Nathan casting agency
Open in Telegram
The best place to get the best casting jobs Our services -casting models - for music clips - movies - series dramas - fashion shows - television shows Contact: 0920358051
Show moreEthiopia16 170The category is not specified
408
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
═❖• •❖═══╗
የጠፋው ሬሳ
╚═══❖• •❖═══╝
ክፍል ሁለት
...ስልኬን አወጣሁና ጓደኛዬ ጋር ደወልኩ "ሄሎ ባርሰናይት እንዴት አደርሽልኝ" አልኳት "ሜርሲዬ ሰላም አድሬያለሁ ባባ እኮ መኪናውን ይዞ እየጠበቅንሽ ነው" አለችኝ "እሺ ባርሳዬ አሁን እደርሳለሁ ቻው" ብዬ ስልኩን ዘጋሁት...ባባ ማለት የባርሰናይት ፍቅረኛ ነው...እኔ ብቻ ነኝ እንጂ ሁለቱ ጓደኞቼ ጥንድ ናቸው...ወደ ጉዞው አምስት ሆነን ነው ምንሄደው ከደቂቃዎች ጉዞ በሗላ ጓደኞቼ ጋር ደረስኩ...ከመኪና ውስጥ ከሹፌሬ ጋር ዕቃዬን አወጣንና የባባ መኪና ላይ ጫንን..."ምንም አይነት ነገር ቢፈጠር ወይም የሚያጠራጥር ሁኔታ ውስጥ ከገባሽ ደውዪልኝ" አለኝ እጅግ የዋሁና የሚያሳዝነኝ ሹፌሬ "እሺ እደውላለሁ" አልኩና እቅፍ አርጌ ተሰናበትኩት ሹፌሬ እስኪሄድ ድረስ ጓደኞቼ ትንፍሽ አላሉም ነበር ልክ እሱ እንደሄደ..."ሜርሲ" ብላ ቅድስት ከመኪናው ዘላ ወረደች "ቅድስቴ" ብዬ እቅፍ አርጌ ሳምኳት ተራ በተራ ሁሉም ሰላም አለኝ "Rav 4" መኪና ውስጥ ገብተን ጉዞ ወደ ውቧ ከተማ አዳማ ናዝሬት ጀመርን...ጓደኞቼ ከሚያረጉት ነገር የማረገው ቢኖር መብላት ብቻ ነው ግን ምንም ቢያረጉ በጣም ነው ምወዳቸው እነሱም እደ ፍላጎታቸው ባልሆንም በጣም ይወዱኛል ባባ ለስለስ ያለ ዘፈን እኔ ግን ብዙም የዘፈን አድናቂ አልነበርኩምና ኤርፎኔን አውጥቼ መዝሙሬን ከፈትኩ...
፡
"እንደ ዋላ ውሃ እንዳማረው፣
በበረሃ ጥም እንደያዘው፣
ልቤ አንተን ይላል(2)...የሚለውን የሊሊን መዝሙር ከፈትኩኝ ብዙም ሳልቆይ ቅድስቴ ነካ ነካ አርጋ ጠራችኝ ኤርፎኔን አውልቄ "ወዬ" አልኳት "ልናጨስ ነበር አይደብርሽማ" አለችኝ "መኪናውን አቁሙና አጭሱ እኔም ራቅ ብዬ እቀመጣለሁ ከዛ እንሄዳለን" አልኳቸው በሀሳቤ ተስማምተው መኪናውን አቆሙ..."ሁለት ስቲክ ብቻ ነው ምንነፋው ይቅርታ እሺ ሜርሲ" አለኝ ባባ "አይ ችግር የለውም" አልኩት የቆምንበት ቦታ ከከተማ ወጣ ብለን ስለነበር በቅርብ የሚታየኝ በዛፍ የተከበበ ስፍራ ብቻ ነው ኤርፎኔን ሰክቼ ወደ ዛፉ ውስጥ ጉዞ ጀመርኩ ውሎዬን እንደ አዲስ የሚያስጀምር ደስ የሚል ቅዝቃዜ አለው ፀጥታው ሰው ከራስ ጋር እንኳን ቢነጋገር ያስተጋባል ብል ማጋነን አይሆንብኝም ከዛፎች ፍትጊያ እና ከሚረገፉት ቅጠሎች ውጪ ሌላ ምንም ድምፅ የለውም ፍፁም ሰላም የሞላበት ስፍራ...ሳላስበው ወደ ውስጥ ብዙ ተጓዝኩኝ ጫካው እንዳለቀ መሀል ላይ እጅግ ፅዱ ሰማያዊ የፏፏቴ ውሃ አለ ከላይ ተምዘግዝጎ መሬት ያለውን ድንጋይ ሲመታው የሚፈጠረው ድምፅና ፍንጥርጣሪ የተለየ ድባብ አለው እዚ ስፍራ ላይ ለአንድ ቀን ካምፕ አርገን ብናድር ብዬ ተመኘሁ ግን ቦታው በምሽት እንደሚያስፈራ ምንም ጥርጥር የለውም አንዳች ብርሃን የማይገፈው ድቅድቅ ጨለማ ነው...ፊቴን ለመታጠብ ወደ ውሃው ተጠጋሁ ልክ ስነካው ፍል ውሃ ነው ይሄ ቦታ የቱንም ያህል ቢያስፈራ ማደር አለብን አልኩኝ ወዲያውኑ ወደ ጫካው ሠውጫ አመራሁ...ምንጣፍ ከአንድ ዛፍ ጥላ ስር ዘርግተው አራቱም ተኝተዋል ይሄን ያህል መቆየቴን አላስተዋልኩትም ነበር...እንደውም በእንቅልፍ ለዛለ ሰውነታቸው ፍቱን መነቃቂያ..."ሄይ ጋይስ" ብዬ ጨውኩባቸው "ውይ ሜርሲ የት ጠፍተሽ ነው" አለችኝ ባርሰናይት "እኔ ያየሁትን ብታዩ እዚ መቼም አትተኙም" አልኳት "ምን አየሽ ሜርሲዬ አሳዪና" ብላ ሌሎቹንም ቀሰቀሰቻቸው ያወጡትን ዕቃ ሁሉ ወደ መኪናው መለሱና እኔን መከተል ጀመሩ...