Nathan casting agency
Open in Telegram
The best place to get the best casting jobs Our services -casting models - for music clips - movies - series dramas - fashion shows - television shows Contact: 0920358051
Show moreEthiopia16 170The category is not specified
408
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ዘራፍ ዘራፍ ሀካኪ ዘራፍ
ማን ይደፍራታል የጀግናን በራፍ
ባጭሩ ታጥቆ ካላሉ ዘራፍ
ዛፍ ይቆረጣል ከሞኝ በራፍ
ከጀመረማ ወሳኙን ምዕራፍ
እራሱ ገርፎ ይጮሃል ጅራፍ
ሀካኪ ዘራፍ ጉልበት ነዉ ተገን
መች ቀልድ አለና በሀገር በወገን
ሀገር እኮነው አንድ የሚያደርገን
ህብረታችን ነው የሚታደገን
ከሰሜኑ ጫፍ እስከ ደቡቡ
ከምስራቁ ጫፍ እስከ ምዕራቡ
በኢትዮጵያ ጉዳይ አንድ ነው ልቡ!!!
አደዋ የኛ!
🔴🔵በቀል
✅💟ክፍል 1⃣1⃣
.
.
.
.
👇👇👇✍✍✍👇👇👇
ሠላምና አባቷ ካሊፎርኒያ ከከተሙ ይሄው 1 ወር ሞላቸው.....ወዳጃቸው ሰለሞንም በተንጣለለ ቪላው ተቀብሏቸው ቤታቸው ያሉ እሥኪመሥላቸው እየተንከባከባቸው ነው።ወ/ሮ ምእራፍ እንደቀድሞዋ እንድትናገር ለማስቻል ያልተደረገ ጥረት የለም ብዙ ህክምና በስፔሻሊሥት ዶክተሮች ቢደረግላትም ምንም ጠብ የሚል ነገር አልተገኘም...ለነገሩ እጅን አጣጥፎ ከመቀመጥ መሞከሩ አይከፋም በእርግጥ መናገር ባትችልም በወ/ሮ ምእራፍ እግሮች ላይ የተወሰኑ ለውጦች ታይቶባቸዋል....እንደማንኛውም ሰው መንቀሳቀስና መራመድ ባትችልም እቃ፤ግድግዳ ወይም ሌላ ሠው በመደገፍ መቆም ጀምራለች።.........ይሄም ይበል ነው።
ቦርዱ በወ/ሮ ምእራፍ ህክምና ዙሪያ መክሮበትና ዘክሮበት ከሆስፒታል እንድትወጣና ቤቷ ሆና በግል ሀኪም የቴራፒይ እንቅሥቃሴ እንድታደርግ ስለወሰነ በሄዱ በአንድ ወር ከ15 ቀናቸው ወደ ቤታቸው ተመለሱ።.......እንግዲህ ወ/ሮ ምእራፍ ቤቷ ከቀረች 1 አመት ሞላት። ዛሬም ከመቆም በቀር ምንም የተቀየረ ነገር የለም...እንደ ሁልጊዜው መናፈሻቸው የሚገኘው ውድ ሶፋ ላይ ተንፈላሳ ተፈጥሮን ታደንቃለች....ከተራራው አናት ላይ ብርሃን የምትፈነጥቀውን የጥዋት ጸሀይ ለማግኘት በለሌት ትሠጣለች።........ቆንጅዬዋና ቤቷን ቀጥ አድርጋ የያዘችው የቤት እመቤት በባሏ እንዝህላልነት ምክንያት ለእድሜ ልክ ጉዳት ተዳረገች.....ይሄን ሁሉ ታሪክ ሠላም ቁባ የላትም የምታውቀው በአባቷ የተነገራትን ብቻ ነው....የምታስበው እናቷ በደም ግፊት ምክንያት ከደረጃው እንደተንከባለለች ነው......ምክንያቱም አባቷን ታምነዋለች ለሷ አባቷ ማለት አርአያዋ ነው...ለሷ አባቷ ማለት የአለም ምርጥ አባት ነው.....የምታውቀው ቤተሠቡን እንደሚወድና ለቤተሠቡ ትልቅ ፍቅርና ክብር እንዳለው ነው። ለሰላም ያልታያት መጥፎ ባህሪውና ቆሻሻ ሥራዎቹ እናቷ ወ/ሮ ምእራፍና ውሥጥ አዋቂ የሆነው ጌታ ቢያውቁትም እሥካሁን ተዳፍኖ ቀርቷል.....በእርግጥ ወ/ሮ ምእራፍ መናገር ባትችልም እጇ በሚገባ ይሠራል ሥለዚህ ሁሉንም ነገር በወረቀት ማሥፈር ትችላለች.....ይሄን እንዳታደርግ የያዛት ለሠላም ያላት ፍቅር ነው። ከዚህ በላይ ሥቃይና የልብ ቁሥል ልትጨምርባት አልፈለገችም..."ልጄ እኔን በቁም አጥታ የተሠቃየችው ይበቃታል...እኔንም አባቷንም አጥታ እንዴት ትችለዋለች....እውነቱን ነግርያት ደሥታዋን ከምታጣ በውሸት አለም ብትኖር ይሻለኛል" ብላ በማሠብ ሁሉንም ነገር በሆዷ አምቃ ይዘዋለች።........
*///////******/----*****
ወ/ሮ ምእራፍ ልጇ ሰላም አዲስ በሚሰማት ስሜት ፍክት ብላለች......ከዚያ ሁላ ስቃዩዋና ጭንቀቷ በሁዋላ ሥለ ወንድ ማሰብ ስለጀመረች ደስተኛ ሁናለች።......ወ/ሮ ምእራፍ መልሳ ደግሞ ትክዝ አለች...እንደ ባልተቤቷ አይነት ወንድ እንዳይሆን ልቧ ፈራ። እንደ አይኗ ብሌን የምትሳሳላት አንድያ ልጇ በወንድ ልቧ ተሰብሮ ስትሠቃይ አሠበችውና አንገሸገሻት.....
"ብቻ ጥሩ ሠው ያድርገው" አለች በሆዷ...
"ሲስተር... ሲስተር አዜብ"...ሠላም ነበረች የተጣራችው...
