውቃቸው"....
"አይ ጋሼ ምንም ዘመድም ቤተሠብም የለኝም"...
"አዝናለሁ በጣም...ጓደኛስ.....?"
"እዚህች ምድር ላይ የኔ የምለው አንድም ነገር የለም.....ቤተሠቤን በልጅነቴ በዘመኑ በሽታ በኤች አይ ቪ ቫይረሥ ተነጠቅኩ...... ቤተሠቤ ሢፈርሥ ህይወት ከባድ ሆነችብኝ....ኑሮ ጎዳና ላይ እንደ እቃ ወረወረኝ።.....ከምልዎት በላይ ተሠቃይቻለሁ....
በብርድ፤በረሃብና በሠው ፊት ተገርፌ አደግኩ....ከፍ እያልኩ ሥመጣ እየሠራሁ መማር እንዳለብኝ ወሠንኩ....በቀን አንድ ዳቦ እየበላሁ 9ኛ ክፍልም ደረሥኩ...ያውቃሉ ጋሼ ተማሪዎች ይሠድቡኝ ያንቋሽሹኝ ነበር.....ሠው ሆኜ ከሠው በታች እንደሆንኩ እንዲሠማኝ አድርገውኛል.....ይሄን ሁሉ ተቋቁሜ እየተማርኩ ሳለ ግን ከአንዲት ቆንጆ ፍቅር ያዘኝ....በጥላቻ የተሞላውን ውሥጤን ከዚህች ልጅ የያዘኝ የአይን ፍቅር ድምጥማጡን አጠፋው.....ግን እንደኔ አይነቱ ቆሻሻና ወፍ ዘራሽ በአካል አግኝቼ ብጥይቃት ምን ልትለኝ እንደምትችል በማሠብ ማንነቴን ደብቄ ደብዳቤ እየጻፍኩ እልክላት
ጀመር......ከእሷ መልሥ ባይኖርም እኔ በተደጋጋሚ ላኩላት.....ከእለታት አንድ ቀን ላግኝህና እናውራበት የሚል መልሥ ደረሠኝ.....እሺ ብዬ በሠራዋት ገንዘብ የተቻለኝን ተሽቀርቅሬ ሄድኩ....ስደርስ ግን ብቻዋን አልነበረችም። ከጓደኛዋ ጋር ለስላሳ አዘው እየተጎነጩ ተመለከትኳቸው...ልቤ ለሁለት ተከፈለ..ፍርሃትና ጭንቀት ወጥሮ የያዘው ህሊናዬ "ተው! ከመዋረድ ብትመለሥ ይሻለሃል" እያለ ሲነግረኝ....አፍቃሪው ጎኔ ደግሞ "አንተ ወንድ አይደለህ......?ከማንስ ታንሳለህ...? አንዴ መጥተሃልና ወደ ሁዋላ አታፈግፍግ....አምሮብሃልም...በዚያ ላይ በደብዳቤዎችህ ወዳህ ሊሆንም ይችላል...ስለዚህ ይሄ እድል እንዳያመልጥህ" እያለ ወተወተኝ......በሁለቱ ሀሳቦቼ መጋጨት አንዴ ወደ ፊት ስራመድ አንዴ ወደ ሁዋላ ሳፈገፍግ ቆየሁኝ በመጨረሻም አፍቃሪው ጎኔ አሸነፈና ጉልበት..ወኔና ድፍረት ሰጠኝ.....ምንም ሳላንገራግር የተቀመጡበት ቀጥ ብዬ ሄጄ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁ.... ያፈቀርኳት ልጅ ማን ልበል ብላ ጨበጠችኝ...ደብዳቤውን ሥጽፍላት የነበርኩት ልጅ እንደሆንኩ ነገርኳትና እጄን ወደ ጓደኛዋ ላኩ.....ጓደኛዋ ግን ሠላም ከማለት ይልቅ "እጅህን ሰብስብ" ብላ አሸማቀቀችኝ።....ቀጥላም ከጸጉር እሥከ ጥፍሬ በንቀት አይን መንጥራ አየችኝና "አንተ ነህ ባለደብዳቤው.....?"ብላ ተንከትክታ ሣቀች... ሳቋ እስካሁን ጆሮዬ ላይ ያቃጭልብኛል.......