ከደቂቃዎች በሗላ ፍል ውሃው ጋር ደረስን "ወይኔ በፈጣሪ ሲያምር" አለች ቅድስቴ ዘላ ለመግባት ልብሷን እያወላለቀች ሙሉ ዕርቃኗን ቀረች ምንም ልብስ ገላዋ ላይ አልነበረም ወዲያውኑ ዘላ ገባች "እንዲ ፍል ውሃ" አለች እየተገረመች ባርሰናይትም ማውለቅ ጀመረች እነ ባባም እንደዛው እኔ ግን ዝም ብዬ እነሱን ማየት ጀመርኩ..."ተቀላቀዪን እንጂ" አለ የቅድስት ጓደኛ ብዙም ደስ ስለማይለኝ መልስ እንኳን አልሰጠሁትም ነበር "ሜርሲ" አለኝ ባባ እሺ ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ...ለራሴ እስኪገርመኝ ድረስ እጅግ ትልቅ ቅርፅ ነው ያለኝ አነስ አነስ ያሉ ጡቶች ነጥብ የሌለበት ጥርት ያለ ገላ ነው ያለኝ...ወንዶቹ እኔ ላይ ማፍጠጥ ጀመሩ "አረ ጡት ማስያዣውን አውልቂው አለች ቅድስት በሀሳቧ አለመስማማቴን በጭንቅላቴ ንቅናቄ አሳየሗትና ዘልዬ ገባሁ...እኔ ቅድስቴ እና ባርሰናይት እየተረጫጨን መጫወት ጀመርን ወንዶቹ ዳር ይዘው ይመለከቱናል...እስኪደክመን ተጫወትንና "ወጣን ለምን ዛሬ እዚ ካምፕ አርገን ለምን አናድርም" አልኳቸው "በቂ መጠጥ እና ምግብ አለን ለዛሬ ይበቃናል እንደር" አለ የቅድስት ጓደኛ ባርሳም ተስማማች እነ ቅድስቴም ሀሳቤን ተቀበሉ ሰውነታችን እስኪደርቅ አንሶላ ላይ ጋደም አልንና ትንሽ ቆየን ከዛም ልብሳችንን ለብሰን ከመኪና ውስጥ ዕቃ ለማምጣት ሄድን...የተለያዩ መጠጦች ሚለበሱ ልብሶች እና ምግቦችን አወጣን እኔ ከአገልግሌ ውጪ ሌላ ምንም አልነካም...የሚጠጣም ነገር ፈልቶ የቀዘቀዘ ውሃ አለኝ..."አንዴ ተመልሰን የቀረውን ዕቃ እናምጣ" አለ ባባ እሺ ብለን ሁላችንም ተመለስን መኪናችን ጋ እንደደረስን እጅግ በፍጥነት የሚመጣ የተጋጨ መኪና ማንሻነት የሚጠቅም መኪና ሲመጣ ተመለከትን እየቀረበን ሲመጣ መስታወቱ ላይ እና የፊት የመኪናው ክፍል በደም ተጨማልቋል በጣም በፍጥነት አለፈን ባባ ግን "አንተ ደደብ ቀስ አትልም" አለ መኪናው ወዲያውኑ ቀዘቀዘ እስከሆነ መንገድ ድረስ ወደ ሗላ ተመለሰ ስፖኪዮውን ወደ እኛ አቅጣጫ አስተካከለና ትንሽ ቆሞ መንገዱን ቀጠለ...ይሄ ነገር ምንም አላማረኝም ውስጤን ፍርሃት ፍርሃት አለኝ "ከዚ እንሂድ" አልኳቸው "አረ ሜርሲዬ አትፍሪ ሰው ገጭቶ እያመለጠ ይሆናል" አለች ቅድስቴ እኔን ለማረጋጋት "እሺ" አልኩና ወደ ውስጥ ጉዞ ጀመርን ውሃው ዳር እንደደረስን ሴቶቹ እንጨት ለቀማ ሄድን ወንዶቹ ደሞ ምንተኛበትን መስራት ጀመሩ በድንገት ከነ ባርሳ ተለይቼ ወደ ሌላ አቅጣጫ ሄድኩኝ ነይ እንጂ ስትለኝ ቅድስቴ ሽንቴን ልሸና ነው አልኳት ልክ ትተውኝ ሲሄዱ ወደ መኪናችን ሄድኩኝ ከመኪናችን በስተ ግራ በኩል በተቃራኒው አቅጣጫ የቅድሙ መኪና
እንዲቀጥል አብሮነታችሁ አይለየን ላይክ @fkrnahiwot
(እጅግ ልብ አንጠልጣይ ድረሰት)
ባልንው መሰረት ልብወለዱ ጀመርን አብራቹን ቆዩ
╔═══❖•💀💀•❖═══╗
የጠፋው ሬሳ
╚═══❖•💀💀•❖═══╝
(ምዕራፍ አንድ)
፡
ክፍል አንድ
፡
.....ሜርሲ እባላለሁ ቤተሰቦቼ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ናቸው የተወለድኩ ወድምም እህትም የሌለኝ የቤቱ ብቻ ልጅ ነኝ...ያልኩት ይደረግልኛል አንዲትም ሳትቀር በጣም ይሽቆጠቆጡልኛል ዛሬም ዕለቱ የትምህርት ማቆሚያ የክረምቱ ደግሞ መጀመሪያ ስለሆነ ከጓደኞቻችን ጋር ወጣ ብለን የመለያያ ፕሮግራም ለማድረግ እየተዘገጃጀሁ ነው ለሳምት እንቆያለን ስለተባለ ልብሶቼን በሻንጣ በውል አዘጋጀሁ..."ሜርሲ ሜርሲ" አለች የቤት ምግብ አብሳያችን አቤት ስንዱ አልኳት የመኝታ ክፍሌን መዝጊያ እየከፈትኩ "አቶ አላዛር ሊያናግሩሽ ይፈልጋሉ" አለችኝ "እሺ መጣሁ" አልኳት አቶ አላዛር ማለት ውዱ አባቴ ነው...