"አቤት ሠላም ፈለግሽኝ"
"አዎ ትንሽ የማጠናው ነገር ስላለኝ ይቅርታ አድርጊልኝና እናቴን እንድትከታተያት ነው"...
"ሠላምዬ ሥራዬ ሥለሆነና ሥለሚከፈለኝ ብቻ አይደለም እናትሽን የምንከባከባት እንደ እናቴ ሥለማያት ቢሆን እንጂ...ሥለዚህ ሥታዥኝ አትጨነቂ በደሥታ ነው የማደርገው"...
"እሺ አመሠግናለሁ" ብላት ወደ ክፍሏ አመራች.....
ከውሥጥ ቆለፈችውና ከቦርሳዋ ውስጥ ማስተወሻዋን አወጣች ከዛም ገለጥ ገለጥ አደረገችና ከወዲህ ወዲያ እየተንጎራደደች ማነባነቧን ቀጠለች....
~~~~~~*******~~~~~~~
በእጄ ያልዳበሥኩህ በአይኔም ያላየሁህ
ከንፈርህ ያልሳመኝ ትንፋሼ ያልደረሠህ
በእቅፍህ ያልገባሁ ያልተሠማኝ ድምጽህ
እንዲሁ በህልሜ አሣምሬ የሣልኩህ
ዛሬሥ አትመጣም ወይ ተሠቃየሁብህ።
*
በህልሜም በእውኔም ቀሥፈህ ይዘኸኝ
ልቤ እንዳያፈቅር እሥረህ አሥቀምጠኸኝ
የአዳም ዘር በሙሉ በባህሪው ቢያንስብኝ
ሳነሳ ስጥል አረከኝ ሞኛ ሞኝ
እንከን ሥደረድር እድሜ ተላለፈኝ።
አሁንሥ ይበቃል.....
ልቤ የሚነግረኝን አዳምጠዋለሁ
ውስጤ የሚሰማኝን አጣጥመዋለሁ
መሥፈርት መደርደሬን ዛሬሥ አቆማለሁ።....
የማላውቅህ ፍቅሬ በህልሜ የማይህ
አገኘሁህ መሠል ልቤን ከፈትኩልህ
ጠቅልለህ ኑርበት ቤቴን ፈቀድኩልህ
ህልሜም ይፈታልኝ ልሸጎጥ ከጉያህ።..........................
*******
ሠላም ከ10 ቀን በሁላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሥቲ ለሚካሄደው የስነ ጽሁፍ ውድድር ለመሳተፍ እየተለማመደችና እየተዘጋጀች ነው።........
ምእራፍ አንድ ተፈጸመ።
.
.
.
.
💟💟ምእራፍ 2ን በጉልበትም ቢሆን እንቀጥለዋለን.....
👉👉ጎበዝ ሼር እና ላይክ ያድርጉልና .....
join👇👇
@fkrnahiwot
💟❤️በቀል💟
✔️ክፍል 🔟
.
.
.
👇👇💟💟👇👇❤️❤️👇👇
"ሌላ ደግሞ ምንድነው....? በማለት ሁለቱም አይን አይኑን
የመውጋት ያክል እየተመለከቱ የከንፈሩን እንቅሥቃሴ
ይከታተሉ ጀመር።.....
ዶክተሩ የደረቀው ጉሮሮውን ለማርጠብ ውሃ በብርጭቆ
ቀዳና ባንድ ትንፋሽ ጭልጥ አደረገው....."ምን መሰላችሁ
ወ/ሮ ምእራፍ መራመድ አትችልም"
"ምን.....?"የሠላም አባት በድንጋጤ ቁጭ ብድግ
አለ..ሠላም ተሥፋ በቆረጠ ሥሜት ውሥጥ ሆና ባለችበት
ወለሉ ላይ በቂጧ ዘርፈጥ አለች።.....ዶክተሩ እንዲረጋጉ
ለሁለቱም ውሃ በብርጭቆ ሠጣቸው...
"እና ምን ተሻለ ዶክተር....?"
"ሥትወድቅ የጀርባ አጥንቷ(spinal cord) በመመታቱ ነው
ለዚህ የተጋለጠችው......ተረጋጉ አሁን ወደ ዶክተር ውድነህ
እመራታለሁ ቴራፒሥት ላይ የተሻለ ሀኪም ነው....ከበፊቱ
ይበልጥ ጠንካራ መሆን አለባችሁ። ሥነ ልቦናዋ እንዳይጎዳ
እንክብካቤና ፍቅር ልታሳዩዋት ይገባል።"...
" ዶክተር መች ይዘናት ልንወጣ እንችላለን...?"
"ከሁለት ቀን በሁዋላ"
"እናመሥግናለን"....ሠላም መጠየቅም ሆነ መናገር
አልቻለችም....ሠማይ በአናቷ የተደፋባት ያህል ጨንቋታል።
ከዶክተሩ ክፍል ከወጡ በሁዋላ የሠላም አባት በውሥጡ
ያሰላስላል "ምነው እንደ ወደቀች ትንፋሿ ጠጥ ባለ...ምን
አይነት መከራ ነው ያመጣችብኝ...ዊልቼር ተደግፋ የሠው
መሣቂያና የሚዲያ አርእሥተ ዜና ልታረገኝ አይደል...አንድ
ነገርማ ማድረግ አለብኝ" አለና ስልኩን አውጥቶ ካሊፎርኒያ
ያለው ወዳጁ ሰለሞን ጋር ደወለ....
ስልኩ ይጠራል ግን አይነሳም....
በሥጨት አለና "ሠላሜ አንቺ ሂጂላት እናትሽ ጋር..እኔ ሥለ
እናትሽ ጉዳይ ዘዴ ልፈልግ"አላትና ግንባሯን ሳማት..
"እንዴ አባ እሥካሁንኮ ነቅታ አላየሃትም"..
"ምን መሠለሽ ሠላሜ እናትሽን ምን ያህል እንደምወዳት
ታውቂያለሽ...እንደዚህ ሁና በምን አቅሜ ልያት...አጠገቧ
ሁኜ ብነፋረቅና ሥሜቴ ሲረበሽ ብታይ የምትጎዳ
አይመሥልሽም..ባይሆን ታዋቂ እሥፔሻሊስቶችን ላፈላልግና
እፎይታ ይኑረን።"
"እሺ አንተ እንዳልክ አባ ቻው እወድሃለሁ"..