ያፈቀርኳት ልጅ ምንም እንኳን ትህትና ብታሣየኝም ፍቅረኛ እንዳላት ነገረችኝ።....
አፍሬና አንገቴን ደፍቼ ወደመጣሁበት እየተመለሥኩ ሳለ"መጀመሪያ ታጠብ"የሚል ልብ ሰባሪ ቃል በጆሮዬ ጥልቅ አለ።...
የመጠላት...የባዶነት ሥሜት ተሠማኝ።....ህይወት ገፍታ የጣለችኝ፤እግዜር ሣያሥብበት የፈጠረኝ ከንቱ መሆኔን አመንኩ....ሠውን ማፍቀርም ሆነ በሠው መፈቀርም እንደማልችል ደመደምኩና ብን ብዬ ጠፋሁ።....
ከዛች ቅጽበት በሁዋላ ትምህርት ቤትም አልተመለሥኩም ከሠውም ጋር አልተገናኘሁም...ብቻዬን ከከተማው ወጥቼና ዳሥ ሠርቼ የጫካ ውሥጥ ኑሮ መኖር ጀመርኩ......ምድር ላይ መኖር ሲያንገሸግሸኝ ነው እንግዲህ መኪናዎት ላይ ዘልሌ የገባሁት....ሥለዚህ እርሶ ምንም ጥፋት የለበወትም።..እንዲያውም ደግነትዎ በበድኑ አካሌ ላይ ህይወት እንዲዘራብኝ አድርጓል..."
አባቴ ይሄን የሠውዬውን ታሪክ ሲሰማ ስቅሥቅ ብሎ አለቀሠ...."አይዞህ ካሁን በሁላ እኔ አለሁልህ..በቻልኩት መጠን የወንድምነት ፍቅርን ልሠጥህ ቃል እገባልሃለው"አለው.......
ከጥቂት ቀናት በሁላ አባቴ ለሠውዬው ቤት ገዛለት...ድርጅቱም ውሥጥ የአባቴ ቀኝ እጅ ሆነ።.....ሠውዬው የድሮ ማንነቱን እርግፍ አርጎ ትቶ አዲሥና ጣፋጭ ህይወት መኖር ጀመረ.... እራሡንም መኩሪያው ብሎ ሠየመ።....ከዚህ በሁዋላ እንግዲህ አቶ መኩሪያው እያልኵ አወጋችሁዋለሁ...አቶ መኩሪያው በሥራው ቀልጣፋ በመሆኑ ከአባቴ ሙገሳንና ትልቅ እምነትን አገኘ።....ይህ በእንዲህ እንዳለ እናቴ ሁለተኛ ልጅ አረገዘች....የአራት ወር ቅሪት እንደሆነች አበሠረችን...ቤቱ በደሥታ ሠከረ።....
እለተ ሰንበት ከቀኑ 12 ሠዓት ገደማ ከሠፈር ልጆች ጋር ኴሥ እየተጫወትኩ ነው....ድንገት ሁለት ጥቁር ፒካፕ መኪናዎች ወደ ቤት ሲገቡ ተመለከትኩ።.. መኪኖቹን ችላ ብዬ ጨዋታዬን ቀጠልኩ በመሀል ግን ውሃ ጠማኝና ወደ ቤት አመራሁ.....ግቢውን አልፌ ማም እያልኩ ሥገባ በቤታችን ውሥጥ ያልተለመደ እና ሠምቼው የማላቀው አሥደንጋጭ ድምጽ ጆሮዬ ላይ አሥተጋባ......
ይቀጥላል
ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ ይተባበሩ
@fkrnahiwot
ገራራሚ coveroch የታዋቂ ሰዎች ዘፈን በሚማርክ ቃና ማዳመጥ ከፈለጉ join ያርጉ አሁኑኑ
join us @fkrnahiwot
@Fkrnahiwot
Any coment @nahita2
❤️በቀል❤️💝
#ክፍል 1
#by nahi የእናቱ ልጅ💝🌷
.
.
.