የመኝታ ቤቱን እያንኳኳሁ "ልግባ አባቢ" አልኩት "ግቢ የኔ ልጅ" አለኝ በምላሹ እኔም ወደ ውስጥ ገባሁ "እንዴት አደርሽልኝ የኔ ልዕልት ነይ እስቲ" ብሎ ግንባሬን ሳመኝ "የቀኖቹ ባለቤት እሱ ይመስገን ዛሬም አዲስ ቀን አየሁ" አልኩት "የኔ አንደበተ ማር ቃሎችሽ እኮ እንደ ከርቤ ዕጣን ያውዳሉ"አለኝ አልጋው ጎን ተቀምጬ ፀጉሬን እየነካካ "አባቢ ደሞ ምን የተለየ ነገር ተናግሬ ነው" አልኩት "እኔ ያልኩትን ራሱ ብትደግሚልኝ እንደ አዲስ ብርቅ ሆኖብኝ ነው ምሰማው" ብሎ ፈገግ አለ "ማሚስ የት ሄዳ ነው በጠዋት" ብዬ ጠየኩት "ጉዞ ሄዳለሁ ብለሽ የለ ከስንዱ ጋር ለጉዞሽ የሚሆን ስንቅ እየሰሩልሽ ነው የሆቴል ምግብ እንደማትጠቀሚ እያወቀች ዝም ብላ አትለቅሽ" አለኝ "እውይ የኔ እናት ሄጄ ልጠምጠምባታ" ብዬ ከአልጋው ስነሳ "የተጠራሽበትን ዋና ጉዳይ ሳልነግርሽ ወዴት ልትሄጂ ነው" አለኝ "እሺ ንገረኝ" አልኩት ወድያውኑ "ት/ት ቤት የሚያመላልስሽ ሹፌር አብሮሽ እንዲሆን ነግሬዋለሁ ከከተማ ውጪ ማንም አጠገብሽ ሳይኖር ብቻሽን ልተውሽ አልፈልግም አሁን ይመጣል"አለ "አረ አባቢ ችግር የለውም ጓደኞቼ እኮ አሉ ብዙ ነን የኔ አሳቢ አባቴ አመሠግናለሁ በነፃነት እንድዝነናና ፍቀድልኝ አባቢ ይሄን ብቻ ተቸገርልኝ ደሞኮ አድጌያለሁ"አልኩት "እሺ እንዳልሽ ስልክሽ ግን ሁሌም ክፍት አርጊው በምንም አይነት ሁኔታ ዝግ እንዳይሆን እንደውላለን አንቺም ደውዪ" አለኝ ማስጠንቀቂያ በሚመስል ትዕዛዝ "እሺ የኔ አባት አታስብ" ብዬ ግንባሩን ስሚው ከክፍሉ ወጣሁ ከዛ ማሚ ከኔ ክላስ ስትወጣ አየሗት የኔ እናት ብዬ ጥምጥም አልኩባትና ጉንጯን ሳምኳት "አረ ቀስ ወዜን እንዳትመጪው" አለችኝ እቅፍ አርጋ እየሳመችኝ..."የኔ ልጅ በጣም ተጠንቀቂ እሺ ነገሮችን በማስተዋል አድርጊ" አለችኝ ለኔ እጅግ እንደምትሳሳ አይኗ ላይ ይነበባል "እሺ የኔ እናት አታስቢ እኔ ያንቺ ልጅ አድጌልሻለሁ እኮ" አልኳት "ፈጣሪ ይመስገን ጎርምሰሽልኛል መልካም መንገድ የኔ ልጅ ታዲያ ቶሎ ቶሎ ደውዪ እሺ እድንጨነቅ አታርጊን" አለችኝ "እሺ እናቴ" ብዬ ወደ መኝታ ክፍሌ ገባሁ ተለቅ ያለ አገልግል ጠረጴዛዬ ላይ ተቀምጧል አይ የኔ እናት ...ለጉዞዬ የመረጥኩትን ልብስ ለበስኩኝ እጅግ አማረብኝ ስለ ራስሽ አወራሽ አትበሉኝና...እጅግ በጣም ቆንጅዬ ሴት ነኝ የናቴ ልጅ ራሴን በጣም ነው ማቆለጳጵሰው ሌላ ማን ያቆለጳጵሰኛል "ስንዱ ዕቃዬን ታግዢኛለሽ" አልኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ በሩን ከፍቼ አንገቴን አስግጌ ጠራሗት "እሺ ሜርሲዬ" ብላ መጣች እሷ ሻንጣውን እኔ ደግሞ አገልግሉን ይዤ ወደ መውጫው ጉዞ ጀመርን "የኔ አባት እና የኔ እናት ትናፍቁኛላችሁ እስክንገናኝ ምወደው ፈጣሪዬ ምወዳቹን ይጠብቅልኝ"አልኳቸው ድምፄን ከፍ አድርጌ "እሺ ሰላም ግቢልን የኛ ልጅ" አለ አባቢ ማሚ መዳፏን እያወዛወዘች በፈገግታ ሸኘችኝ...የሳሎኑን በር ዘግቼ ወጣሁ የግቢ ጠባቂያችን "አምጪው ሜርሲዬ" ብሎ አገልግሉን ተቀበለኝ "አመሠግናለሁ አስራት አምላክ ይባርክህ" አልኩት "አሜን አለኝ በምላሹ "እና ምን አዲስ ነገር አለ" አልኩት "ምንም ሜርሲዬ ይነጋል ይመሻል ድጋሜ ይነጋል ድጋሜ ይመሻል" አለኝ በውስጤ "አይ የሰው ልጅ ምን አዲስ ነገር አለ ሲባል ምንም ይላል የዛሬውን ቀን ከዛሬ በፊት ያየውና ውሎ ያደረበት ይመስል"እላለሁኝ ግን ለአስራት መልስ አልሰጠሁትም ነበር...ጓደኞቼ ድረስ የሚያደርሰኝ ሹፌሬ ደጅ ላይ ቆሞ እየጠበቀኝ ነው "ሰላም አደርክ" አልኩትኝ ኮፈኑን እንዲከፍትልኝ በእጄ እየጠቆምኩት ወዲያው ከፈተው "አስራት አገልግሉን ከውስጥ አርገው ስንድዬ ሻንጣውን እዚ አስገቢው"አልኳቸው ሁለቱም "እሺ አሉኝ...እቅፍ አርጌ ሳምኳቸውና ሰላም ያገናኘን ብዬ ወደ መኪናው ገባሁ
እንዲቀጥል አብሮነታችሁ አይለየን የሼር ላይክ እና ኮመንት ቁጥር አይተን ምንቀጥል ይሆናል
ይቀጥላል ...............