"እኔም እወድሻለሁ የኔ ልእልት..ቻው እናትሽን ተንከባከቢያት
ነገ እመጣለሁ"..
የሠላም አባት ፈረሥ የሚያሥጋልበው ቢሮውን ከፍቶ
በተሽከርካሪው ወንበር ላይ ፈልሰሰ ብሎ እንደተቀመጠ
ቫይብሬት ሞድ ላይ ያለው ሥልኩ ነዘረው......ከኪሱ
አውጥቶ ሲያየው ቅድም የደወለለት አሜሪካ ያለው ወዳጁ
ነው።።
"ሄሎ ወንድሜ.....የጠፋ ሠው"
"ምን ሆነህ ነው ሥልክ የማታነሳው እንደዛ ደጋግሜ
ሥደውልልህ"...
"ዛሬ ደግሞ ጠንከር ብለህብኛል ሻወር ልወሥድ ገብቼ
ነው..እዚህኮ በበጋ ሙቀቱ አይቻልም።...ለመሆኑ በሰላም
ነው..? ሚሥትህሥ እንዴት ናት ...?"
"ምን ሠላም አለ..በሷው ጉዳይ አይደል መደወሌ"
"እሺ ምን ልርዳህ ወንድሜ"
"ምን መሰለህ ነቅታለች ግን መራመድም ሆነ መናገር
አትችልም....ሥለዚህ የተሻለ የፊዚዮ ቴራፒይ ህክምና
የምታገኝበትን ሆስፒታል አፈላልገህና ሁሉንም ነገር ጨርሠህ
እንድትጠብቀኝ ነው።..
"አታሥብ በኔ ጣለው...ዛሬውኑ እጀምራለሁ"..
"ከዚህ ጉድ አውጣኝ ወንድሜ ቢያንስ በ15 ቀን ውሥጥ
መምጣት ይኖርብናል።
"ሁሉም ነገር እንዳለቀ ቁጠረው...አትጨነቅ"..
"በል ደህና ሁን"...ስልኩን እንደዘጋው ቢሮውን ቆለፈና ወጣ።
ሹፌሩን ደውሎ አሥጠራና ከሁዋላ በቄንጥ ተቀምጦ ወደ
ፒያሳ አመራ.....ለዲታዎች ተብሎ በከፍተኛ ሚስጥር
በተዘጋጀው ድብቅ ቤትም ጎራ አለ።...ከአንዷ ልጃ ገረድ ጋር
ሊጫወት.....
//////*******/////////
ሠላም ወደ እናቷ ክፍል ሥታመራ በሙሉ ፈገግታ
ነበር.....ውሥጧ ቢጨልምም ፈገግ ማለትን
ታውቅበታለች.....ፍልሥፍናውም የጠቀማት ይመሥላል...
እንደገባች ከጎኗ ቁጭ አለችና ጁስ በብርጭቆ ቀዳች..ከዛም
አንገቷን ቀና አደረገችላትና "እማ እቺን ጠጪ ፈሳሽ
ያሥፈልግሻል"......አለቻት
ወ/ሮ ምእራፍም ፈገግ አለችና በደሥታ ጠጣችላት...
መልሳ አደላድላ አሥተኛቻትና እንደተለመደው ታሪክ
ልታነብላቸው መጽሀፏን ከቦርሳዋ አወጣች...
"እማ ዛሬ የማነብልሽ ሥለ አንድ ያልታደለ አባት ታሪክ
ነው"....
እናቷም አንገቷን በመነቅነቅ እንድትጀምር ጋበዟት....
"በድሮ ጊዜ ድህነት እጅግ የጎዳቸው ሁለት ጥንዶች
ነበሩ...የሚተዳደሩት ባልዬው በቀን ሥራ ለፍቶ በሚያመጣት
ትንሽዬ ሳንቲም ነበር..ምሳ በልተው እራት የማይደግሙበት
ጊዜም አለ....ፈተናቸው ሲበዛ ደግሞ ፈጣሪ ልጅም
ከለከላቸው......የበላነውን በልቶ ያድጋል..ልጅ የእግዛብሄር
ነው ፈጣሪ ያሣድገዋል ብለው ለመውለድ ቢፈልጉም.. ብዙ
ጊዜ ቢሞክሩም አልሳካ ይላቸዋል።በኑሮውና በልጅ
ያልታደለው ባልም ብሥጭት ሲበዛበት በሚያገኛት ሳንቲም
አረቄ መጠጣትና እየሠከረ ወደ ቤት መግባቱን የእለት ተእለት
ተግባሩ አደረገው።.....ምንም የተለወጠ ነገር ሳይኖር
አመታት ነጎዱ..ከሆነ ጊዜ በሁዋላ ግን ሠውዬው ጤና
አጣ...ሁሌ ይጠጣል ሁሌ ደም ይተፋል....በመጨረሻም
አልጋ ይዞ ቤት ውሥጥ ለመቅረት ተገደደ...
የፈጣሪ ተአምር ግን የአልጋ ቁራኛ ከመሆኑ በፊት ያደረጉት
ሙከራ ሠርቶ ሚሥቱ ቅሪት ሆና ነበር....ሣይጠበቅ ሆዷ
እያፈጠጠ መጣ።...እንዳረገዘችም አወቁ... ነገር ግን ምን
ያደርጋል አባትዬው ፈጣሪን በትእግሥት ባለመጠበቁና ተሥፋ
በመቁረጡ አጉል ሡሥ ውሥጥ ገብቶ ባመጣው መዘዝ
የሚጠብቃትን ልጁን በአይኑ ለማየት ሳይበቃ
እሥከወዲያኛው አሸለበ።".....
ሠላም ታሪኩን አንብባላት እንደጨረሠች መጽሀፉን ከደነችና
"አየሽ እማ በፈጣሪ ተሥፋ አይቆረጥም።...ፈጣሪ ፈተናን
አያበዛም የተሻለ ህይወት ሊሠጠን ቢሆን እንጂ.. ሥለዚህ
እማ ለእኔ ስትይ ተሥፋ እንዳትቆርጪብኝ..በቅርቡ መናገር
እንደምትጀምሪ ዶክተሩ ነግሮናል " አለቻት አይን አይኗን
እያየች....
