en
Feedback
Petroleum and Energy Authority

Petroleum and Energy Authority

Open in Telegram

Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern

Show more
962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
የነዳጅ ዕጥረት ምክንያት በሆኑ ነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ፡፡******************************************* የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ሰኔ
+2
የነዳጅ ዕጥረት ምክንያት በሆኑ ነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ፡፡******************************************* የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ሰኔ 23/2014 ዓ.ም ከነዳጅ አቅራቢ ኩባኒያዎች ጋር ባደረገው ውይይት ነዳጅ ተጭኖላቸው ወደ መዳረሻቸው ባልሄዱና መረጋፍ በሚገባው ማደያ ያላረገፉ ተሸከሪካሪዎች እና ኩባኒያዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃረላ አብዱላሂ አሳውቀዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚ/ር ሚንስትር ዲኤታ ክቡር አቶ ሐሰን መሐመድ ጋር በጋራ በሰጡት አቅጣጫ ሰኔ 23/2014 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፤00 ነዳጅ ቀደም ሲል ከሶስት እና አራት ቀን በፊት ተጭኖላቸው በመዳራሻቸው ያላራገፉ ተሸከርካሪዎች የጫኑት ነዳጅ በመዳረሻቸው ካላራገፉ እንደሚወረስ ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይም ነዳጁን ባስጫኑ ኩባንያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስበዋል፡፡ በቀጣይም በነዳጅ ቁጥጥር በተቋቋመ ግብረኃይል ማደያዎች እና ከማደያ በመቅዳት ነዳጅ በሚያከማቹ አካላት ላይ ቁጥጥር በማድረግ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጸዋል፡

photo content
+5

ከነዳጅ አቅርቦት ስርጭት ጋር የተያያዘ እያጋጠሙ ባሉት ወቅታዊ ችግሮች በተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ
+9
ከነዳጅ አቅርቦት ስርጭት ጋር የተያያዘ እያጋጠሙ ባሉት ወቅታዊ ችግሮች በተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ

ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን ከሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ ከኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ ከደቡብ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ንግድ ገበያ ልማት ኢንዱስትሪና ትራንስፖርት እንዲሁም ከተለያዪ ዞኖችና ወረዳዎች ለተውጣጡ ለዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በነዳጅ ውጤቶች ማስተካከያና የታለመ ድጎማ አፈጻጸም እና ነዳጅ ግብይት ሪፎርም ጋር የተያያዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ በአዋሳና አርባ ምንጭ ከተማ ከሰኔ 3 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በዕለቱም በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አሻግሬ ጀምበሬ በሥልጠናው ላይ የተገኙ ሲሆን ሥልጠናውን በከፈቱበት ወቅት መንግስት ለነዳጅ ትልቅ ትኩረት የሰጠ ሲሆን በዚሁ ሥልጠና ላይ እየተሳተፋችሁ ያላችሁ አመራሮችና ባለሙያዎች ለሥልጠናው ትኩረት በመስጠት እንድተከታተሉ እና በቂ ግንዛቤ ይዛችሁ ለተግባራዊነቱም አፈጻጸም ራሳችሁን ከወዲሁ እንድታዘጋጁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን የእቅድ ክትትል ግምገማ ዳይሬክተር አቶ ፍሬው ረቢቱ ሥልጠናውን ሲሰጡ እንደገለጹት ከነዳጅ ዘርፉ መሠረታዊ ችግሮች መካከል ዋነኛው ከዋጋ ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲሆኑ በዚህ ረገድ ያለውን ችግር መፍታት የዘርፉን አብዛኞቹን ችግሮች መቅረፍ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በዚህም መሠረት መንግሥት በቅርቡ ከዋጋ፣ ከታሪፍና ከትርፍ ህዳግ ጋር የተያያዘ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ ውሳኔ የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ እና በፖሊሲ ያልተደገፈውንና ሀገሪቷን ለከፍተኛ ዕዳ የዳረገውን ጥቅል ድጎማ ደረጃ በደረጃ በማስቀረትና በሂደቱም አነስተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጎማ የሚደረግበትን መንገድ አመቻችቷል፡፡ የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ እና የድጎማ አሰጣጥ ውሳኔ ዓላማ ከዓለም የነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የዋጋ ማሻሻያ ባለመደረጉ ምክንያት ሀገሪቱ ካጋጠማት ከፍተኛ የዕዳ ጫና መውጣት የምትችልበትን እና በሂደቱም የህብረተሰቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መፍትሄ መስጠት ነው፡፡ ለዚህ ዓላማ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያሉ አስፈጻሚ አካላት፤ህብረተሰቡ እና አገልግሎት ሰጪዎች የመንግስትን ውሳኔ በአዎንታዊ መልኩ በመረዳት ለተፈጻሚነቱ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ በቂ መረጃ መስጠትና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ 📸 ፎቶ በ ፍቃዱ ደሴ

