Petroleum and Energy Authority
Open in Telegram
Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern
Show more962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
Repost from Ethiopian Electric Utility
በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅርቦት
በአማራ ክልል በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ ላይ በሚገኘው የሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብሬከር ብልሽት ምክንያት በመርጦለ ማርያም፣ በግንደወይን፣ በፈለገ ብርሃን እና አካባቢው ላይ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡
በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን የተቋረጠውን የኤሌክሪክ አገልግሎት ወደ ነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አውቃችሁ፤ በትዕግስት እንድትጠብቁ እናሳዉቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የበለጠ መረጃ ለማግኘት ይህንን ድረ-ገፅ ይጎብኙ፡ http://www.eeu.gov.et
ወደ ሽረ ከተማ ነዳጅ እየተጓጓዘ ነው (FBC) - የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ወደ ሽረ ከተማ ነዳጅ እየተጓጓዘ መሆኑን የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በባለስልጣኑ የነዳጅ አቅርቦት፣ ሎጅስቲክስና ክትትል ዳይሬክተር አቶ ፈቃዱ ሹመት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች ጥገናቸው ለተጠናቀቁ እና ምርቱን ለጠየቁ የነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ ለማቅረብ በልዩ ትኩረት እየተሠራ ነው፡፡
በዚህም በሦስት ሚኒስትር ዴኤታዎች የተመራ ቡድን በጎንደር-ደባርቅ-ሊማሊሞ-ማይጠምሪ- ሽረ እንዲሁም በደሴ- ወልዲያ- ሀራ መገንጠያ- ቆቦ- አላማጣ- ኮረም እና በዓብዓላ መስመር የነዳጅ ማደያዎችን ሁኔታና ነዳጅ ለማቅረብ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ከቡድኖቹ ምልከታ በኋላ ከማደያዎቹ ባለቤቶች ጋር ማደያዎቹ በአስቸኳይ በሚጠገኑበት ሁኔታ ላይ በተደረገው ተከታታይ ውይይት የተወሰኑት መጠገናቸውን እና በጥገና ሂደት ላይ ያሉ መኖራቸውንም ነው የተናገሩት።
በዚህም በሽረ ከተማ ለሚገኝ አንድ ማደያ ነዳጅ እየተጓጓዘ ሲሆን፥ በዚሁ ከተማ ለሚገኙ ተጨማሪ አንድ ማደያ እና በማይጠምሪ ለሚገኝ አንድ ማደያ ደግሞ በዚህ ሣምንት ነዳጅ ማጓጓዝ እንደሚጀመርም አስረድተዋል።
በሌላ በኩል በደሴ-ወልዲያ- ሐራ መገንጠያ- ቆቦ መስር ላሉ ማደያዎች ግን ነዳጅ እቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በአላማጣ እና ኮረም የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ባለቤቶች የገንዘብ እጥረት ስላለብን ነዳጅ ለማዘዝ አንችልም በማለታቸው ነዳጅ ለማቅረብ አለመቻሉ ተገልጿል፡፡ ባለቤቶቹ በሚጠይቁ ጊዜ ምርቱ እንደሚቀርብም ነው የተመላከተው፡፡
በዓብዓላ ያሉ ሁለት ማደያዎች ባለቤቶቻቸው ባለመገኘታቸው ነዳጅ ለማቅረብ የሚያስችል ሁኔታ ቢኖርም ሁኔታው መስተጓጎሉን አንስተዋል፡፡
ለጊዜው ግን ባለስልጣኑ ከአፋር ክልል ንግድ ቢሮ ጋር በመነጋገር በጀሪካን እና በበርሜል ነዳጅና ቤንዚል እየቀረበ መሆኑን ተናግረው ባለቤቶች ተገኝተው ለኩባንያዎቹ ክፍያ ሲፈጽሙና ነዳጅ እንዲቀርብላቸው ጠይቀው አስፈላጊውን ሂደት እንደጨረሱ ነዳጁን ለማቅረብ እንደሚቻልም አረጋግጠዋል።