እናቷ ወ/ሮ ምእራፍም እሽታዋን በፈገግታ መለሰችላት.....
ሠላም "እማ አንዴ መጣሁ ነርሷን ጠርቼ ግልኮስሽ ስላለቀ
ትቀይርልሽ....በዚያውም ካርድ ልግዛ" አለችና በሩን ገርበብ
አድርጋው ወጣች...
ወ/ሮ ምእራፍ ሽንቷ ወጥሯት ስለነበር የሽንት ፊኛዋን
ማሥተንፈሥ ሥለፈለገች የተሠካካባትን መርፌ ከእጇ ላይ
ነቃቅላ ቀኝ እግሯን አሥቀድማ ለመቆም ስትሞክር እንደ ህጻን
ልጅ ሽብልል ብላ ወደቀች።....
ግሉኮሱን እንድትቀይር የተነገራት ነርስ ክፍሉ ውሥጥ
የመተራመስ ድምጽ ሥለሠማች ፍጥነቷን ጨምራ ሥትገባ
ወ/ሮ ምእራፍ ወድቃለች....ሌሎች ነርሶችን ጠርታ
ተጋግዘው አልጋዋ ላይ አሥተኟትና ክንዷ ላይ የሚሰካኩትን
መርፌዎች በሚገባ አሥተካክለው መድሀኒት ሠጧት።....
ሠላም ከውጪ ሥትገባ ከምትንከባከባት ነርስ ውጪ ሌሎቹ
ስለሄዱ ብዙም ግር አላላትም.....
"ሲስተር እሥክመለሥ እናቴን ሥለጠበቅሽልኝ
አመሠግናለሁ" አለቻትና ስትቀመጥ ግን ደነገጠች...የእናቷ
ፊት በእንባ ታጥቦ ነበር.....ተሥፋ የቆረጡት የእናቷ አይኖች
እንባ ያለማቋረጥ ያፈልቃሉ.....
ሠላም ግራ ተጋባች "እንዴ እማ ምን ሆነሽ ነው
የምታለቅሽው....? ሲስተር ምን ሆናብኝ ነው....ምን ተፈጥሮ
ነው...?"
"አንቺ ነግረሽኝ እንደመጣሁ እናትሽ መሬት ላይ ወድቃ
አገኘሁዋት"..
አሁን የእናቷ ፊቶች ለምን በእንባ እንደረጠቡ በደንብ አድርጎ
ገባት....ለማልቀሥ ቢዳዳትም እናቷ ፊት ጠንካራ መሆን
እንዳለባት ሥለምታውቅ ከውሥጥ የሚያቃጥላትን እሣት
ለጊዜውም ቢሆን እዛው እፍን አድርጋ አከሠመችው....
"ተይ እንጂ እማ ቅድም ያንብኩልሽ ታሪክ ም
💟💟በቀል💟
✔️ክፍል 9⃣
✍ድርሰት በሸረፈዲን የእናቱ ልጅ
.
.
.
.....🌹🌹💟💟👇👇👇✅💝
ሰላም ከሠአታት በሁዋላ ሥትነቃ በሠመመን ውሥጥ ገብታ
ከመኝታዋ ተነሣችና አንድ ሁለት እርምጃ ተራመደች ግን የሆነ
ነገር እጇን ከብዷታል እንደፈለገችው አላንቀሣቅሥ
አላት...በትኩረት አይኗን ገልጣ ሥታይ እጇ ላይ መርፌ
ተሠክቷል ቀና ስትል ለሠአታት ሥትጠጣ የነበረችውን
ግሉኮሥ ተመለከተች....አባቷ በር ላይ ሥለነበር ኮሽታ
ሲሰማ ወደ ውሥጥ ዘለቀ......
"አባ ምንድነው ነገሩ ምን ሆኜ ነው...? ግልኮሥ
የተተከለልኝ"
"እራሥሽን ሥተሽ ነበር....አሁን አትንቀሣቀሺ ትንሽ እረፍት
አርጊ"..
"እማ ምን ሆነች...?"
"ገና አልጨረሡም...አሁንም ቀዶ ህክምናው ላይ ናቸው"...
"እማ እዛ ተንጋላማ እኔ እረፍት አላረግም" ክንዷ ላይ
የተሰካውን ግልኩስ በጥሳ ጣለችው...
"እንዴ ሠላሜ ምን ማድረግሽ ነው"
"አሣልፈኝ ልውጣበት"....
አባቷም እንደማትሠማው ሥላወቀ ሊቃወማት
አልፈለገም..ተከታትለው ሄዱ።.....
ዶክተሮቹ ቀዶ ህክምናውን ከጀመሩ 4 ሠአታት ቢያልፉም
እሥካሁን እንዲህ ናት የሚል ነጋሪ የለም።....
በድንገት ግን ውክብያ ተፈጠረ..
ተጨማሪ ዶክተሮችና ነርሶችም ወደ ወ/ሮ ምእራፍ ክፍል
እየተሯሯጡ ገቡ።....በዚህ ጊዜ ሠላምና አባቷ የሚይዙትን
የሚጨብጡትን አጡ...
የሠላም አባት"እረ ባለቤቴ እንዴት ነች...? አንድ እንኳን
የሚነግረኝ ሰው ይጥፋ" እያለ ያጓራል...ይጮሃል....
ሠላምም ግድግዳውን ተደግፋ ታነባለች።....
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በሁዋላ አንዲት የተባረከች ነርስ
ወጣች...ጭንቀታቸውን አይታ ሥለተረበሸች ሙያው
ባይፈቅደውም ወደ እነሡ አመራች
"አይዟችሁ አሁን ሁሉም ተረጋግቷል....ቀዶ ጥገናው
እየተካሄደ ሳለ ደሟና ሥኳሯ ከፍ ብሎ የልብ ምቷ ቆሞብን
ነበር....ፈጣሪ ሲረዳት አሁን ወደ ቀድሞው ተመልሳለች"
ብላ ጭንቀታቸውን አረገበችላቸው።....
