en
Feedback
Nathan casting agency

Nathan casting agency

Open in Telegram

The best place to get the best casting jobs Our services -casting models - for music clips - movies - series dramas - fashion shows - television shows Contact: 0920358051

Show more
Ethiopia16 170The category is not specified
408
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
the bakery አዳዲስ english music ማግኘት ከፈለጉ join በማድረግ ወዳጆን ይጋብዙ @fkrnahiwot @fkrnahiwot

🎙YG • 2020 🎼Out On Bail @fkrnahiwot @nahita2

​​​​​❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ ሰባት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ በፍጥነት እንዲደርስዎ ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ!!! ሄኖክ ወደተላከለት አድራሻ በፍጥነት መሄድ ጀመረ ማንነቷ አላሳሰበውም ፍሎራን ልቶን ትችላለች ብሎ ገምቷል ... ልክ ሲደርስ ኤልሳን ተመለከታት ልክ ሲያያት የደነገጠው መደንገጥ ልብ ድካም ቢኖርበት ፀጥ ያደርግ ነበር እሷም ልክ ስታየው እየሮጠች እግሩ ላይ ወድቃ ልጄ ሊሞትብኝ ነው በግሉኮስ ሀይል ነው ያለው ከወላጅ አባቱ ደም ያስፈልጋል ተባልኩ እናም ውዴ በፍቅራችን ይዤሃለው ልጄን አድንልኝ አለች ስቅስቅ እያለች በሚያሳዝን አንደበት... ሄኖክም በንዴት ጦፎ ... ቆይ አንቺ ምን አይነት እራስ ወዳድ የማይገልፅሽ ሴት ነሽ ለምን በሰው ህይወት ትቀልጃለሽ ማነው ቆይ መለወጤን የሚነግርሽ ሁሌም ባንቺ እቆስላለው ከዛ ልክ ሲሻለኝ ትመጪና ዳግም ታቆስይኛለሽ... አለ ንዴትና ሀዘን ተደምረው አንደበቱ ቃል ለማውጣት እየቸገረው... ኤልሳ ግን መማፀኗን ቀጠለች ልጄ ልጅህ ነው እባክህ ሄኒ የኔን አትይ አሁን ለልጅህ ስትል ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ከዚ ቡሃላ እንዳትደርሺብኝ ህይወቴ ውስጥ ስትፈልጊ መግባት ሳትፈልጊ መውጣት የምትችይ ይመስልሻል ይሄኮ የህይወት ጉዳይ ነው ብሎ ገፍትሯት ሊሄድ ሲል እሺ እውነቱን ልንገርህ ለትንሽ ደቂቃ አድምጠኝ አለች ማልቀሷን ሳታቆም... ሄኖክም ጀርባውን እንደሰጣት ቆም አለ... እኔ ድሮም ሆነ አሁን ካንተ በቀር ማንንም ማፍቀር አልችልም ባሌም ቢሆን የልጄ አባት እንዳልሆነና እንደማላፈቅረው ያውቃል!! ግን የግድ እኖራለው ይህም የሆነው ... ያኔ ካምፓስ እያለን ካንተ አረገዝኩ ማሶረድ ብፈልግም አልቻልኩም ምክንያቱም ያንተ ስጦታ ልጄ ብቻ ነው... እናቴ ደግሞ ልጄ ተመርቃ አያለው ብላ በጉጉት ትጠብቅ ነበር ጉዷን አላወቀችም ከዛ አባቴ ባጋጣሚ ባልሰራው ወንጀል ታሰረ ይሄኔ እናቴ በኪራይ ቤት ልጅ ይዛ ተቸገረች ያሁኑ ባለቤቴ ደግሞ ችግራችንን ያውቅ ስለነበር አባዬን ብዙ ገንዘብ ከፍሎ አስፈታው ቤት ገዛልን እኔንም እንድመረቅ ይረዳኝ ጀመር ግን እናቴ ማርገዜን ስትሰማ ደሟ ከፍ ብሎ ላትመለስ አጣኋት... አሁን አባቴ ያለው ባሌ በገዛልን ቤት ውስጥ ነው እኔ አልፈልግም ብዬ ብፈታው አባቴን እንዳስፈታ አርጎ ያሳስርብኛል አባቴ ላይ ይህን መፍረድ አልችልም በእማዬ ይብቃ ...በቃ ከዚ በላይ ምንም አልልህም አሁን ሂድ ግን እንዳትረሳ እኔም ልጄም እኖድሃለን አለች ተስፋ በቆረጠ አስተያየት እያየችው.... ሄኖክ ጮሆ ቢወጣለት ደስ ባለው ግን አልቻለም ኤልሳም ከሱ ባላነሰ ፈተናዎችን አሳልፋለች ሊያውም ለሰው እንኳ የማይነገር የማይታይ ችግር ... ሄኖክ ግዜ ሳያጠፋ ልጁን ለማዳን ሄደ... ኤልሳንም አቅፎ አባበላት ግን ምንም ሊላት አልፈለገም ... ልጁን ሲያየው ደስታ ይሁን ሀዘን የማያውቀውይ ስሜት ሰውነቱን ይወረዋል ... የኛስ ይሁን ይሄ ህፃን ልጅ አያሳዝንህም እያለ ፈጣሪን መውቀስ ይጀምራል ... ሄኖክ ልጁን አዳነ ከዛም ለኤልሳ ስለፀሎት ነገራት ለሱ በሱ ምክንያት የሆነችውንና አሁን ሊክሳት እንደሚፈልግ ሲነግራት ኤልሳ ውስጧ በቅናት አረረ ...ግን ሲለያዩ መልካም እድል ከማለት ውጪ ምንም አላለችም እሱም በቀጥታ ፀሎትን ያየበት ቤት ሄደ... ልክ ደርሶ ሲያንኳኳ በር ተከፈተለት አባቷ ነበሩ ገና ሲያዩት ልጄን ልጨርስብኝ ነው አሉ በሄኖክ ድፍረት የተገረሙ በመምሰል...እሱም ገና ፀሎት ከማለቱ ማነው አባዬ አለች ፀሎት ዊልቸሯን እየገፋች ውጪ የቆመውን ሰው ለማየት ጓጉታ............ .............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━