+5
commerical customer Presentation final.pptx2.36 KB

+1
Presentation1.of vowucher.pptx1.58 KB

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶች ሰጥተዋል በዚህም መሰረት :- አቶ ሄኖስ ወርቁ -የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል

ከነዳጅ አቅርቦት ስርጭት ጋር የተያያዘ እያጋጠሙ ባሉት ወቅታዊ ችግሮች በተመለከተ በ አምቦ ከተማ ስልጠና ተሰጠ......... የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን ከምስራቅ ወለጋ፣ ከምዕራብ ወላጋ፣ ቄለም ወለጋ፣ ምዕራብ ሸዋ እንዲሁም ሆሮ ጉዱሩ ለተውጣጡ ለዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በነዳጅ ውጤቶች ማስተካከያና የታለመ ድጎማ አፈጻጸም እና ነዳጅ ግብይት ሪፎርም ጋር የተያያዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ በአምቦ ከተማ ከግንቦት 26 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በዕለቱም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ክቡር አቶ ተስፋዬ ጌሾ በሥልጠናው ላይ የተገኙ ሲሆን ሥልጠናውን በከፈቱበት ወቅት መንግስት ለነዳጅ ትልቅ ትኩረት የሰጠ ሲሆን በዚሁ ሥልጠና ላይ እየተሳተፋችሁ ያላችሁ አመራሮችና ባለሙያዎች ለሥልጠናው ትኩረት በመስጠት እንድተከታተሉ እና በቂ ግንዛቤ ይዛችሁ ለተግባራዊነቱም አፈጻጸም ራሳችሁን ከወዲሁ እንድታዘጋጁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ስታነደርድ ገበያ ጥናት እና ምርምር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ለሜሳ ቱሉ ሥልጠናውን ሲሰጡ እንደገለጹት ከነዳጅ ዘርፉ መሠረታዊ ችግሮች መካከል ዋነኛው ከዋጋ ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲሆኑ በዚህ ረገድ ያለውን ችግር መፍታት የዘርፉን አብዛኞቹን ችግሮች መቅረፍ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በዚህም መሠረት መንግሥት በቅርቡ ከዋጋ፣ ከታሪፍና ከትርፍ ህዳግ ጋር የተያያዘ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ ውሳኔ የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ እና በፖሊሲ ያልተደገፈውንና ሀገሪቷን ለከፍተኛ ዕዳ የዳረገውን ጥቅል ድጎማ ደረጃ በደረጃ በማስቀረትና በሂደቱም አነስተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጎማ የሚደረግበትን መንገድ አመቻችቷል፡፡ የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ እና የድጎማ አሰጣጥ ውሳኔ ዓላማ ከዓለም የነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የዋጋ ማሻሻያ ባለመደረጉ ምክንያት ሀገሪቱ ካጋጠማት ከፍተኛ የዕዳ ጫና መውጣት የምትችልበትን እና በሂደቱም የህብረተሰቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መፍትሄ መስጠት ነው፡፡ ለዚህ ዓላማ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያሉ አስፈጻሚ አካላት፤ህብረተሰቡ እና አገልግሎት ሰጪዎች የመንግስትን ውሳኔ በአዎንታዊ መልኩ በመረዳት ለተፈጻሚነቱ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ በቂ መረጃ መስጠትና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በነዳጅ ግብይት ሪፎርም አፈጻጸም ግንዛቤ ማስጨበጫ በይፋ ተጀመረ። ........................ በአማራ ብ/ክ/መ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እንዲሁም ኦሮሚያ ብ/ክ/መ ንግድ ቢሮ ሃላፊዎች እ
+9
በነዳጅ ግብይት ሪፎርም አፈጻጸም ግንዛቤ ማስጨበጫ በይፋ ተጀመረ። ........................ በአማራ ብ/ክ/መ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እንዲሁም ኦሮሚያ ብ/ክ/መ ንግድ ቢሮ ሃላፊዎች እና ባለሙያዎች በነዳጅ ግብይት ሪፎርም አፈፃፀም እና የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ እና የታለመ ድጎማ ማስፈፀሚያ የህግ ማዕቀፎች በተመለከተ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ግንቦት 26 በ ባህርዳር እና አምቦ ከተማ በይፋ ተጀምሯል::