👇👇👇✍✍✍👇👇👇
ቀኑ ቅዳሜ ነው ጸሀይዋ በሥተምሥራቅ በኩል ለመውጣት እያኮበኮበች ነው።... ምድርን ልታበራው አዲሥ ነገርን ልታሣየን ተሥፋችንን ልታለመልም...አየሩ ነፋሻማ ነው በጭጋግ የተሸፈነው በነጎድጓድ ድምጽ የታጀበው ሶሥቱ የክረምት ወራት ዳንኪራውን ጨርሶ እነሆ ዛሬ አዲሥ አመት ተቀብለናል..አዲሥ ተሥፋ አዲሥ እቅድ...እኔም እንደተለመደው ጸሀይ ሥትወጣ ለማየትና ከበረከቷም ለመቋደሥ ከቤታችን ግቢ ቁጭ ብዬ በሃሣብ ነጉጅያለሁ...ጥልቅ ሃሣብ ንዴት ቁጭት ብሥጭት የተቀላቀለበት ሃሣብ ለረጅም ሠአት ይዞኝ ሄዷል።....."እዩብ ቁርሥ ደርሷል" የሚለው የሠራተኛችን የአበበች ድምጽ ነበር ከሃሣቤ ያባነነኝ....
እንደመበርገግ ብዬ"እሺ አበበች መጣሁ"አልኳትና ቡና ለማፍላት ወደ ኪችን ገባሁ... ...እናቴ ሣትነሣ ቀድሜ ቡና በማፍላት ወደ ክፍሏ ይዞ መሄድ የእለት ተእለት ተግባሬ ነው.....እሷም ቢሆን በኔ እጅ የተፈላ ቡና ከአልጋዋ ሣትወርድ መጠጣት ሱስ ሆኖባታል....ዛሬም ይሄንኑ ነው ያደረግኩት....ቡናውን አፍልቼ እንደጨረስኩ አንድ ስኒ ቡና ላይ ሁለት ማንኪያ ሱካር ጨመርኩበትና ወደ እናቴ ክፍል አመራሁ.....
"እማዬ ተነሽ አንቺ እንቅልፋም አታንኮራፊብኝ..ምሳ ደረሰኮ"..
"እሺ የኔ አንበሳ መጣህልኝ"እንደመንጠራራት አለች..
"አንቺኮ እኔ ባልኖር ዝንት አለም ትተኚ ነበር ክክክ"...
"አይ እንግዲህ ድንበር አትለፍ ባንተ መቀሥቀሥ ሥለምፈልግ ነው እንጂ ነቅቼ ነበር"..
"ይሄው እማ የተለመደው"
"ጎሽ የኔ ልጅ...ናልኝ የኔ ቆንጆ"እያለች አገላብጣ ሣመችኝ...ቡናውን ከጠጣች በሁዋላ በፈገግታ ታየኛለች....
ጉያዋ ውሥጥ ትሸጉጠኝና በእናትነት ፍቅሯ ጸጉሬን እየደባበሠች ሌላ አለም ውሥጥ ትከተኛለች......ለጊዜውም ቢሆን በውሥጤ ያለው ጥላቻ ብን ብሎ ይጠፋል........እማ ጋር ሁሌም ሥናወራ እንደ እናትና ልጅ ሳይሆን .....ልክ እንደ እኩያ ጓደኛ ወይም እንደ ፍቅረኛሞች ነው...ምድር ላይ ካለሷ ማንም ሥለሌለኝ ይሆናል...እሷም ካለኔ ማንም ሀይ ባይ ዘመድ ሥለሌላት ይሆናል እንዲህ ፍቅር በፍቅር የሆነው.....ለነገሩ ያየን ሠው ሁላ እናትና ልጅ ናቸው ብሎ ለማመን ይቸገራል....እኩያ ወንድምና እህት ነው የምንመሥለው....እናቴ ወ/ሮ የሺወርቅ ትባላለች......መካከለኛ ቁመት ሲኖራት ከለሯ ቀይ ነው....ዳሌዋ ወጣ ያለና ወገቧ ቀጠን ያለ በመሆኑ በሷ እድሜ ክልል ያሉ ወንዶች ሁሉ ይሻፍዱባታል...