​​​​​ ❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ ስድስት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ሄኖክ ሲወድቅ ሁሉም ደንግጠው ከበቡት ፀሎት ግን መቆም ስለማትችል እዛው ሆና ማነው ፍሎራ ምንድነው ንገሩኝ ትላለች ፀሎት ሳታየው አፋፍሰው ወደ ሀኪም ቤት ወሰዱት ከረጅም ሰዓታት ቡሃላ ሄኖክ ነቃ ዞር ብሎ ሲያይ ፍሬ እጁን በጇ ይዛ አልጋው ጠርዝ ላይ አቀርቅራለች ይሄን ሲያይ እንባው በጆሮው በኩል ይንቆረቆር ጀመር ፍሬም ቀና አለች ስታየው ነቅቷል እኔ አላምንም የኔ ውድ ነቃህ ብላ እጁን እየሳመች የደስታ እንባዋን ዘረገፈችው እሱ ግን ያቺ የሱን ሀዘን የማትሻው ፍልቅልቋ ፀሎት አሁን መራመድ አቅቷት በሰው ስትገፋ ማየቱ ይህ የሆነው ደግሞ በራሱ ጥፋት መሆኑን እያሰላሰለ ነው እንባው የሚወርደው... ፍሬም እንባዋን እየጠረገች እሱን ማባበል ጀመረች ሄኖክም የተሰካለትን ግልኮስ ነቅሎ እወጣለሁ አለ ፍሎራ አይሆንም ሀኪሞቹ ሲሉ ትወጣለህ አለች እንደመቆጣት እያረጋት ሄኖክ ግን ማንንም መስማት አልፈለገም ፍሎራ ኮንትራት ታክሲ ጠርታ እሺ ግን እዛ ሆቴል አሎስድህም እኛ ቤት ትቆያለህ አለችው ሆቴል ነው የምሄደው አላት ልዝዝ ባለ አንደበት ... ታክሲው መቶ መንገድ ሲጀምሩ ምን ሆኖ እንደሆነ ለማወቅ የነበራት ጉጉት ጨመረና የኔ ውድ ግን ፓርቲው ላይ ምን አይተህ ነው የደነገጥከው? ስትል ጠየቀች ሄኖክም የሀጥያቴንና የበደሌን ዋንጫ ግቢያቹ ውስጥ አይቼ አላት ...በጣም ግራ ተጋብታ አልገባኝም አለች መቼም አይገባሽም አንቺን አለና ጮክ ብሎ እየውልሽ ፍሎራ ስለኔ ምንም አታውቂም ግን ከዚ ቡሃላ ወደራሴ እንድመለስ እርጂኝ ይሄን አስመሳይ ማንነቴን ሳይሆን ትክክለኛ እኔነቴን እፈልገዋለው ... አላት "OMG እኔ ጭንቀት አልችልም በግልፅ ምን እንደተፈጠረ ንገረኝ" አለች... ግዜው ሲደርስ ይገባሻል እስከዛ ግን ከዚ ቡሃላ ከኔጋ ፍቅር ምናምን የሚባል ጨዋታ የለም አለና ገና ሳይደርስ ወራጅ አለ ብሎ ወረደ ፍሎራ ነገሮች የሚሆኑት በህልሟ መሰላት እሱ ሲወርድ እሷ በድንጋጤ ፈዛ ስለነበር እዛው ቀረች... ሄኖክ ስለ ፀሎት ለማሰብና እንዴት ዳግም ሊክሳት እንደሚችል ያስብ ጀመር ሆቴል ውስጥም ገብቶ እንደቀድሞው ሴቶችን ማማለል አይፈልግም እንዲያውም በተቃራኒው ኮስታራ ሆነ ያም ሆኖ ግን ስራውን ቀጥሏል ፍሎራ እሱን ብላ መመላለሷን ቀጥላለች ... አንድ ቀን ፍሎራ ወደሄኖክ በመቅረብ እየውልክ ሄኒ የቀልድ ብንጀምርም አሁን ከልቤ አፈቅርሃለው ስለዚ እንድትጎዳኝ አልፈቅድልህም አለች እሱም ትከሻዋን ያዝ አድርጎ እኔ የማፈቅራትና የምታፈቅረኝ ሴት አለችኝ አንቺ ለግዜው አሜሪካ እስክትመለሽ የቀረብሽኝ ስለመሰለኝ ልቤን አልከፈትኩልሽም እናም ፍሎሪ እባክሽ ከዚ ቡሃላ እራቂኝ አለ... ፍሎራ ግን አልችልም ነበር መልሷ አንድ ቀን ታድያ አንዲት ትንሽዬ መናፈሻ ስር ቁጭ ብሎ እንዴት ብሎ ፀሎትን አግኝቶ እንደሚክሳት እያሰላሰለ ስልኩ ጠራ ለማንሳት ብዙም ደስ ስላላለው አይቶ ዝም አለ ስልኩ ግን ደግሞ ጮኸ አንስቶ ገና ሄሎ ሳይል እርዳኝ እባክህ ልጄ ሊሞት ነው አለች አንዲት እያለቀሰች ያለች ሴት ድምፁ አዲስ አልሆነበትም ማነሽ አለ ከተቀመጠበት እየተነሳ... አድራሻ እልክልሃለው አሁኑኑ ድረስልኝ አለች........ .............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━