ዶክተሩ 8 ሰአታትን የፈጀውን ቀዶ ጥገና አጠናቆ ወጣ.......
"ዶክተር እንዴት ናት ታዲያ"
"ቀዶ ህክምናው የተሳካ ነበር....ጭንቅላቷ ውሥጥ
የፈሠሠውን ደም ማሥወገድ ችለናል....ግን"
አላስጨረሱትም "ግን ምን ዶክተር"
"ኮማ ውሥጥ ገብታለች"...
"እና ምንም አይነት ዘዴ ተጠቅመህም ቢሆን አሥነሳታ"
"ብችል ደሥ ባለኝ....ያለን አማራጭ መጠበቅ ብቻ ነው።"
"ቁጭ ብዬማ አልጠብቅም ወደ ውጭ እወሥዳታለሁ"....
"የፈለከውን ሀኪም ማማከር ትችላለህ አሁን ላይ ግን
ብታንቀሣቅሣት የባሰና የከፋ ችግር ነው የምትፈጥርባት..
"እሺ አሁን ልናያት እንችላለን..? ሠላም ነበረች
የጠየቀችው..
"ከፍተኛ ክትትል ውሥጥ ናት....የምታዩበት ጊዜው ሲደርሥ
ነርሷ ታሳውቃችሁዋለች...በርቱ" ብሎ በቆሙበት ጥሏቸው
ሄደ።...
ከሰላም አባት ጋር ንኪኪ ያላቸው ከፍተኛ ባለስልጣናትና
የንግዱ አለም ሰዎች ሆስፒታሉን ሞሉት። ያው ገንዘብ ካለህ
አሸርጋጁ ብዙ አይደል....ጀሌውና ጭፍራውም እንደዚሁ
አለቅጥ ይበዛል....
ቀኑ ይበራል.....ሠላምና አባቷ ሆሥፒታል እየተመላለሡ ወደ
አራት ወር ገደማ ተቆጠረ።....ድሮውንም ለስሙ እንጂ
ለቤተሠቡ ግድ የሌለው አባቷ ሆስፒታል መሄዱን እርግፍ
አርጎ ትቶት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ ሥራው
ተመለሰ.....ሠላም ግን ትምህርቷን አቋርጣ ዛሬም ከእናቷ ጎን
ካለው ወንበር ላይ ተቀምጣ ታሪክ ታነብላታለች።.......
ምክንያቱም ሠላም እናቷ ወ/ሮ ምእራፍ እንደምትሠማት
ታምናለች.....አንደበቷ ቢዘጋም ሠውነቷ ባይንቀሳቀሥም
አይኗ ባይገለጥም ውሥጧ ያዳምጠኛል በማለት ሁሌ
ታዋራታለች።.....
እለተ ሰንበት ሠላም በለሊት ተነሥታ ነጠላዋን በማጣፋት
ወደ ቤተክርሥቲያን ሄደች..
በጉልበቷ ተንበረከከችና እጇን ወደ ሠማይ ከፍ አድርጋ
"እግዛብሄር ሆይ አንተ ሠማይን ካለ ምሶሶ ያቆምክ
ጌታ....የአለማት ንጉስና ገዢ የሆንክ ጌታ እባክህ በርህን
ክፈትልኝ...የተዘጋጋብንን መንገድ ግለጽልን...እናቴን አድንልኝ
ተሥፋዬ አንተ ነህና".... በማለት ጸሎቷን አሠማች።...
እንደጨረሰች ነጠላዋን ሳታወልቅ ወደ ሆሥፒታሉ
አመራች.....ገርበብ ያለውን የእናቷን ክፍል ገፋ ሥታደርገው
ክፍሉ በሀኪሞች ተሞልቷል..
"እንዴ ምን ተፈጥሮ ነው" አንባረቀችባቸው...
ሁሉም ፈገግ አሉላት.."እናትሽ ነቅታለች ሠላም"...
በቆመችበት እዛው ወለሉ ላይ ፈጣሪዋን ለማመሥገን
ተነጠፈች....ወገቧን አሥጎንብሳ በውሥጧ አነበነበች....
ወዲያው ተነሳችና እማ እያለች ተንደርድራ ተለጠፈችባት ሁሉ
ነገሯን ትስማት ጀመር..እናቷ ግን ምንም መልስ
አልሠጠቻትም..
"እንዴ እማ እኔኮ ነኝ ልጅሽ ሠላም አላወቅሽኝም...?"
ከእናቷ የሚመጣ ምንም አይነት መልሥ የለም።....
ሠላም ወደ ዶክተሩ አፈጠጠችበት..
ሁኔታዋ የገባው ዶክተሩ "ነይ አንዴ እውጪ እናውራ" ብሏት
ይዟት ሄደ።..
"ሠላም እኛም አለመናገሯ እንግዳ ሆኖብናል...ድንጋጤና
ፍርሃቱም ሊሆን ይችላል...አሥፈላጊውን ምርመራ አድርገን
እናሳውቅሻለን"...
ሰልም ከዶክተሩ ጋር እንደተለያየች ለአባቷ ደወለችለት...
"ሄሎ ሠላሜ አዲሥ ነገር አለ...?"
"አዎ አባዬ እናቴ ነቅታለች"
"omg እንዴት ደሥ ይላል በቃ እዛው መጣሁ"...ሥልኩ
ተዘጋ....
"አንዱ ጣጣ ሲያልቅ አንዱ ይተካል ነቃችልኝ ብዬ ሥደሠት
ወዲያው
ይከፋኛል.....ቢሆንም በፈጣሪ ተሥፋ አልቆርጥም ይሄንንሥ
ማን አየበት በሂደት ደግሞ ትናገር ይሆናል።"በውሥጧ
እያሠላሠለች እናቷ ጋር ሄደች....
ከአልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ "እማ አሁን ወደ ቤትሽ
እንወሥድሻለን" እያለች እጆቿን ሳመቻቸው..
ወ/ሮ ምእራፍም ልቀፍሽ በሚመሥል እጇን አንከረፈፈችው
ሠላምም እጉያዋ ገባች።..