@fkrnahiwot
Tariku k temechachu endiket👍ychanu Lela endijmr mifelg kale 🤚
(እጅግ ልብ አንጠልጣይ ድረሰት)
ባልንው መሰረት ልብወለዱ ጀመርን አብራቹን ቆዩ
╔═══❖•💀💀•❖═══╗
የጠፋው ሬሳ
╚═══❖•💀💀•❖═══╝
(ምዕራፍ አንድ)
፡
ክፍል አንድ
፡
.....ሜርሲ እባላለሁ ቤተሰቦቼ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ናቸው የተወለድኩ ወድምም እህትም የሌለኝ የቤቱ ብቻ ልጅ ነኝ...ያልኩት ይደረግልኛል አንዲትም ሳትቀር በጣም ይሽቆጠቆጡልኛል ዛሬም ዕለቱ የትምህርት ማቆሚያ የክረምቱ ደግሞ መጀመሪያ ስለሆነ ከጓደኞቻችን ጋር ወጣ ብለን የመለያያ ፕሮግራም ለማድረግ እየተዘገጃጀሁ ነው ለሳምት እንቆያለን ስለተባለ ልብሶቼን በሻንጣ በውል አዘጋጀሁ..."ሜርሲ ሜርሲ" አለች የቤት ምግብ አብሳያችን አቤት ስንዱ አልኳት የመኝታ ክፍሌን መዝጊያ እየከፈትኩ "አቶ አላዛር ሊያናግሩሽ ይፈልጋሉ" አለችኝ "እሺ መጣሁ" አልኳት አቶ አላዛር ማለት ውዱ አባቴ ነው...የመኝታ ቤቱን እያንኳኳሁ "ልግባ አባቢ" አልኩት "ግቢ የኔ ልጅ" አለኝ በምላሹ እኔም ወደ ውስጥ ገባሁ "እንዴት አደርሽልኝ የኔ ልዕልት ነይ እስቲ" ብሎ ግንባሬን ሳመኝ "የቀኖቹ ባለቤት እሱ ይመስገን ዛሬም አዲስ ቀን አየሁ" አልኩት "የኔ አንደበተ ማር ቃሎችሽ እኮ እንደ ከርቤ ዕጣን ያውዳሉ"አለኝ አልጋው ጎን ተቀምጬ ፀጉሬን እየነካካ "አባቢ ደሞ ምን የተለየ ነገር ተናግሬ ነው" አልኩት "እኔ ያልኩትን ራሱ ብትደግሚልኝ እንደ አዲስ ብርቅ ሆኖብኝ ነው ምሰማው" ብሎ ፈገግ አለ "ማሚስ የት ሄዳ ነው በጠዋት" ብዬ ጠየኩት "ጉዞ ሄዳለሁ ብለሽ የለ ከስንዱ ጋር ለጉዞሽ የሚሆን ስንቅ እየሰሩልሽ ነው የሆቴል ምግብ እንደማትጠቀሚ እያወቀች ዝም ብላ አትለቅሽ" አለኝ "እውይ የኔ እናት ሄጄ ልጠምጠምባታ" ብዬ ከአልጋው ስነሳ "የተጠራሽበትን ዋና ጉዳይ ሳልነግርሽ ወዴት ልትሄጂ ነው" አለኝ "እሺ ንገረኝ" አልኩት ወድያውኑ "ት/ት ቤት የሚያመላልስሽ ሹፌር አብሮሽ እንዲሆን ነግሬዋለሁ ከከተማ ውጪ ማንም አጠገብሽ ሳይኖር ብቻሽን ልተውሽ አልፈልግም አሁን ይመጣል"አለ "አረ አባቢ ችግር የለውም ጓደኞቼ እኮ አሉ ብዙ ነን የኔ አሳቢ አባቴ አመሠግናለሁ በነፃነት እንድዝነናና ፍቀድልኝ አባቢ ይሄን ብቻ ተቸገርልኝ ደሞኮ አድጌያለሁ"አልኩት "እሺ እንዳልሽ ስልክሽ ግን ሁሌም ክፍት አርጊው በምንም አይነት ሁኔታ ዝግ እንዳይሆን እንደውላለን አንቺም ደውዪ" አለኝ ማስጠንቀቂያ በሚመስል ትዕዛዝ "እሺ የኔ አባት አታስብ" ብዬ ግንባሩን ስሚው ከክፍሉ ወጣሁ ከዛ ማሚ ከኔ ክላስ ስትወጣ አየሗት የኔ እናት ብዬ ጥምጥም አልኩባትና ጉንጯን ሳምኳት "አረ ቀስ ወዜን እንዳትመጪው" አለችኝ እቅፍ አርጋ እየሳመችኝ..."የኔ ልጅ በጣም ተጠንቀቂ እሺ ነገሮችን በማስተዋል አድርጊ" አለችኝ ለኔ እጅግ እንደምትሳሳ አይኗ ላይ ይነበባል "እሺ የኔ እናት አታስቢ እኔ ያንቺ ልጅ አድጌልሻለሁ እኮ" አልኳት "ፈጣሪ ይመስገን ጎርምሰሽልኛል መልካም መንገድ የኔ ልጅ ታዲያ ቶሎ ቶሎ ደውዪ እሺ እድንጨነቅ አታርጊን" አለችኝ "እሺ እናቴ" ብዬ ወደ መኝታ ክፍሌ ገባሁ ተለቅ ያለ አገልግል ጠረጴዛዬ ላይ ተቀምጧል አይ የኔ እናት ...