​​​​​ ❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ አምስት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ሄኖክ በባህር አቋርጦ ከሀገር ለመውጣት ብዙ መንገድ ተጉዞ ነበር ነገር ግን ሳይሳካለት ቀርቶ በ3ወሩ ከሱዳን ተመለሰ እስከዛች ቀን ድረስ ፀሎት ሀኪም ቤት ቤቷ ሆኖ ነበር አባቷም ከልጃቸው ምንም ስለማይበልጥ ስራቸውን መስዋዕት አርገው ከሷ አይጠፉም ሄኖክም ከሀገር ወቷል ብለው በማመናቸው ልጃቸውን ቀስ በቀስ ብትረሳው ብለው ብዙውን ግዜዋን ሄኖክን የሚያስረሳ ነገር ያደርጋሉ ነገር ግን ከሀገር መውጣቱን አልነገሯትም... ሄኖክ ከሱዳን ከተመለሰ ቡሃላ እጁ ላይ አምስት ሳንቲም አልነበረም የነበረችውንም ብር ለደላላ ከፍሎ ጨርሶታል ይሄኔ ምንም ምርጫ ስላልነበረው 2ቀን ከአንድ ሆቴል በር ላይ አደረ በ3ኛው ቀን ግን እዛ ያዩት የሆቴሉ ባለቤቶች በጥበቃነት እነሱ ጋር እንዲሰራ አነጋገሩት መጀመርያ ላይ እንዴት ተምሬ እንዳልተማረ ጥበቃ እሆናለው ሲል አሻፈረኝ ብሎ ነበር ግን በረንዳ ከማደርና ለሲጋራ ከመለመን ይሻላል ሲል እራሱን በራሱ መከረ ... የሆቴል ጥበቃነት ሲቀጠር ባለቤቱ እንቅልፍ እንዳይዝክ ለሊት እየጠበክ አንብብ ሲል መፅሃፎችን ይሰጠው ጀመር ... ሄኖክ ማንበብ ሲጀምር አስተሳሰቡ መቀየር ጀመረ የመጀመርያ ግዜ (ፀሀፊውን ባላስታውሰውም) የቢሆን አለም የሚል አሳዛኝ ልቦለድ ነበር ያነበበው እዛ መፅሀፍ ላይ ብዙ ለፍቅር ተብለው የተከፈሉ መስዋዕቶችን አነበበ ከዛም ግን እራሱን በባለታሪኩ ቦታ አድርጎ ሲያየው የኔ ፈተና ምንም አይደለችም ሲል ያስባል ይመልስና ደግሞ ይሄ ልብ ወለድ ነው እንደኔ በፍቅር የተገፋ የለም ሲል ያማርራል ... በዚ ሁኔታው ወር ከ15 ቀን ከሰራ ቡሃላ ሰውየው የሄኖክን ቁመናና ውበት አይቶ ስራ ሊቀይርለት ወሰነና ጠራው ሄኖክም ወደ ሰውየው ሄዶ አቤት አለ ሰውየውም ካሁን ቡሃላ 4የምታጨሰውን ቀንስ ከዛ አለባበስህን ሁሌም አስተካክል እና ሆቴሌን ከኔ ስር ሆነህ ትቆጣጠራለህ (ሱፐር ፋይዘር ) ትሆናለህ አለው ሄኖክም ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ታየው በሀሳቡም ተስማማ ከዛች ቀን ቡሃላም እንደ ሄኖክ ዘናጭ የለም እሱን ብለው