የተለጣፊ ምልክት ትግበራ ፕሮግራምና ተጠባቂው ውጤት
*******************************************************************************************
በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ከአጠቃላይ ከሚመነጨው 5000 ሜጋ ዋት ኃይል በላይ የኢነርጂ ምርት ከ25 እስከ 26 በመቶ የሚሆነው ኢነርጂ አገልግሎት ሳይሰጥ ቴክኒካል እና ቴክኒካል ባለሆኑ ምክንያቶች እንደሚባክን መረጃዎች ይጠቁማሉ ፡፡ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ባስጠናው ጥናት ቴክኒካል ባልሆኑ ምክንያቶች የሚባክነው ኢነርጂ በዋነኝነት ብቃት በሌላቸው የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎችና መሳሪያዎች እንዲሁም በአጠቃቀም ወቅት በሚታዩ ቸልተኝነቶች እንደሚፈጠሩ ያመለክታል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ለአገልግሎት የቀረበውን ኢነርጂ ከብክነት ለመከላከል በባለስልጣን መ/ቤቱ በኩል የኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ስትራቴጂውን ለማስፈፀም የተለያዩ ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል፡፡ ከእነዚህም ፕሮግራሞች መካከል የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ ኢነርጂ ብቃት ተለጣፊ ምልክት ፕሮግራም አንዱ ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም በኤሌክትሪክ የሚሠሩ መገልገያ ዕቃዎች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን ባልሰልጣኑ ባስጠናው ጥናት ውጤት የኢነርጂ ብቃታቸው ዝቅተኛ የሆኑ በመኖሪያ ቤትና በኢንደስትሪዎች ግልጋሎት ላይ የሚውሉ ዕቃዎችን በመለየት ደረጃ በደረጃ ብቃት ባላቸው ዕቃዎች መተካት የሚያስችል የተለጣፊ ምልክት ትግበራ ፕሮጀክት በመንደፍ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ፡፡
በተለጣፊ ምልክት ፕሮግራም ትግበራው በቤት ውስጥ ግልጋሎት ላይ የሚውለው የእንጀራ መጋገሪያ ምጣድ ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ። ይህም የሆነው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባስጠናው ጥናት የኤሌክትሪክ እንጀራ መጋገሪያ ምጣድ ምርት የኢነርጂ አጠቃቀም ብቃት ዝቅተኛ ሆኖ በመገኘቱ ነው።
" በ2007 ዓ.ም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባስጠናው ጥናት በሀገራችን ወደ 530 ሺህ የሚደርሱ የኤሌክትሪክ እንጀራ ምጣዶች አገልግሎት ላይ መዋላቸዉን እነዚህም ምጣዶች እያንዳዳቸዉ ከ3 ነጥብ 7 እስከ 4ኪ.ዋ የኃይል ፍጆታ እንዳላቸው ተረጋግጧል ፡፡ በዚሁ ጥናት ላይ በተገኘ መረጃ መሠረት የሀገሪቱን የሀይል ፍላጎት ጣሪያን በ800ሜ.ዋ በሚገመት መጠን እንዲጨምር ማድረጉን ያሳያል ፡፡ በአብዛኛው ምርቶቹ ከ3 እስከ 4 ኪ.ዋ በሰዓት እንደሚጠቀሙ ጥናቱ ያመለከታል ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከአጠቃላይ የአገሪቱ ኤሌክትሪክ አቅርቦት 37 በመቶ ለመኖሪያ ቤት ግልጋሎት እንደሚውል መረጃዎች ይጠቁማሉ ። አብዛኞቹ መኖሪያ ቤቶች የኤሌክትሪክ ምጣድና ምድጃ ተጠቃሚዎች እንደሆኑና አገልግሎት ላይ ከሚውለው ኤሌክትሪክ ፍጆታቸው 60 በመቶ ያህሉን ኤሌክትሪክ ምጣድ ይውላል ። የኤሌከትሪክ እንጀራ ምጣዶቹ ደግሞ የምርት ሂደታቸውም በአብዛኛው ሳይንሳዊ ሂደትን የተከተለ ልኬት የማይደረግበት በመሆኑ ግልጋሎት ላይ በሚውልበት ወቅት ከፍተኛ የሆነ ኢነርጂን በመጠቀም አብዛኛው ኢነርጂ ግልጋሎት ላይ ሳይውል እንዲባክን ያደርጋሉ ፡፡