ለጉዞዬ የመረጥኩትን ልብስ ለበስኩኝ እጅግ አማረብኝ ስለ ራስሽ አወራሽ አትበሉኝና...እጅግ በጣም ቆንጅዬ ሴት ነኝ የናቴ ልጅ ራሴን በጣም ነው ማቆለጳጵሰው ሌላ ማን ያቆለጳጵሰኛል "ስንዱ ዕቃዬን ታግዢኛለሽ" አልኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ በሩን ከፍቼ አንገቴን አስግጌ ጠራሗት "እሺ ሜርሲዬ" ብላ መጣች እሷ ሻንጣውን እኔ ደግሞ አገልግሉን ይዤ ወደ መውጫው ጉዞ ጀመርን "የኔ አባት እና የኔ እናት ትናፍቁኛላችሁ እስክንገናኝ ምወደው ፈጣሪዬ ምወዳቹን ይጠብቅልኝ"አልኳቸው ድምፄን ከፍ አድርጌ "እሺ ሰላም ግቢልን የኛ ልጅ" አለ አባቢ ማሚ መዳፏን እያወዛወዘች በፈገግታ ሸኘችኝ...የሳሎኑን በር ዘግቼ ወጣሁ የግቢ ጠባቂያችን "አምጪው ሜርሲዬ" ብሎ አገልግሉን ተቀበለኝ "አመሠግናለሁ አስራት አምላክ ይባርክህ" አልኩት "አሜን አለኝ በምላሹ "እና ምን አዲስ ነገር አለ" አልኩት "ምንም ሜርሲዬ ይነጋል ይመሻል ድጋሜ ይነጋል ድጋሜ ይመሻል" አለኝ በውስጤ "አይ የሰው ልጅ ምን አዲስ ነገር አለ ሲባል ምንም ይላል የዛሬውን ቀን ከዛሬ በፊት ያየውና ውሎ ያደረበት ይመስል"እላለሁኝ ግን ለአስራት መልስ አልሰጠሁትም ነበር...ጓደኞቼ ድረስ የሚያደርሰኝ ሹፌሬ ደጅ ላይ ቆሞ እየጠበቀኝ ነው "ሰላም አደርክ" አልኩትኝ ኮፈኑን እንዲከፍትልኝ በእጄ እየጠቆምኩት ወዲያው ከፈተው "አስራት አገልግሉን ከውስጥ አርገው ስንድዬ ሻንጣውን እዚ አስገቢው"አልኳቸው ሁለቱም "እሺ አሉኝ...እቅፍ አርጌ ሳምኳቸውና ሰላም ያገናኘን ብዬ ወደ መኪናው ገባሁ
እንዲቀጥል አብሮነታችሁ አይለየን የሼር ላይክ እና ኮመንት ቁጥር አይተን ምንቀጥል ይሆናል
ይቀጥላል ...............
@fkrnahiwot
Tariku k temechachu endiket👍ychanu Lela endijmr mifelg kale 🤚
🙏 ሰላም ለእናንተ ይሁን ቤተሰቦቻችን ካነበብኩት ይችን ቆንጅዬ ታሪክ ተጋበዙልኝ !!🙏
✍️ወጣቷ ከምታፈቅረው ሰው ጋር በትዳር ተጣምራ ከባሏ እናት ጋር በአንድ ቤት መኖር ጀመረች፡፡ ከቀናቶች በኀላ ግን ከአማቷ ጋር ተግባብተው መኖር እንደማይችሉ ተረዳች፡፡ አማቷ ወግ አጥባቂ የሚባሉ አይነት ሰው ሲሆኑ በአንፃሩ ወጣቷ ደሞ ነፃ አስተሳሰብን የምታራምድ ናት፡፡ በዚህም የተነሳ በየጊዜው በአስተሳሰባቸውና በህይወት መርሀቸው መለያየት ምክንያት በየቀኑ መጣላት ጀመሩ፡፡ ቀናቶች ፣ ወራቶች አለፉ፤ አንዳቸውም ግን ባህሪያቸውን መቀየር አልቻሉም፡፡
ወጣቷ በጊዜ ሂደት እጅግ ተናዳጅ እየሆነች መጣች፤ አማቷንም መጥላት ጀመረች፡፡ አንድ ወቅት እንደተለመደው ከአማቷ ጋር ስትጣላ ባለቤቷ ከእናቱ ጎን ሲቆም እጅግ በመናደድ ትዳሯን ትታ ወደ አባቷ ቤት ተመለሰች፡፡ አባቷ ኬሚስት (ቀማሚ) ነው፡፡ እናም የተፈጠረውን በሙሉ ነገረችው፡፡ እናም መርዝ እንዲሰጣትና አማቷን እንድታስወግዳት እንዲረዳት ለመነችው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ወደ ትዳሯ እንደማትመለሰ ነገረችው፡፡