በነዳጅ ግብይት ሠንሠለት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰኑ የውሳኔ ሃሳቦች አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ።( ድሬ ቲቪ)

የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ተፅእኖ በማያደርስ ሁኔታ ይፈፀም ዘንድ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ ። ነዳጅ በሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ ቁልፍ ሚና የሚጫወትና ከእያንዳንዱ ዜጋ ኑሮ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት የችርቻሮ መሸጫ ዋጋው በኢኮኖሚውና በህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንዳይፈጥር ቁጥጥር እያደረገበት ለረጅም ጊዜያት ሲሰራበት ቆይቷል ። በተለይም የነዳጅን ዋጋ ለማረጋጋት ይቻል ዘንድም በመንግስት በኩል የነዳጅ ዋጋ ማረጋጊያ ፈንድ በአዋጅ ተቋቁሞ በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን የፈንዱ ዋና አላማም በአለም ገበያ በሚከሰተው የነዳጅ ዋጋ ማደግ ምክንያት የሚያስፈልገውን ተጨማሪ ወጪ በመደጎም የነዳጅ ዋጋን ማረጋጋት ነው ። ከዚሁ ጋር ተያይዞም በዛሬው እለት በኢትዮጲያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አዘጋጅነት የነዳጅ ድጎማና ዋጋ ማስተካከያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በድሬዳዋ አስተዳደር እየተሰጠ ይገኛል ። በዚሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሀርቢ ቡህ በተለይም የሀገራችንን ወቅታዊ የማክሮ ኢኮኖሚ እንዲሁም የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የሀገር ውስጥ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ የአለም አቀፍን ዋጋ በሚያንፅባርቅ መልኩ እየታየ በየጊዜው እየተከለሰ ወደ ሸማቹ ህብረተሰብ እንዲተላለፍ መደረግ የሚገባው የነዳጅ ዋጋ ከ 2009 ዓ.ም ጀምሮ ወቅቱን በጠበቀና የአለምን ዋጋ ባገናዘበ መልኩ ማስተካከያዎች ሳይደረጉ በመቆየታቸው ምክንያት በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የሆነ እዳ በሀገር ላይ ተከማችቶ እንደሚገኝ ተናግረዋል ። አቶ ሀርቢ ቡህ አክለውም የነዳጅ ውጤቶች ዋጋ ማስተካከያ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ የጎላ ተፅእኖ በማያደርስ ሁኔታ እንዲፈፀም ለማስቻል ይቻል ዘንድም በመንግስት በኩል ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች የተመረጡ ሲሆን አገልግሎት አሰጣጡ ህዝብን መጥቀሙን ለማረጋገጥ ስራዎቹ ወደ ህዝብ መውረድና የሚፈለገውን ግብ ማሳካት እንደሚኖርባቸው ተናግረው ይህንንም ማድረግ የሚችለው በተቀናጀ አግባብ ሁሉም ግንኙነት ያላቸው አካላት ስራውን ወደ መሬት ማውረድ ሲችሉና ህብረተሰባችንም የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያና የታለመ የነዳጅ ዋጋ ድጎማ በሀገራዊ ኢኮኖሚያችንና በህብረተሰቡ ውስጥ ሊያመጣ የሚችለውን ፋይዳ ማስረዳትና በአግባቡ መተግበር ሲቻል መሆኑን አቶ ሀርቢ ቡህ በእለቱ ተናግረዋል ። በነዳጅ ላይ የሚስተዋለውን የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድም በሶማሌ ክልልና በደቡብ ኦሮሚያ ባሉ ከተሞችና አካባቢዎች የሚሄዱ ነዳጆች ላይ ኮታ በማስቀመጥ ችግሩን መቀነስ መቻሉን በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ስታንዳርድ ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ለሜሳ ቱሉ ተናግረዋል ። በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይም ከፍተኛ የድሬዳዋ አስተዳደርና የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አመራሮች ፣ የምእራብ ሀረርጌ ፣ የምስራቅ ሀረርጌ ፣ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፣ ሀረር እንዲሁም የድሬዳዋ የንግድ ቢሮና የትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች ተሳታፊ ሆነዋል ። በአለማየሁ አበበ ። ፎቶ :- በሙሉአለም ደሴ ። የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCQNCC5tcc6Jd9zCKcmzQ-eA ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/DDGCAB በትዊተር ይወዳጁን https://twitter.com/DawaOffice ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን!