ብዙዎቹ ለትዳር ቢጠይቋትም ልጄን በእንጀራ አባት አላሣድግም በማለት አሻፈረኝ ብላ ይሄው እሥካሁን ብቻዋን ናት...የኔ ሚሥኪን እናት....እኔ ባህሪዬንና ከለሬን ከእናቴ ብወሥድም ሌላውን ከአባቴ እንደወረሥኩት እናቴ ፎቶውን እያሣየችኝ አውግታኛለች....እኔ ማለት ዠለግላጋ ቁመት ያለኝ....አፍንጫዬ ሥልክክ ያለ...ጸጉረ ሉጫና ሠውነተ ደንዳና ነኝ...ብዙውን ጊዜ ታንቆ መሄድ አይመቸኘም...ለቀቅ የሚያረጉ ልብሶችን መልበሥ እመርጣለሁ...ይሄው ዘንድሮ 27ኛ አመቴን ይዤያለሁ..በሆቴል ማነጅመንት ተመርቄ ሥራ ከያዝኩ ድፍን 3 አመት ሆነኝ... እኔ እና እናቴን ለማሥተዳደር ላይ ታች ማለት የጀመርኩት ገና በ13 አመት እድሜዬ ነው....ከትምህርቴ ጎን የማልሠራው ሥራ አልነበረም...ሊሥትሮ መጥረግ፣የተለያዩ ትንንሽ ሸቀጦችን እንደ ማሥቲካ... ሲጃራ...ብሥኩት ወዘት....የመሣሠሉትን ከሡቅ እየገዛሁ እቸረችራለሁ ...ህይወትን ታግዬ እዚህ ደርሻለሁ ላቤን ጠፍ አድርጌ ሠርቼ በቂ ገንዘብም አጠራቅሚያለው....አሁን ላይ ህይወት ተሥተካክሎልኛል ቢሆንም የዋጋ ንረትና ግሽበቱ ለአንድ ተቀጣሪ ሠራተኛ የሚቀመሥ አይደለም... የሚወጣው ገንዘብና የሚገዛው እቃ ለየቅል ነው... እንዲያውም የቤት ኪራይ ሃሣብ ሥለሌለብን እፎይታ ነው....የምንኖረው በጅማ ከተማ አጂፕ ሠፈር ውስጥ በሚገኘው 1500 ካሬ ላይ ባረፈ ባለ 3 መኝታ ክፍል ባለው ቪላ ውሥጥ ነው... ልክ እንደማንኛውም የከተማ ዲታ.....ይገባኛል እንዴት ከእጅ ወዳፍ እየኖራችሁ እንዲህ የተንጣለለ ቪላ ሊኖራችሁ ቻለ? የሚለው ጥያቄ እያቃጨለባችሁ ነው...አዎ ልክ ናችሁ ልጠይቁም ይገባል.......ወደ ሁዋላ መለሥካችሁ ከ20 አመት በፊት........ወንዱ አያቴ ከተማዋ ላይ የታወቀ ባለጸጋና ሀብታም ነበር...ይሄ ሁሉ ሀብት ቢኖረውም እዚች ምድር ላይ ያለው ብቸኛው ልጁና የሃብቱ ወራሽ አባቴ ብቻ ነው......አባቴ በእናቴ ፍቅር እፍ ብሎ መክነፉን አያቴ በመሥማቱ ጊዜ ሣያጣፋ ድል አርጎ ደግሶ ሙሉውን ሃብቱን ወደ አባቴ አዘዋወረው....ብዙም ሣይቆይ አያቴ አረፈ......አባቴም ድርጅቱን የበለጠ በማጠናከር በየቦታው ማለትም አዲሥ አበባ...አዳማ እና ደብረዘይት ሆቴሎችን ከፈተ.......የሥኬትን ቁልፍ በእጁ ተቆናጠጠ....እኔም ከአምሥት አመት በሁዋላ እቺን አለም ተቀላቀልኩ....ቤተሠባችን ደሥታ ፌሽታና ተድላ የሞላበት ሆነ......13ተኛ አመቴን እንዳገባደድኩ አሪፍ ቤተሠባዊ ጊዜ ለማሣለፍ በሚል የተፈጥሮ ድምቀት ወደሆነችው ደብረ ዘይት(ቢሾፍቱ ሆራ) ጉዞ ጀመርን........ድንገት ግን ምንነቱን ያለየሁት ነገር ተንደርድሮ ገባብን...
ሙሉ ታሪኩን ለማግኘት ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@fkrnahuwot