አባቷ ልጁ ባለችበት ሁኔታ በጣም አዘነ፤ "ለአማትሽ መርዝ ሰጥተሽ የምትገድያቸው ከሆነ እኔም አንቺም መጨረሻችን የሚሆነው እስር ቤት ነው" አላት፡፡ ወጣቷ ግን ይሄን የምታዳምጥበትም የምትረዳበትም ስሜት አልነበራትም፡፡ በስተመጨረሻ አባቷ ተስማማ፡፡ " እሺ እንዳልሽ ግን አንቺን ታስረሽ ማየት አልፈልግም፤ እና እንደምልሽ አድርጊ" አሏት፡፡ እሷም ተስማማች፡፡ "በየቀኑ ምሳ ወይም እራት ስትሰሪ የአማትሽ ምግብ ላይ ከዚህ ዱቄት ትንሽ ቆንጠር እያደረግሽ ነስንሽበት፤ መጠኑ ትንሽ በመሆኑ ቶሎ አትሞትም፤ ነገር ግን ቀስ በቀስ ከወራቶች በኀላ ትሞታለች፤ ሰዎችም ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ እንደሞተች ያስባሉ፡፡" አላት፡፡
በተጨማሪም "ማንም በአንቺ ላይ ጥርጣሬ ሊኖረው ስለማይገባ ከዛሬ ጀምሮ ከአማትሽ ጋር በፍፁም በምንም ጉዳይ መጣላት የለብሽም፤ በተገላቢጦሽ በደንብ ትንከባከቢያታለሽ ፣ ፍቅር ትሰጫታለሽ ፣ ረባሽ አትሆኝም ፣ ትሁት ትሆኛለሽ፡፡" አላት፡፡
ወጣቷ በአባቷ ሀሳብ ተስማምታ ከወራቶች በኀላ ከአማቷ ጭቅጭቅና ጥል ነፃ እንደምትሆን እያሰበች ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ በዛም እንደደረሰች አባቷ እንዳሏት የአማቷ ምግብ ላይ ትነሽ ዱቄት እየነሰነሰች ትሰጣቸው ጀመር፡፡ አማቷን መንከባከብና በምትናገረው ነገር ከመበሳጨት በዘለለ በትህትና መግባባት ጀመረች፡፡
ጊዚያቶች በሄዱ ቁጥር አማቷ እራሱ ፀባያቸው መቀየር ጀመረ፡፡ ምራቷ ስትንከባከባትና ፍቅር ስትሰጣትጊዜ እሷም የልጇን ሚስት እየወደዷት መጡ፡፡ እንደወትሮው መጣላት ቀረ፤ ለጎረቤታቸው ሲያወሩ አንዳቸው ሌላቸውን ማወደስ ጀመሩ፡፡ እንደ አማትና ምራት ሳይሆን እንደ እናትና ልጅ ፍቅራቸው ደመቀ፡፡
በዚህ ወቅት ወጣቷ በየቀኑ ምግቧ ላይ እየጨመረች የመትሰጣት መርዝ አማቷን ይገላቸዋል በማለት መጨነቅ ጀመረች፡፡ እየበረረች ወደ አባቷ ቤት አመራች፡፡ "አባዬ እባክህ ባለፈው ለሰጠከኝ መርዝ የሚሆነውን ማርከሻ ስጠኝ፤ አማቴ እንድትሞት አልፈልግም፤ ልክ እንደ እናቴ ናት፤ በጣም ነው የምወዳት፤ እባክህ አድናት" በማለት ለመነችው፡፡ አባቷ ፈገግ እያሉ " የምን መርዝ? የሰጠውሽ እኮ ጣፋጭ ዱቄትን ነበር" አሏት፡፡😍
#ጭብጥ
ሁሉም ሰው በዙሪያው ባለው ነገር የተነሳ የተለያየ ነው፡፡ ይሄ ልዩነት ደሞ ወደ አለመግባባት ሊወስድ ይችላል፡፡ ነገር ግን ለመግባባት መሞከርና ጤናማ ቅርርብን ለመፍጠር በባህሪያችን ላይ ማሻሻያዎችን ማድረግ አለብን፡፡ በሰዎች መካከል እንደዚህ አይነት አለመግባባቶች ሲፈጠር እንዲረጋጉና ወደ ትክክለኛው መንገድ እንዲጓዙ ማድረግ የሚወዷቸው ሰዎች ሀላፊነት ነው፡፡
🙌
ሼር🙏ሼር🙏ሼር🙏
🗣ለሀሳብ እና አስተያየት
📩 @fkrnahiwot
ሰላም ብዙ ሰው ለምንድን ነው መposet ያቆምከው እያለኘ ነው በጣም ይቅርታ ነገሮች ስላልተመቻቹልኘ ነው ካሁን ቡሀላ በደንብ እለቃለው ልቦለዶች ግጥሞች ከቨሮችን እለቃለው!። 👍እንዲጀምር ምትፈልጉ አመሰግናለው።
Repost from Nathan casting agency
ሰላም ብዙ ሰው ለምንድን ነው መposet ያቆምከው እያለኘ ነው በጣም ይቅርታ ነገሮች ስላልተመቻቹልኘ ነው ካሁን ቡሀላ በደንብ እለቃለው ልቦለዶች ግጥሞች ከቨሮችን እለቃለው!። 👍እንዲጀምር ምትፈልጉ አመሰግናለው።
ሰላም ብዙ ሰው ለምንድን ነው መposet ያቆምከው እያለኘ ነው በጣም ይቅርታ ነገሮች ስላልተመቻቹልኘ ነው ካሁን ቡሀላ በደንብ እለቃለው ልቦለዶች ግጥሞች ከቨሮችን እለቃለው!። 👍እንዲጀምር ምትፈልጉ አመሰግናለው።
😘የቆንጆዋ ጦስ😘
8
✍ሼn
.
.
.