የሚመጡ የከተማዋ ቆነጃጂቶች በዙ ሁሌም ቢሆን ከደሞዙ ይልቅ የሚሰጡት ቲፖች ብዙ ናቸው ... ታድያ ሄኖክን ልጋብዝህ የማትለው ሴት የለችም ከታዳጊ እስከ አሮጊት(ሹገር ማሚ) ሄኖክን ይመኙታል እሱም ይሄ ያስደስተዋል ሁሌም አንድ አባባል አለው ሴት ልጅ ስቶዳት ከሀዲ ናት ስትገፋት ደግሞ ፈላጊ ናት ይላል...ይሄ አባባሉ በኤልሳ ከተጎዳ በኋላ የመጣ ነው... ሄኖክ ገንዘብ ከምትሰጠው ሴት ጋር ግዜ ያሳልፋል ሲሰለቸው አይንሽን አልይሽ ብሎ ያባራታል... ከዛ ብታለቅስም ግድ አይሰጠውም በዚ ሁኔታው ሴቶችን ማማለልና መጉዳቱን ከስራው በላይ ይዘጋጅበት ነበር አንድ ቀን ታድያ አጋጣሚ ከአንዲት ፍሬ የምትባል ቆንጂዬ ልጅ ጋር ይተዋወቃል ልጅቷ ከአሜሪካ ለመዝናናት ነበር የመጣችው ስታየው ወደደችው እሱም ከሌሎቹ የተሻለ ግልፅነቷ ተመችቶት ከስራ በኋላ እሷን ማግኘት ስራው ሆነ ... ሲያገኛት ሁሌም ግጥምና ልብ ወለድ ታሪክ ያነብላታል ከዛም አልፎ እሷ እሱን የምታፈቅርበትን የተለየ ነገር ያደርጋል ... ቀስ በቀስ ከሄኖክ ውጪ ሰው የለም አለች እሱ ግን ፈፅሞ በልቡ ቦታ አልሰጣትም... ሁሌም ስለአንድ የልጅነት ጓደኛዋ ትነግረዋለች... ጓደኛዋ አሁን ከቤት አትወጣም በድንገት በገጠማት ችግር ማለትም ፍቅረኛዋ ጥሏት ከሀገር መውጣቱን ስትሰማ በንዴት ከፎቅ ላይ ወድቃ እግሮቿ መራመድ እንደማይችሉና እቤት እንደምትውል ስትነግረው ያፈቀረችው ወንድ ታድሎ ይላታል እሷም ፈገግ ብላ አንተ ግን ጥለኸኝ የትም አትሄድም አይደል ትለዋለች እሱም አንቺ ወደ አሜሪካሽ ልትሄጅ አይደል ይላታል ... እሷ ግን ሄኖክን ጥሎ መሄድ ሞት መስሏታል ... ይህ በንዲህ እንዳለ አንድ ቀን ፍሎራ ለሄኖክ ደውላ የዛች አካል ጉዳተኛ ጓደኛዋ ልደት ስለሆነ ቤታቸው ብሮግራም አዘጋጅታ ጠራችው ያ ቀን መሄድ እየቀፈፈው ከላይ እስከታች ዝንጥ ብሎ ሄደ ደርሶ ልክ በሩ ሲከፈት ባለልደቷ ያቺ ፍልቅልቋና ማራኪዋ ፀሎት ሆና ያገኛታል ልደቷን ዊልቸር ላይ ተቀምጣ ስታከብር ደረሰ በሱ ምክንያት መሆኑን ለመገመት ሰከንዶች በቂ ነበሩ በኤልሳ ስራ ልቡ ታውሮ የገፋት የህይወቱ ድንቅ ሴት ... ሄኖክ ምድር ዞረችበትና በቁሙ ተዘረረ....... .......ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━✦✿✦━━━━━━━