****-/////////**-*-----******
የሰላም አባት እንደደረሰ ምርመራው ተጠናቆ በነርሷ
ተጠሩ........ዶክተሩ ፊት ላይ ጥሩ ነገር
አይነበብም...ጭምት አድርጎታል..
አኳሁዋኑ ያላማራት ሠላም" ምርመራው ምን ያሳያል...?"
አለችው
"አዝናለሁ ወ/ሮ ምእራፍ መናገር አትችልም"
"ግራ የተጋባው የሠላም አባት እንዴት ሆኖ እራሷን መመታቷ
ከመናገሯ ጋር ምን ያገናኘዋል"...እንደመሳቅ አደረገው
ሠላም ዝምታን መርጣለች ብቻ ሁለቱም ጉንጮቿ በእንባ
እረጥበዋል።....
"ተረጋጉ ችግሩ ይሄ ብቻ ቢሆን ጥሩ ነበር"...
"ሌላ ደግሞ ምንድነው...?" በማለት ሁለቱም አይን አይኑን
የመውጋት ያክል እየተመለከቱ የከንፈሩን እንቅሥቃሤ
ይከታተሉ ጀመር።...
አባቷን ኮሪደሩ ጋር ስታየው እየሮጠች ሄዳ ተጠመጠመችበት....
......
"አባ እማ ምን ሆና ነው....? የት ክፍል ነች አሁን..?"
ጭምቅ አድርጎ ያዛትና" ደም ግፊቷ ጨምሮ ድንገት ከደረጃው ላይ ወድቃ ተንከባለለች".....
"እና አሁን እንዴት ናት....? ሄደን እንያታ"
"አሁን ማየት አንችልም...?"
"ለምን.....?"
"ጭንቅላቷ ውሥጥ ደም ስለፈሰሰ ቀዶ ጥገና ላይ ናት።"
ሰላም ይሄን ስትሰማ የሆስፒታሉ ወለል ላይ ተንፈራፈረች....ወዲያውም እራሷን ስታ እሷም አንዱ ክፍል አልጋ ያዘች።
ይቀጥላል
4 any comment👉@S_Viva
🌹እስኪ ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ ቻናሉን እናሳድገው...
So
💟በቀል💟
✅ክፍል 8⃣
.
.
👇👇👇✍✍✍❤️❤️👇
........ስልኳን አንስታ ቁጥሩን አወጣችና ልጫነው ወይሥ ይቅርብኝ እያለች ስታመነታ ድንገት ስልኳ ጮኸ....የሚያስፈራውን ዝምታም ባንዴ ገፈፈው.....
........አዎ ሚኪ ነበር የደወለው...ትንሽ እንደጠራ አነሳችው
"ሄሎ"...ፍርሃት ያዘለው ድምጽ
"ሄሎ ሰላም ሚኪ ነኝ"
"አውቄሃለሁ.....ልደውልልህ እያሠብኩ ነው የቀደምከኝ"
"እንዴት ነሽ ታዲያ በደንብ እራሥሽን ዘና አደረግሽ...?"
"አዎ አንተስ ክልኒክ ክንድህን ለሀኪም አሳየሀው...?"
"አይ ቀላል ነገርኮ ነው ቤት ገብቼ አልኮል ምናምን አደረግኩበት አያሳስብም"...
"እንደዛ ከሆነ ጥሩ...ምስጋናዬን በትንሹም ቢሆን ለመግለጽ ምሳ ልጋብዝህ እፈልጋለሁ"...
"ተገኝቶ ነው... ባንቺ መጋበዝ ማን ይጠላል ብለሽ ነው......ግን ሰላም ነገ ጠዋት ፊልድ ክፍለ ሀገር ልወጣ ሥለሆነ መጥፎ አጋጣሚ ሆነብን"...
"አይ አትጨናነቅ ችግር የለውም....መልካም ጉዞ"
"ሰሊና ድምጽሽ ቅር ያለው ይመስላል ከሳምንት በሁዋላ እመለሳለሁ....ያኔ እራሴ ደውዬ ነው የማስታውስሽ".....
"እሺ ቻው".....
ሰላም አውርታ እንደጨረሰች ሥልኩን አልጋው ላይ ወረወረችው....ያሰበችው ስላልተሳካና ሚኪን ለሳምንት ያህል እንዳማታየው ቁርጧን ስላወቀች ድብርት ውስጥ ገባች....ቢሆንም ድምጹን በመስማቷ ደሥ ብሏታል። ትራሷን አቀፈችና በእንግልሏ ተኛች......ጣራ ጣራውን እያየች"ግን ፈጠንኩበት መሰል.. እረ ሰላም ተረጋጊ የሌለብሽን አመል ከየት አመጣሽው" በማለት ከራሷ ጋር አጉተመተመች.........ክፍሉ የራሷን ሀሳብ እያስተጋባ ከየአቅጣጫው የሚያወራት መሰላት።.....ብቸኝነቱ ሲጨንቃት ተሥፈንጥራ ከአልጋዋ ወረደች።...የተፈጠረውን ሁሉ ሁሌም ለምታደምጣት ለእናቷ ልትነግራት..ስለሚሰማት ስሜት ልታወጋላት እናቷ ወደምታዘወትርበት የግል መናፈሻቸው በስሥ ውሥጥ ልብሥ አመራች።..ምክንያቱም እናቴ ምርጥ አዳማጭ ናት ብላ ታምናለች....ስትደርስ እናቷ በዛፎች በተከበበውና በአበቦች ባጌጠው ውብ ቦታ ላይ ተንፈላሰው ተቀምጠው አይናቸውን እያቁለጨለጩ ግቢያቸው ውስጥ የገባውን አየር ይምጉታል......የአበቦቹን መአዛ ብቻቸውን ይኮመኩምታል።....
"እንዴት ነሽልኝ የኔ ውብ እናት" አለችና ግንባሯን ስማ ከፊት ለፊት ያለው ወንበር ላይ ቁጭ አለች...