የውይይቱ ተሳታፊዎች በቀረቡት ሠነዶች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ሀገሪቱ በነዳጅ ዘርፍ እያጋጠማት ካላው የዕዳ ጫና ለመውጣት በመንግስት የተወሰነው የውሳኔ ሃሳብ ተገቢ መሆኑን ገልጸው አፈፃፀሙን በተመለከተ ጠንካራ ክትትል እና ቁጥጥር እናደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በዕለቱ መድረክ ማጠቃለያ ላይ በባለስልጣን መ/ቤቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በተሰጠው ምላሽ በነዳጅ ግብይት ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የነዳጅ ውጤቶች መሸጫ ዋጋ ማሻሻያ እና የታለመ ድጎማን ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያግዙ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ለማፅደቅ በሂደት ላይ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን ረቂቅ መመሪያዎቹም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

በነዳጅ ግብይት ሠንሠለት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰኑ የውሳኔ ሃሳቦች አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ። የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ እና የታለመ ድጎማ ውሳኔ አፈፃፀምን
በነዳጅ ግብይት ሠንሠለት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰኑ የውሳኔ ሃሳቦች አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ። የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ እና የታለመ ድጎማ ውሳኔ አፈፃፀምን በተመለከተ የተቀናጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ በአዳማ እና ድሬደዋ ከተሞች በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሰልጣን በአገር አቀፍ ደረጃ ለመስጠት በታቀደ የግንዛቤ ማስጨበጫ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር፤ሱማሌ ክልል እንዲሁም በአዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ ዞኖች እና ወረዳዎች የንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል፡ በአዳማ ከተማ በተካሄደው መድረክ የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገሶ ለተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት የነዳጅ ውጤቶች መሸጫ ዋጋ ማስተከከያ እንዲሁም የታለመ ድኀማ አፈጻጸም አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ባገናዘበ መልኩ ተፈጻሚ እንደሚሆን ገልጸው ለተፈጻሚነቱ በየደረጃው ያሉ የስራ ኃላፊዎች ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅ ገልጸዋል፡ በውይይት መድረኩ በነዳጅ ግብይት ሠንሠለት ያሉ መሠረታዊ ችግሮች፤ችግሩን ለመፍታት የተቀመጡ የመፍቴ ሃሳቦች እና አፈጻጸማቸውን የተመለከቱ ሠነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።