❤️❤️😭😘 join @fkrnahiwot

0.75 KB

0.86 KB

1.37 KB

ተወዳጁ❤️❤️ክፍል 15አሁን እንዲለቀቅ ሚፈልግ ካለ👍

❤​​​​​ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ አራት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ሄኖክ የኤልሳ ማግባት አረጋግጦ ሲመለስ ላየው ሰው የአይምሮ ችግር ያለበት ይመስል ነበር ብቻውን እያወራ ብቻውን ይስቃል ኤልሳ ባል እያላት ለምን ወደ ህይወቱ በድጋሚ እንደመጣች ሲያስብ ግራ ይገባዋል ... አሁን ብቸኛ የነበረችው ተስፋ ፀሎትም እርቃዋለች ሄኖክ በድጋሚ ትምህርት አቆመ ሴት ልጅ ሲያይ ይሸሻል ብዙ በፊት የሚያቁት ሰዎች "ሄኖክኮ ነቀለ" እያሉ ያፊዙበታል እሱም ቢሆን ምን ቅንጆ ቢሆንምና ያየችው ሴት የምትማለልበት አቋም ቢኖረውም አሁን ላይ ግን ልብሱን እንኳ አይቀይርም ከወር እስከ ወር ይለብሰዋል ማጨስ መቃም መጠጣት የግሉ ሆኑ ቁም ነገር ስራበት ተብሎ የተቀመጠለት ገንዘብ ግማሽ ደረሰ... አንድ ቀን እንደተለመደው ብቻውን እያወራና እየሳቀ ሲሄድ ፀሎት ከአባቷ ጋር ወክ ታደርግ ነበር ስታየው ማመን አቃታት እንደዚ እራሱን ጥሎ ይሆናል ብላ አስባ አታውቅም ... ሄኖክ ልክ ሲያያት ከት ብሎ ሳቀ ፀሎትም እንባዋን መቆጣጠር አቃታት ወደሱ ስትቀርብ እሱ ግን ጥሏት ሮጠ ይሄኔ ፀሎት እዛው አስፓልት ላይ እራሷን ስታ ወደቀች... አቧቷም ልጄ ብለው በመጮህ መንገደኛውን እርዳታ በመጠየቅ አንስተው ወደ ሆስፒታል ወሰዷት... ፅሎት የልብ በሽታ ስላለባት መጨነቅና መደንገጥ ከመሳሰሉት ነገሮች መራቅ አለባት ብለዋል ሀኪሞቹ ይሄም የሚሆነውና ፀሎት ደስተኛ መሆን የምትጀምረው ሄኖክን ከጎኗ ስታገኝ ነው... ይሄም እንዲሆን አባቷ ነገሩ ስላልገባቸው ፀሎት ስታገግም ስለተፈጠረው ጠየቋት ፀሎትም እንባዋ ያለገደብ እየወረደ አባዬ ሄኖክን አፈቅረዋለው እሱ እንደዚ የሆነው እኔ ጥዬው ስለሄድኩ ነው ፈልግና አምጣልኝ ልክሰው እፈልጋለው አለች አባትየውም ልጃቸውን እናትም አባትም ሆነው ስላሳደጓት በሷ መጨከን አይችሉምና ሄኖክን ማፈላለግ ቀጠሉ... ታድያ አንድ ቀን ሰፈር ውስጥ በተለምዶ ድድ ማስጫ የሚባል አካባቢ ተቀምጦ አገኙት አለባበሱም ሆነ ሁኔታው እንኳን በልጃቸው ሊፈቀር የልጃቸው በር ጠባቂ እንዲ ሆን ባልፈቀዱለት ነገር ግን አሁን ላይ ያን ማሰብ አይችሉም ምክንያቱም ልጃቸው የሞት አፋፍ ላይ ናት እየቀፈፋቸው ተጠጉትና ልጄ ደና ነህ አሉት እሱም ቀና ብሎ ገልመጥ አረጋቸውና ከኪሱ ሲጋራ አውጥቶ ለኮሰ ይሄኔ በንዴት ጦፈው እንዳንተ አይነቱን ጋጠወጥማ ልጄ ፀሎት አታፈቅርም አሉ ሄኖክ ገና ፀሎት የሚለውን ስም ሲሰማ እንባው መንታ መንታ ይወርድ ጀመር ሰውየውም ትተውት ሊሄዱ መንገድ እንደጀመሩ ልጃቸውና ጭንቀቷ ትዝ አላቸው ከዛም መለስ ብለው ልጄን አድንልኝ እባክህ አሉት ሄኖክም እርሶም ጥቅመኛ ኖት? ከትከትከት ሆ እርሶም እንደ ኤልሳ ጥቅም ያታልሎታል? ካካካካ ትተውኝ ሊሄዱ መንገድ ጀምረው ሲያበቁ ተመልሰው ይለምኑኛል? አለና እያነባ ትቷቸው ሄደ ከዛ ቀን ቡሃላ ሄኖክን አየው የሚል ጠፋ ፀሎት ሄኖክን እያለች ከሆስፒታል ሳቶጣ ድፍን 20 ቀን ሞላት አባትም የልጃቸውን መድሃኒት ሄኖክን ፍለጋ ተያይዘውታል... ልክ በ24ኛው ቀን ሄኖክን አየው የሚል ሰው ተገኘ በሊቢያ በኩል አድርጎ ከሀገር ሊወጣ መሆኑን የፀሎት አባት አወቁ ለማስቆም ግን ግዜው ረፍዷል ያ ካልሆነ ደግሞ ፀሎት በርግጠኝነት ትሞታለች ምክንያቱም ጥዬው ባልሄድ እንዲ አይሆንም ነበር ብላ ታምናለች........ ............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━