"እማ ዛሬ በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለወንድ ለረጅም ሰአት አሰብኩ....ልጁ ሚኪ ይባላል" ገና ተዋወቅን" በማለት ሁሉንም ነገር ዘረዘረችላቸው። እናቷ የሆነውን ሲሰሙ ልጄ አንድ ነገር ሆናብኝ ቢሆንስ በሚል በየመሀሉ ፊታቸውን ቅጭም ግንባራቸውን ኩሥትር ፈታ እያደረጉ አዳመጧት። ሠላም ወሬዋን ስትጨርስ "እና ምን ታስቢያለሽ እማ"..አለቻት
ግን መልስ የለም....ግቢው ጸጽታ ሠፈነበት....ከወፎች ዝማሬና ፉጨት በሥተቀር የሠው ድምጽ አይሰማም...
እናቷም አንገታቸውን በማነቃነቅ የሚሰማት ስሜት ጥሩ እንደሆነ በምልክት ነገሯት።....ሠላም በደሥታ ፍንድቅ ብላ ሳቀችና ተነሥቷ እጉያቸው ውሽቅ አለች...የእጃቸውን መዳፍ እያገላበጠች ሳመቻቸው...ግን ብዙም መቆየት አልቻለችም ሆድ ባሳትና ወደ ቤት ሮጠች...ወዲያውም ሊፈስ የተቃረበውን እንባዋን ዘረገፈችው። ሰላም ሁሌ እንዲህ ናት እናቷ ፊት ደሥተኛ ለመምሰል መሳቅና መጫወት ታበዛለች ተደብቃ ግን ታነባለች....የምታነባው በእራሷ ጉዳይ አይደለም። የምታነባው ስለ እናቷ ቢሆን እንጂ.....
-*---******/////*********
የሰላም እናት ወይዘሮ ምእራፍ ትባላለች.....ሽንቅጥ የቤት እመቤት ስትሆን...እድሜዋ በሰል ያለ ነው ግን ኑሮ ሥለተመቻት እድሜዋን አትመሥልም። ሠው ኑሮውን ነው የሚመሥለው ይባል የለ....
**--ከአንድ አመት በፊት****
እለተ ሰኞ የሠላም እናት እና አባት ይጨቃጨቃሉ ይጯጯሃሉ..
"አንተ ባለጌ እንዴት በስተርጅና ትንዘላዘላለህ....እንዴት የሰው መሳቂያ ታረገኛለህ"...
"ደግሞ ምን አባሽ ሆንሽ!"
"አንተ ወስላታ እንደምትማግጥብኝ የማላውቅ መሰለህ...."
"ባክሽ የሠው ወሬ እየሠማሽ አትጨቃጨቂኝ...ብዙ ሥራ አለብኝ ላንቺ አሉባልታ ጊዜ የለኝም"
"እና ይሄ ፎቶ ምንድነው....? እየሳምካት ያለኸው ልጅህ ናት.....? እንዴት ከምትወልዳቸው ልጆችህ ጋር ትንዘላዘላለህ..ትንሽ እንኳን ክብርህን አጠብቅም ክብረ ቢስ.....እሥከዛሬ የሆዴን በሆዴ አድርጌ የታገሥኩህ ለልጃችን ብዬ ነበር አሁን ግን በቃኝ የእኔና ያንተ ነገር ማብቃት አለበት"....ተንዘፈዘፈች....ወ/ሮ ምእራፍ እንደ አንዳች ተቀያየረች
"ቆይ አንቺ ይሄን ሁላ እንዴት አወቅሽ ሥትከታተይኝ ነበር..?....አንቺ አሮጊት ከኔ ጋር በመሆንሽ ብቻ መላው የሀገሪቱ ህዝብ እንደሚያከብርሽ አታውቂምን...አንቺ ውለታ ቢስ" በማለት በእጆቹ ገፈተራት.....
ወ/ሮ ምእራፍም ከደረጃው ላይ ተንከባለው ወለሉ ላይ ዝርግትግት ብለው ወደቁ። ይሄን ያላሰበው የሠላም አባትም የሚያደርገው ጠፋውና ድንግርግር አለው...እንደምንም እራሱን አንቀሳቅሶ የግቢውን የጥበቃ ሰራተኛ ጠራና ለሁለት ተረባርበው የካቲት 22 ሆስፒታል አደረሷት።...
የሆስፒታሉ ዶክተርና ነርሶች የወ/ሮ ማራማዊትን ነፍስ ለማትረፍ እየተንጋጉ ወደ ድንገተኛ ክፍል ገቡ....ከሰአታት በሁዋላ ነፍሷን ታድገዋት የድንገተኛው በር ተከፈተ.....
ዶከተሩ እንደወጣ አከባቢውን በመቃኘት የወ/ሮ ምእራፍ ቤተሠብ የታሉ....? በማለት ጠየቀ...
የሠላም አባትም ከመንደርደር ባልተናነሠ እርምጃ በመሄድ "ዶክተር እኔ ነኝ....እንዴት ናት?"
"ተከተለኝ ቢሮ እንግባና እንነጋገር"
ከፊትና ከሁዋላ በመሆን ተከታትለው ቢሮ ገቡ....
"እባክህ ተቀመጥ"
"እሺ አመሠግናለሁ"....
"ከታካሚዋ ጋር ምንድነው ዝምድናህ...?"
"ባለቤቷ ነኝ"
"እንግዲያውሥ መነጋገር እንችላለን....እየውልህ የባለቤትህን ነፍስ ለጊዜው አቆይተናታል"
"እንዴ ምን ማለት ነው አቆይተናታል....ህይወቷ አደጋ ውሥጥ ነው እንዴ....?"
"አዎ ካልፈጠንን እንዳልከው ነው....የልብ ምቷ ከተሥተካከለ በሁላ የተለያዩ ምርመራዎችን አድርገንላታል....የምርመራው ውጤት ግን መጥፎ ነው ሥትወድቅ ክፉኛ በመመታቷ የጭንቅላት ደም መፍሰስ አጋጥሟታል"....
"ምን ለማለት ፈልገህ ነው እሥቲ በግልጽ ንገረኝ"
"በፍጥነት ቀዶ ጥገና ካልተደረገላት አትተርፍም"
"ዶክተር የሚደረገውን አድርጉና ሚስቴን አድኗት....የገንዘብ ችግር የለብኝም ብቻ አትርፉልኝ"
"የቻልነውን ሁሉ ለማድረግ እንሞክራለን....ግን እዚህች ሰነድ ላይ መፈረም አለብህ"...ዶክተሩ ሰነዱን አሥፈርሞ እንደጨረሰ ነርሶችንና ለቀዶ ህክምናው የሚረዱ መሳሪያዎችን በማሥከተል ወደ ወ/ሮ ምእራፍ ክፍል ዘለቀ።....