የኢነርጂ ብክነት መፈጠሩ በተገልጋዩ ህብረተሰብ እና በአገልግሎት ሠጪው ተቋም ወይም መንግስት ላይ ቀላል የማይባል ኪሳራን የሚያስከትል ሲሆን በምርቱ ምክንያት በሚከሰትው ብክነት ተገልጋዩ ያለአግባብ ለሚባክነዉ ኢነርጂ ለተጨማሪ ክፍያ የሚዳርግ ይሆናል። በሌላ በኩል በአገልግሎት ሰጪው ተቋም ላይ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ መጨናነቅ እና የኃይል ብክነት እንደሚፈጠር ይሆናል ። መስመር ላይ የሚከሰተውም የኃይል ብክነት የኃይል መቆራረጥ እንዲከሰት በማድረግ ጉዳት ያስከትላል ፡፡ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ወጪ ወጥቶባቸው በሚገነቡ እና ለአገልግሎት በሚውል ማመንጫዎች የሚመረተው ኢነርጂ ያለአግባብ መባክን በአቅርቦት ተደራሽነት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እንደሚኖረው ባለሙያዎች ይናገራሉ ።
በመሆኑም ባለስልጣን መስሪያቤቱ የምርቱን የኢነርጂ ብቃትን ለማሻሻል በተነደፈው ፕሮግራም መሠረት ለኤሌክትሪክ ምጣድ የምርት ደረጃ እና ዝቅተኛ የኢነርጅ ብቃት ደረጃን እንዲወጣ ተደርጓል፡፡ ይህን ተከትሎ የኤሌከትሪክ እንጀራ ምጣድ ምርቶች ላይ የኢነርጂ ብቃት ፍተሻ በማድረግ ለምርቱ የተለጣፊ ምልክት ትግበራ ተጀምሯል፡፡
በቀጣይ እንደ ኤሌክትሪክ ምድጃ ሁሉ በሌሎች ምርቶች ላይ የፍተሻ ስርአቶችን በማውጣትና በመተግበር ፤ ከኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ሰብስቦ በማደራጀት የትንተና ስራ ተሰርቶ ከዚህ የኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ፕሮግራም የተቆጠበውን ኢነርጂና ከቁጠባው የተገኘውን ፋይዳ ለተጠቃሚውና ለሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን የማሠራጨት ስራ የሚሠራ ይሆናል ። በአጠቃላይ የተለጣፊ ምልክት ፕሮግራሙ የተቀመጠለትን ግብ መምታት ከቻለ በአገር ደረጃ 623ሜጋ ዋት - 487 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂን ከብክነት ማዳን ያስችላል ተብሎ እንደሚገመት ባለሙያዎች ይገልጻሉ ።
Repost from Ethiopian Electric Utility
ዛሬ ከረጅም ጊዜ በኃላ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በድጋሚ ባገኘችው የሁመራ ከተማ ያለው የምሽት ድባብ በምስል
Repost from Ethiopian Electric Utility
ማይጫውና አካባቢው ኤሌክትሪክ ሃይል ዳግም አገኙ
*************
በጦርነቱ ምክንት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ የማይጫው ከተማና አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሃይል ዳግም ማግኘታቸውን በኢትጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የወልድያ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሽመል ወ/ሰማያት ገልፀዋል፡፡
ዳይረክተሩ አክለውም አካባቢው የኤሌክትሪክ ሃይል ዳግም ያገኘው ከአላማጣ-ማይጨዉ የተዘረጋው የ66 ኪ.ቮ የሃይል ማስተላለፊያ መሰመር ጥገና ተከናዉኖ በመጠናቀቁ ነው ብለዋል፡፡
በጥገና ሂደቱ ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ የተቋሙ ባለደረቦችና ድጋፍ ላደረጉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረብን በቀጣይ ሌሎች ኤሌክትሪክ የተቋረጠባቸው አካባቢዎች መልሰው እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
ለአገልግሎት ፈላጊ ደንበኞቻችን