@fkrnahiwot @Nahita2🎤🎹🎸🎺🎷🎻🎼....👌👌😍😍😋

@fkrnahiwot @nahita2 🤔🤔🎤🎷🎻🎺🎼🎹 at

​​​​❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ ሶስት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ሄኖክ ምን ማድረግና ማንን መምረጥ እንዳለበት ግራ ገባው የልጁን እናት ኤልሳን ወይንስ ከብዙ ፈተናዎች ታድጋ በስተመጨረሻ መልካም መንገድ እንዲጓዝ የረዳችውን ፀሎት... ይሄን መምረጥ ለሱ ትልቅ ፈተና ነበር ኤልሳን ሲያገኛት በርግጥ ፍቅሩ አገርሽቶበታል በዛ ላይ ልጅ ከሷ አለው ግን ደግሞ ፀሎት ማለት እናቱ ነች ያላትን ፍቅር ሳትሰስት ለግሳ ከመጥፎ መስመር መልሳና መጥፎ ትዝታዎችን አስረስታዋለች... ለዛም ነበር ልጅ እንዳለው እንኳ ነግሯት ቅስሟን መስበር ያልፈለገው... ሄኖክ በድጋሚ ጭንቀቱን ለመርሳት ሲል ማጨስና መጠጣት ጀመረ ትምህርት ቤት ከሚሄድበት የማሄድበት ቀንይበልጣል ባጭር ቋንቋ ሄኖክ ልክ እንዳለፈው ሱስ ውስጥ ተዘፈቀ ይሄኔ ነበር ፀሎት አንድ ነገር እንድተፈጠረ የጠረጠረችው... ሄኖክን ከመሸሽ ይልቅ ቀርባ ልትረዳው ሞከረች ፀሎት በተፈጥሮዋ ብዙ ፈተናን መጋፈጥ አትችልም በዛ ላይ የልብ በሽተኛ ነች ትንሽ ጭንቀት ይጥላታል ለዛም ፀሎትን የሚያስደነግጣት ነገር መፈጠር የለበትም አንድ ቀን ሄኖክና ፀሎት ሰፈር ውስጥ ተቀምጠው ፀሎት እንደተለመደው ሄኖክን ለማዝናናት የባጥ የቆጡን ትለፈልፋለች ይሄኔ ኤልሳ ሳያስቡት መጥታ ከፊት ለፊታቸው ቆመች ትንሽዬ የሚያምር ህፃን ይዛለች ሄኖክ በድንጋጤ ከተቀመጠበት ተነሳ ኤልሳም እኔና ልጄ ሰላም ልንልህ ነው የመጣነው አለች ሄኖክም ፀሎት ከዚ በላይ ከሰማች ስለምትደነግጥ የት ታቂኛለሽ እብድ ነሽ እንዴ ሴትዮ ብሎ ፀሎትን እየጎተተ ይዟት ሄደ ግን እንዳሰበው ፀሎትን መሸወድ አልቻለም እውነቱን እንዲነግራት አፋጣ ያዘችው እሱም እንድትረጋጋ ካደረጋት ቡሃላ ስለኤልሳና ሜላት ይነግራት ጀመር... ፀሎት ኤልሳን ማፍቀሩንና የልጅ አባት መሆኑን አምኖ መቀበል አቃታት በዚም ልትርቀው ወሰነች ሄኖክ በድጋሚ የሚወደውንና የሚያስብለትን ሰው አጣ ... ዶጮም እንደመጀመርያው አያገኘውም ሄኖክ ግን ያለው አማራጭ ዶጮን ፈልጎ ማግኘት ነበርና አገኘው... ስለኤልሳ የነገረውን በማስታወስ ዶጮ ያኔ ስለኤልሳ የሰማኸው ልክ አልነበረም ማለትም ፊዚክስ ቲቸራቹ አጎቷ ነው አለ አይኖቹ እምባ አቀርዝዘው ዶጮም በምፀት ፈገግ ብሎ ጓደኛዬ እኔ ላንተ ያልተጣራ ወሬ አላቀርብልህም ኤልሳን ምን ያህል እንደምታፈቅራት አውቃለው ለዛም አንድ እንድቶኑ ብቻ ነበር የምፈልገው ለዚም ብዬ ብዙ ለማጣራት ጥረት አድርጌአለው ሄኖክ አንተ ማለት ወንድሜ ነህ ማንም ሰው ሲያስከፋህ ማየት አልፈልግም ከፈለክ በዚ አድራሻ ኤልሳ ቤት ሂድ ከዛም ሁሉንም ታያለህ... አለና በትንሽ ወረቀት አድራሻ ፅፎ ሰቶት ይልቅ ወንድሜ ፀሎትን በደምብ ያዛት ላንተ ህይወት መስመር የምቶንህ እሷ ብቻ ናት ብሎ ትቶት ሄደ... ሄኖክ እውነቱን ሳያውቅ ማደር አልፈለገም በቀጥታ ወደ ኤልሳ ሄደ እንደተባለውም የኤልሳ ግቢ ሲደርስ ማመን አቃተው ኤልሳን ሲያውቃት የድሃ ልጅ ነበረች ፓርቲ ለመሄድ እንኳን ቀሚስ የለኝም ትል የነበረች ልጅ ዛሬ መቼም ከሰማይ አይወርላልትም ይሄ ሁሉ ሀብት አለ በውስጡ የኤልሳ ቤት እጅግ ውብ የሚባል ነው... በመደመም ካየው ቡሃላ እውነቱን ለማረጋገጥ አንኳኳ አንድ ጎልማሳ የክፍለ ሀገር ሰው ከፈተለት ማንነቱን ለማወቅ ጥያቄ አያሻውም የግቢው ጥበቃ ነው... ሄኖክ በሩ ሲከፈት ደንግጦ ምን ለመጠየቅ እንደመጣ ጠፋበት ከዛም ሰውየው ምን ፈለክ ጎረምሳው አሉ እ...እ..እ እያለ ሲርበተበት ምናባቱ እ ይልብኛል ምን ፈለክ አሉ እ... ኤልሳን ነው ትኖራለች ሲል ጠየቀ ሰውየውም እትዬ የለችም ባልተቤቷ ግና አሉ አለ ባሏ አለና ቃሉን ደገመው አዎ ልጥራልህ አሉ አይ ተውት ግን የምር ኤልሲ አግብታ ነው? ሲል በድጋሚ ጠየቀ ምን ይላል ይሄ የስንት አመቱን ነው ሲል ድንገት አሸብር ማነው የመጣው አለ አንድ ጎርናና ድምፅ ከወደ ውስጥ ሄኖክም እንደ እብድ ብቻውን እያወራ በመጣበት መመለስ ጀመረ..... ............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━

❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ ሁለት 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ፀሎት ስትወድቅ ሁለቱም ተደናግጠው አነሷትና ምን ማድረግ እንዳለባቸው ግራ ተጋቡ ይሄኔ የኤልሳ ፀሃፊ ሲጯጯሁ ሰምታ ስለነበር በፍጥነት ወደ ውስጥ በመግባት ፀሎት ላይ ውሃ አፈሰሰችላት ፀሎት ግን አልነቃችም ይሄኔ አምቡላንስ ጠርተው ወደ ሆስፒታል ወሰዷት ዶክተሮቹም ኤልሳንና ሄኖክን ውጪ እንዲቆዩ ነግረዋቸው ስራቸውን ቀጠሉ... ይሄኔ ሄኖክ ወደ ኤልሳ ተጠግቶ... "ባንቺ ነበር ህይወቴ መስመር መሳት የጀመረችው ከዛም አንቺን አፍቅሬ ታወርኩና የሚወዱኝን ስገፋና ስበድል ኖርኩ ከዛ ፍቅርሽን አግኝቼ መኖር ጀመርኩ ስል ዳግም በራስሽ ላይ መጥፎ ውሳኔን ወስነሽ ልጃችንን አሶርዳለው ስትይ እንዳላጣሽ ፈርቼ ላወራሽ ብመጣ የደከምኩለት ትምህርቴን አጣሁት ለካ አንቺ ከሌላ ወንድ ጉዳይ ስለነበረሽ ነው ያን ያልሽው..." ሄኖክ ንግግሩን መቋጨት አቅቶት ወንበሩ ላይ አቀርቅሮ እያነባ ተቀመጠ ይሄኔ ኤልሳ በዛ ጣፋጭ አንደበትዋ እንባዋን እያዘነበች "አትሳሳት ካንተ ውጪ ማንንም ወንድ አፍቅሬም ሆነ ወደ ህይወቴ አስገብቼ አላውቅም! ሄኒ ያኔ በኔ ምክንያት ስትባረር እኔ ጋር የቀረው ልጃችን ብቻ ነበር እሱንም ልንመረቅ ጥቂት ወራት ቀርተውን ስለነበር ነው ላሶርደው ብዬክ የነበረው ግን አንተን ሳጣ ካንተ ያገኘሁትን አንድና አንድ ስጦታ ልጄን ማጣት አልቻልኩም በሱ ውስጥ አንተ አለህ ..." ይሄኔ ሄኖክ ማመን አቅቶት የሌላ ሰው ታሪክ ታወራ ይመስል አፉን ከፍቶ ያዳምጣታል አክላም "እድሜ ለአጎቴ እዚው ዩንቨርስቲ ፊዚክስ ያስተምር ስለነበር ብዙ ረድቶኝ ተመረኩ ልጄንም ትምህርቴንም ሳላጣ..." እያለች ንግግሯን በእንባዋ አጅባ ስትቀጥል ሄኖክ ዶጮ የነገረው ትዝ አለው "ከፊዚክስ አስተማሪ ጋር ፍቅር ጀምራለች" ብሎት ነበር ሄኖክ ማስተዋል ሲጀምር ምላሽ አገኘ ዶጮም ሆነ ሌሎቹ የኤልሳ አጎት ፍቅረኛዋ መስሏቸው ነበር ግን እውነቱ ያ አይደለም ጭንቅላቱን ይዞ "ማመን አልነበረብኝም አንቺን መጠበቅ ነበረብኝ ግን እረፍዷል ሂጂ ኤልሳ ላይሽ አልፈልግም ሂጂ" ብሎ ሲጮህ ኤልሳ ተስፋ በቆረጠ አስተያየት እንባ በሚያጎርፉት አይኖቿ እያየችው ከተቀመጠችበት ተነሳች ይሄኔ "...አዎ ዳግም ህይወቴ ውስጥ አትግቢ ምክንያቱም ያን ያህል ግዜ ስጠፋ አንዴም አልፈለግሽኝም ከሞት አፋፍ ላይ የመለሰችኝ ፀሎት ናት ያኔ ሜላትን ባንቺ ለውጬ እንደጎዳዋት ሁሉ ዳግም መሳሳትና ፀሎትን መጉዳት አልፈልግም!" አለ ኤልሳም ልትናገር "..እ ግን ለልጃችን የግድ ታስፈልገዋለክ..." ስትል ዶክተሮቹ ወተው የፀሎት ቤተሰብ አሉ ሄኖክም በፍጥነት ወደ ሀኪሙ ቀርቦ ደና ናት ሲል ጠየቀ ሀኪሙም ፈገግ ብሎ ቶሎ ደርሰንላታል ደና ናት ገብተህ ማየት ትችላለህ አለው... ፀሎት ተሽሏት ከሀኪም ቤት ወጣች እራሷን ስትስት ምን ተፈጥሮ እንደነበር ግን እረስታው ኖሮ ጭራሹን አላነሳችም እንደሁልግዜዋ ደስ የሚል ፍቅር መስጠቷን ቀጠለች ሄኖክ ግን ኤልሳን ካገኘና ልጅ እንዳለው ካወቀ ወዲ እንደ እብድ ያረገው ጀምሯል ባህሪው ቅይርይር ከማለትም ባለፈ አይጨበጥም... ይሄ ያስጨነቃት ፀሎት ታድያ አንድ ቀን ምሽት ራት ጋብዛው ሲገናኙ ከዛ በፊት "መች ነው የምታገቢኝ?" ያላትን አስታውሳ "...ፍቅሬ ጥያቄህ መልስ አግኝቷል አሁን ዝግጁ ነኝ ሽማግሌ ላክ" አለችው ፈገግ ብላ በዚ ግዜ ክው አለ የገዛ ምራቁ አነቀው... ማንን መምረጥና ማስቀደም አለበት??? እኔንጃ...... ............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━

❤️ተወዳጁ #ተከታታይ ልቦለድ #ክፍል አስራ አንድ 💢ልብ አንጠልጣይና አሳዛኝ ታሪክ ኤልሳ ትከዳኛለች ብሎ አስቦ የማያውቀው ሄኖክ በሰማው ነገር ቅስሙ ተሰበረ ህይወት አስጠላችው ይሄኔ ማጨስና መጠጥ መጠጣት ጀመረ ሄኖክ ሙሉ ለሙሉ ወደ ሱስ ሲገባ በቀን ከሚያገኘው ገቢ ግማሹ ለሱስ ሲሆን የተረፈው ለአጎቱ ሚስት ሀና የቤት ኪራይ ና ለሷ አንዳንድ ነገር መግዣ ይሰጣታል... በዛ መልኩ ግን ኑሮን መግፋት አልቻለም ሀናም በጣም ትታመም ጀመር ግን በቂ ገንዘብ ስለሌለው በወቅቱ ህክምና አታገኝም ልክ በ7ወሯ ለሊት ላይ ሀና በጣም ታመመች ይሄኔ ሲነጋ በጥዋት ነብስ አባቷን አስጠርታ ሄኖክ ከገባበት መጥፎ መስመር ወጥቶ እንዲማር 100,000ብር ባንክ ያስቀመጠችውን ተናዘዘችለት ... ሀና ገንዘቡን ያገኘችው መንግስት ወረሰን ላለችው ቤት ካሳ ተሰቷት ስለነበር ነው። ሄኖክ በግርምት እናቴ ይሄ ሁሉ ገንዘብ ካለሽ ታድያ ለምን አልታከምሽም ሲል ጠየቀ ይሄኔ ሀና እንባዋ በጆሮዋ በኩል እየተንቆረቆረ ልጄ አንደኛ ገንዘቡ እንዳለኝ ብነግርህ ለኔ አትልም ነበር ልክ አሁን እንዳልከው በሽታዬ ላይድን ነገር በህክምና እንጨርሰው ነበር ሁለተኛ ተቸግሬና ተጎሳቁዬ እንኳ ከልጅ በላይ እንደምትወደኝና ሳይኖርህ ስትንከባከበኝ ልጄ ደስታዬ ልክ አልነበረውም ለዛም ነው እስካሁን የኖርኩት አለች ሄኖክ ማመን አቃተው የተኛችበት አልጋ ጫፍ ላይ አቀርቅሮ አለቀሰ በቃ ህይወት እንዲ ነው አንዳንዱ እንጥፍጣፊ ፍቅር ሳያስቀር አውጥቶ ይሰጥሃል አንዳንዱ ደግሞ ስትሰጠው ብቻ ይሰጥሃል አንዳንዱ ብትሰጠውም ባትሰጠውም ይነፍግሃል ሀና በህይወት መቆየት አልቻለም አረፈች ሄኖክ በምድር ላይ ያሉትን የሚወዳቸውን ነገሮች ሁሉ አጥቷል የሚወደውን ለማግኘት ደግሞ የምትወደውን ሜላትን ልብ ሰብሯል ... ለዛም ሀና ባወረሰችው ገንዘብ ምንም ቁም ነገር ሳይሰራበት እዛው ተወውና ሱሱን ገፋበት በዚ ወቅት ሴት ልጅ ቀርባ ስታዋራው ሁሌም ኤልሳና ያ ውብ አስተያየቷ ትዝ ይለዋል ከዛ ወድያው የሌላ ሆና እነዛን ውብ ከንፈሮቿን በሌላ ወንድ ስትሳማቸው ያስበዋል ይሄኔ ሴት ልጅ ከሀዲ ናት አልቀርብም ይላል...በዚ አቋሙ ሲኖር አንድ ቀን ፊልም ሊከራይ ፊልም ቤት ይሄዳል ይሄኔ አንዲት እድሜዋ ከሱ አነስ የምትል የቀይ ዳማ ቆንጂዬ ፍልቅልቅ ሴት ገና ሲገባ ከመቀመጫዋ ተነስታ በራሷ ምርጫ ፊልም ትሰጠዋለች በጣም ተገርሞ እኔ መች ገና ጠየኩሽ ይላታል ልጅቷም ቅልጥፍጥፍ ባለ ማራኪ አንደበቷ እኔ መረጥኩልሃ ገና ሳትነግረኝ ምን እንደምትፈልግ አወኩ አለች ለረጅም ግዜ ሴት መቅረብ ፈርቶ የነበረው ሄኖክ ከቀን ወደ ቀን በልጅቷ መሳብ ጀመረ ልጅቷ ፀሎት ትባላለች እስከዛሬ ልብ ብሏት ባያውቅም አሁን ግን ልቡ ደንግጦላታል እሷም ሆን ብላ ይመስል እሱ የሚወደውን ቀድማ ታደርግለታለች መቀራረባቸው በጨመረ ቁጥር የተሰበረውን ልቡን ትጠግንለት ጀመር ከ1አመት ቡሃላ ሄኖክ ሱስ የሚባል ነገር እርግፍ አድርጎ ተወ ከዛም የቀን በዲግሪ ፕሮግራም ትምህርት ጀመረ እድሜ ለሀና ልክ መለወጡን ሲያረጋግጥ ገንዘቡን መጠቀም ጀመረ... አንድ ቀን ታድያ አፓረንት ወተው ወደ አንድ ድርጅት ተላኩ የመጀመርያው ቀን ፀሎት አብራው ሄደችና ወደ ዋናው ቢሮ አንኳኩተው ገቡ ይሄኔ ነበር ሄኖክ ተአምር ይመስል ባየው ነገር ደንግጦ የቀረው... የቢሮው ሃላፊ የመጀመርያ የልጅነት ፍቅሩ ኤልሳ ናት ያየው እውነት ባይሆን ብሎ ተመኝቶ አይኑን ጨፍኖ መልሶ ገለጠው ግን እውነት ኤልሳ ፊትለፊቱ ቆማ እንባዋ ይንቆረቆራል... ካንደበቱ ቃል ማውጣት ተስኖት ፈዞ ቀረ ፀሎትም ግራ ገብቷት አንዴ እሱን አንዴ እሷን ታያለች ይሄኔ ኤልሳ "እንዴት ግን አስቻለህ? እኔን ተወኝ በልጅህ እንዴት ጨከንክ?"... አለች ድምጿ እየተቆራረጠ ይሄኔ ሄኖክ ክው አለ ፀሎትም ልጅክ ብላ በድንጋጤ ወደቀች....... ............ይቀጥላል…..........✍ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━