የሠላም አባትም ልጁ ስለ እናቷ ሁኔታ ማወቅ አለባት ብሎ ስላመነ ደወለላት.....
ሠላም ትምህርት ላይ ስለሆነች ሲጠራ እያየችው ችላ አለችው።....ደጋግሞ ሲጠራ ግን አሳሳቢ ነገር እንደሆነ በመገመት መምህሯን አሥፈቅዳ በመውጣት አነሳችው....
"አባ ትምህርት ላይ ሁኜኮ ነው ዝም ያልኩህ...ደጋግመህ ደወልክ በሰላም ነው....?"
"ልጄ" አላት ሲቃ በተናነቀው ድምጽ
"እንዴ አባ ድምጽህ ልክ አይደለም ምን ተፈጠረ..?"
"ተረጋጊ ልጄ.....ቀላል ነው እናትሽን አሟት የካቲት 22 ሆስፒታል ነን።ሁሉንም ሥትመጪ እነግርሻለሁ"
ሠላም እቃዋን ክላሥ ባለበት ትታ ወደ ሆስፒታሉ እየበረረች ሄደች።.....
ማዳመጧን ቀጠለች...
"እሺ ታዲያ ፍቅር ካላፈዘዘህ የታለ ያቀድነው ገንዘብ....? ታውቆሃል እሥካሁንኮ ድንብሎ ሳንቲም እንኳን አላመጣህም"...
"ልጅቷ ግምጭጭ ያለች ነች..ከንፈሯን እንኳን አላሣመችኝም...ሁሌ ገና መች አወቅኩህና ትላለች...ግን እመኝኝ በቅርብ ጊዜ ይዤያት እተኛለሁ...ከዛ በእውኗም በህልሟም እኔን ማሰብ ትጀምራለች...ያኔ ሀብቷን እንዘርፋለን....ውዴ እናልባታለን እያልኩሽ ያውም በቅርቡ"..
"እሺ ናልኝ የኔ ፍቅር ናፍቀሀኛል"..የሸሚዞቹን ቁልፍ እየፈታች ትመጠምጠው ጀመር።..
ይሄን ሁሉ ያዳመጠችው ሠላምም ከመቅጽበት ገርበብ ያለውን በር በርግዳው ገባች..ሶስቱም ደነገጡ ሌላ ትእይንት..ሌላ ድራማ...ከመሣይ ጋር ሥታወራ፤ሥትሣሣምና ሥትተሻሽ የነበረችው የሠላም የልብ ጓደኛዋ ናት።.....
ሰላም አገባቧ መሣይን እጅ ከፍንጅ ይዛው ዳግመኛ አጠገቧ እንዳይደርሥ ልታሥጠነቅቀው ነበር...አብራው የነበረችው የምትወዳት የልብ ጓደኛዋ መሆኗን ሥታይ ግን ያየችውን ማመን ተሥኗት ባለማመን ውሥጥ ሰምጣ አንደበቷ ተዘጋ...ልቧ ክፉኛ በመሠበሩ እነሡን በንዴትና በብሥጭት ከመናገር ይልቅ ወደ ቤቷ መሮጥን መረጠች...እዛው ባሉበት ጥላቸውም ተፈተለከች።...ከዛች ቅጽበት በሁዋላ የሴትም ሆነ የወንድ ጓደኛ የላትም...
በጣም ቆንጆ ሥለሆነች ካምፓሥ ላይ ብዙ ወንዶች ቢያንዣብቧትም ለማንም ፊት ሳትሠጥና እራሷን በትምህርት ቢዚ እንዳደረገች ይሄው የዛሬዋ ቀን ላይ ደርሣለች።......
ሰላም አሁን መኝታ ክፍሏ ገብታና በእንግልሏ ተኝታ ሥለ አንድ ሠው እያሠበች ነው....አዎ ሥለ ሚኪ እያብሠለሠለች ነው....አንድ ላይ ወድቀው አይን ላይ ከተተያዩበት ቅጽበት ጀምሮ እሥኪለያዩ ድረሥ የነበረውን አክሽን በፓርት በፓርት አድርጋ እየደጋገመች ትኮመኩመዋለች...
ላቧን ሲያደራርቅላት....ግንባሯን አይኖቿን አፍንጫዋንና የድንግሉን ከንፈሯን ጥግ በሶፍት ሲነካካው የነበረውን ሂደት መልሳ መላልሳ ታሥበዋለች....
በተለይ "እንዳንቺ አይነት ውብና ደግ ሴት በመተዋወቄ ሎተሪ የወጣልኝ ያህል ነው የተሠማኝ" የሚለው የሚኪ ድምጽ ጆሮዋ ላይ እያቃጨለባት ፍንድቅድቅ አረጋት..በሆዷ ተኝታ እግሯን እንደ ህጻን እያወዛወዘች ትሥቃለች።....ሥለ ወንድ እንዲህ ሥታሥብ የመጀመሪያዋ ነው.....ህይወቷን አትርፎላት ጀግናዋም ሥለሆነ ሊሆን ይችላል..አዎ ሴቶች በመጥፎ ጊዜ የደረሠላቸው ጀግናቸውን ከአይነ ህሊናቸው አያወጡትም ይባል የለ...ብቻ ግን ሚኪ የሆነ ነገሩ ስቧታል..ከአእምሮዋ ልታወጣው አልቻለችም።..
ሳታውቀው ድምጽ አውጥታ "ግሩም ሠው ነው" አለች.. ጸጽታ የሠፈነበት ክፍሏም ይሄንኑ አሥተጋባው.....ሥልኳን አንሥታ ቁጥሩን አወጣችና ልጫነው ወይሥ ይቅርብኝ እያለች ሥታመነታ ድንገት ሥልኳ ጮኸ...የሚያሥፈራውን ዝምታም ባንዴ ገፈፈው.............
ይቀጥላል