ከሀሳቤ ወጥቼ ቀና ስል ነየሀኒ ቀሚስ ታች ድረስ ወርዶ ቀይ ሰውነቷ በጡት ማስያዣ ብቻ ተሸፍኖ ቁማለች ውስጤን አንዳች ነገር ተሰማኝ እንደመደንገጥም አልኩ ነገር ግን አይኔን ከሰውነቷ ላይ ማንሳት አልቻልኩም ነበር የሰውነቷ ጥራት የተለየ ነው ወደኔ ፊቷን እየዞረች አንተ አልሞቀህም እንዴ አለችኝ ተመስጨ እያየሁዋት እንደነበር ሳታቅ አትቀርም መሰል ፈገግ እንደማለት አለች ብዙም አልሞቀኝም አልኳት አይኔን በግድ ገተገለጠው ሰውነቷ ላይ እያነሳሁ የፈራህ ትመስላለህ በቃ ትንሽ ነፈስ ይበልብኝ እና እመጣለሁ ፈታ እያልክ ጠብቀኝ በቃ አለችኝ መፍራቴን ከድንጋጤየ እንዳወቀችው ገብቶኛል ግን እሷ ምንም ሳይመስላት የኔ እንደዛ መሆን ምን ይባላል? ራሴን ጠየኩ ግን መልስ አልነበረኝም ትዛዟን ተቀብየ የመኝታ ቤቱን በር ወጥቸ ወደ ሳሎን የሚያስወርደውን ደረጃ ጀመርኩ ሳሎን ላይ አሁንም ሙዚቃውና ጭፈራው እንደቀጠለ ነው ሁሉም ሞቅ ብሏቸዋል መመለሴንም ቁብ ያለው አልነበረም ሀኒ እስክትመጣ የቀድሞ መቀመጫየ ላይ ሁኛ አንዴ የቤቱን እቃወች አንዴ ደሞ ወደ ሚጨፍሩት የሀኒ ጓደኞች ላይ እያመላለስኩ መታዘቤን ቀጥያለሁ በዚህ መሀል ቀደም ብሎ ለዳንስ አስነስታኝ የነበረችው ልጅ በእጇ የወይን ብርጭቆ እንደያዘች ወደኔ መጣችና ከጎኔ ተቀመጠች ካለባበሷ ውጭ ሁሉም ነገርዋ ደስ ይላል እንደዚህ አይናፍር አትመሰልኝም ነበርኮ አለችኝ እጇ ላይ ያለውን መጠጥ ወዳፏ እያደረገች ኧረ አይናፍር እንኳ አይደለሁም ግን አባባልሽ ከዚህ በፊት የምታቂኝ አስመሰለብሽ ስል መለስኩላት በአካል እንደዚህ ቀርቤ ያየሁህ ዛሬ ቢሆንም በማወቅ ደረጃ ግን ከዚህ በፊት አውቅሀለሁ ማለቴ በፌስቡክ አለችኝና አስከትላ የምፅፋቸውን ነገሮች በጣም ነው የምወድልህ እንደውም አጋጣሚውን እንዳገኛሁ ብትፈርምልኝ ደስ ይለኛል ብላ እንደመሳቅ አለች አመሰግናለሁ ግን እኔ አላወኩሽም የፌስቡክ ስምሽ ማነው ስል ጠየኳት ስሟን ሳትነግረኝ ሀኒ ከደረጃው ብቅ አለች በቃ መልክት አስቀምጥልሀለሁ ሜሴጅ ላይ ያኔ ታውቀኛለህ ብላ በፈገግታ የታጀበ መልስ ሰታኝ ከጎኔ ተነሳች ሀኒ ደረጃውን እየወረደች አይኗ እኛ ላይ ነበር ደስ ያላት አትመስልም ልጅቱም ያን የምታቅ ይመስል ሀኒ ስትመጣ ስታይ ከጎኔ መነሳቷ ይበልጥ ሌላ ነገር ይመስላል ስል አሰብኩ ጓደኞቿ በጭፈራ ተቀበሏት እና ወደመሀል አስገቧት ሀኒም እጇ ላይ ያለውን ባለትልቅ እስክሪን ስልክ የሰልፊ ፎቶ ማንሻ ዘንጉ ላይ እያስተካከለች ለፎቶ እንዲዘጋጁ ነገረቻቸው የሀኒ እህት ደሞ ባራቱም የቤቱ ማእዘን ያሉትን የጌጥ መብራቶች አንድ በአንድ አበራቻቸው እና እሷም ራሷን ለፎቶ አዘጋጀች የቀረሁት እኔ ነበርኩ ሀኒ በአይኗ ስጠቅሰኝ ስለገባኝ ተቀላቀልኳቸውና ማስታወሻነታቸው ለሀኒ ልደት የሆኑ የተለያዩ ፎቶወች ቦታ እየቀያየርን ተነሳን ። ብዙ ሳይቆይ ለዳንስ ያስነሳችኝ ልጅ ብቻ ስትቀር ቀሪወቹ እየተሰናበቱን ወጡ ሰአቴን አየሁ 12።:30 ይላል የሰአቱ መሮጥ ይገርማል ይህን እያሰብኩ መጣን ተጫወት ብለው ሦስቱም ተያይዘው ወደ ፎቅ ወጡ ወዲያው እነሱ እንደወጡ ገና ስንመጣ የግቢውን በር ከፋታልን የነበረችው ሴት ወደ ሳሎን ገብታ እቃወቹን መነሳሳት እና ማዘጋጀት ጀመረች እነሀኒም ብዙ ሳይቆዩ እንዳወጣጣቸው ተከታትለው ወደ ሳሎን ገቡ የሶስቱም ልብስ ተቀይሯል እንዳዲስ ውብ ሁነው ነው የተመለሱት የሆነ እቅድ ሳይኖር እንዳልቀረ ገመትኩ ሌላ ልደት አለባችሁ እንዴ ስል እየቀለድኩ ጠየኳቸው ባንድ ሳቁና ሀኒ ወደኔ መጥታ ፊትለፊቴ ተቀመጠችና አንድ ነገር ልጠይቅህ ነው እምቢ ብለህ እንደማታስከፋኝ ቃል ግባልኝ አለችኝ አይን አይኔን እያየች ምንድነው ጠይቂኝ የምችለው ከሆነ መቸም እምቢ ልልሽ አልችልም የኔ ምላሽ ነበር ትንሽ ውጭ ማምሸት ፈልገን ነበር እና አብረህ እኛጋ እንድትሆን ፈልጌ ነበር አለችኝ እየተቅለሰለሰች ማምሸት የሚለው እስኪ ይብራራልኝ ስል መለስኩላት እራት ልጋብዛችሁ ፈልጋለሁ በዛውም የምንሄድበት አለን እዛ ፈታ ብለን እንመለሳለን ፕሊስ በቃ እሽ በለኝ ስትል እነሱም ተከትለው ልደትዋ ስለሆነ ደስ ይበላት በቃ እሺ በላት ሲሉ የሷን ጥያቄ በነሱ ሽንገላ ደረቡት ቤት እህቴ እንደምጠብቀኝ እና ማምሸት እንደማልችል ነገርኳቸው ሀኒ ካፌ ቀበል አድርጋ እሽ ቤት አብረን እንሂድና እኔ ላስፈቅዳት አለችኝ ሀኒን እንዲከፋት ስለማልፈልግ ብቻ በሀሳቧ ተስማማሁ ቤት ድረስ ባንሄድም ችግር የለውም ደውየ እነግራታለሁ ስል ሀኒ በደስታ ጥምጥም አለችብኝ እኔም ለህቴ ለመደወል ስልኬን አወጣሁና ወደ ውጭ ወጣሁ ሁለት ግዜ እንደጠራ ስልኩ ተነሳ ሰላምታ ካቀረብኩ ቡሀላ ላመሽ እንደምችልና ከዘገየሁ እንዳትጨነቅ ነገርኳት እንደዛ ዘንጠህ ስትወጣ እንደማትመለስ እኮ አውቄ ነበር ለማንኛውም ራስህን ጠብቅ ብላኝ ተሰነባብተን ስልኩን ዘግቼ ወደ ውስጥ ተመለስኩ በመቀጠልም የተከፈተውን ሙዚቃ ዘግቼ ላፕቶፔን አጠፋፍቸ ከጨረስኩ ቡሀላ ተያይዘን ግቢውን ለቀን ወጣን ምሽቱ በጣም ደስ የሚል እና ቀለል ያለ ንፋስ ያዘለ ነበር በሶስት ቆንጆዎች ታጅቤ ቀጥታ ያመራነው ከተማው ውስጥ ወዳለ ስመ ጥር ሆቴል ነበር እዛ እንደገባን ሁላችን እንደየምርጫችን ምግብ አዘዝን ሀኒ ከምግቡ ጋር አብሮ ዋይን እንዲመጣ አዘዘች ካፍታ ቆይታ በዃላ ምግቡና መጠጡ እኩል መጡና በሳቅ እና በጨዋታ የታጀበ ሀሪፍ ግዜ ማሰለፍ ጀመርን እኔም ከነሱ ጋር ተመሳሰልኩ ሌላ ወይን ተጨመረና ጨዋታው ደራ አሁን ሁላችንም ሀሪፍ ሙድ ውስጥ ገብተናል በተለይ እነሱ ቤትም እየጠጡ ስለነበር ያሁኑ ሲጨመር የለለ ድምቅ እንደማለት ብለዋል የተለያየ የወሬ ርእስ እየተነሳ ሳቅ እና ጨዋታው የተለየ መልክ ይዟል በዙሪያችን ለራት የተቀመጡ ሰወች ሳይቀሩ ትኩረታቸው እኛ ላይ ነበር በዚ መሀል ሀኒ ፊቴን ልታጠብ ብላ ወደ እጅ መታጠቢያው አመራች ታጥባ መጥታ ቁጭ እንዳለች ስልኬ ላይ ሜሴጅ እንደገባ ኪሴ ውስጥ ሲነዝረኝ ተሰማኝ አወጣሁና አየሁት የሀኒ ቴክስት ነበር " እንጥፋቸው " የሚል ነበር መልክቱ ቀና ብየ አየሁዋት እሷም አየችኝ እና ሳቀች ከዛም ለመልክቷ ምላሽ ወዴት ብየ? መለስኩላት የሀኒ እህት እና ጓደኛዋ ምን እንደሚያወሩ ባይሰማኝም በጣም ይሳሳቃሉ ሌላ መልክት ስልኬ ላይ ገባ ከፈትኩት እኔ ነኝ የምወስድህ ደሞ የምነግርህም ነገሮች አሉ ይላል መልክቱ ሰአቴን አየሁ አራት ሊሆን ነው መውጣት እንዳለብን አሰብኩ ግን ወጥቸስ ወዴት ብየ ራሴን ጠየኩ በዚ ሰአት በዚ ሁኔታ ሁኜ ወደ ቤት ለመሄድ የማይቻል ነው የግድ ደሞ እነሱን ቤት ማስገባት አለብኝ ለሀኒ መሄድ እንዳለብን ነገርኳት ስልኳን አውጥታ አየችና ወደነሱ ዙራ የሆነ ነገር አወራቻቸው ምን እንደተባባሉ ግን መስማት አልቻልኩም ሁለቱም ቀና ብለው አዩኝና መልሰው የሆነ ነገር አውሩ ከዛም ሀኒ እነሱ መቆየት እንደሚፈልጉና በዛ ላይ ደሞ ከጓደኛየ ቤት ነው ማደር ያሰቡት እኛ እንውጣ በቃ አለችኝ እና ተሰናብተናቸው ሆቴሉን ለቀን ወጣን አሁን ቆንጆ ሀሳብ መጣልኝ እሷን ቤቷ አድርሻት ጎደኛየ ጋር ደውየለት እሱ ጋር ማደር ያ ካልሆነ ደሞ አልጋ መያዝ ይህን ሀሳቤን ለሀኒ ነገርኳት ደስ አላላትም ከፊትዋ ያስታውቃል ቆይ በመጥፋቱ አልተስማማህም እንዴ አለችኝ ኮስተር ብላ እሺ ወዴት ነው የምንጠፋው ስል የቀድሞ ጥያቄየን ደገምኩላት እሱን እኔ አሳይሀለሁ አንተ ብቻ በሀሳቡ ተስማማ ደሞ የምነገርህ ነገር አለኝ ብየህ የለንዴ የሷ መልስ ነበር የሚሆነው ለማየት ተስማማሁ ዝም ብለህ እሽ ማለት ነው ያንተ ስራ ወዴት እና እንዴት የማለት መብትህን ለዛ