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የቢሮ አድራሻ ለውጥ በማድረግ ካዛንቺስ እና ልደታ ከሚገኙ ቢሮዎች በመልቀቅ ጉርድ ሾላ በሚገኘው ማዕድን ሚንስቴር ጊቢ ውስጥ ቢሮውን ያዛወረ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
አገልግሎታችንን ፈልጋችሁ ለምትመጡ ደንበኞቻችን ከሰኞ ታህሳሳ 3/4/2015 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት የምንሰጠው ጉርድ ሾላ በሚገኘው ማዕድን ሚንስቴር ጊቢ ውስጥ ባለው ቢሮ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ
ስልክ፡ 09 22 16 20 98
ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን!
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል፡፡*******************************************************
ሕዳር 27 / 2015 ዓ.ም የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ይፋ እንዳደረገው የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር 2015 ዓ.ም እየተሸጠበት ባለው ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን አስታወቀ።
በዚህም መሠረት ከኅዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር 2015 ዓ.ም እየተሸጠበት ባለው ዋጋ ያለምንም ለውጥ እንዲቀጥል የተወሰነ መሆኑን ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዓለም ዓቀፍ የነዳጅ ዋጋን መሠረት አድርጎ በየወሩ የነዳጅ ዋጋ ክለሳ ጥናት በማድረግ ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚ/ር የሚያቀርብ ሲሆን ከነዳጅ ድጎማ ስርዓት በሂደት ለመውጣት እና የነዳጅ ዋጋ ማረጋጊያ ፈንድ ስርዓት ወደ ነበረበት ለመመለስ የዋጋ ክለሳ ጥናቱ በየወሩ የሚደረግ ይሆናል፡፡
የ905 የስልክ ጥሪ ማዕከል ላይ ምልከታ ተደረገ፡፡ ******************
በኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስልክ ጥሪ ማዕከል የ905 አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድና ኢኮኖሚክስ ሬጉሌሽን ዳይሬክቶሬት የደንበኞች አገልግሎት ቡድን እና የህዝብ ግንኙነት ክፍል ህዳር 21/2015 ዓ.ም በጥሪ ማዕከሉ በመገኘት የአገልግሎት አሰጣጡን ተመልክተዋል፡፡
ቡድኑ በአገልግሎት መስጫ ማእከል በመገኘት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞች አገልግሎት ጥሪ ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጄ አስማማው እና የደንበኞች አገልግሎት ድጋፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፍሬ ህይወትን አነጋግሯል፡፡
ውይይቱ በባለስልጣን መ/ቤቱ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ ቼክ ሊስት መሠረት የ905 የስልክ ጥሪ አገልግሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን የጥሪ ማዕከሉን በመጎብኘት አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበሩ ባለሙያዎችንም አነጋግሯል፡፡
በተደረገው ውይይት ለመረዳት እንደተቻለው የጥሪ ማዕከሉ በስታንዳርዱ መሠረት ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች ሶስት ዓይነት የጥሪ አገልግሎት፤ከኤሌክትሪክ አደጋ፣ስርቆት ጋር የተያዙ ጥቆማዎችና መረጃዎች፣ የኤሌክትሪክ መቋረጥ፣የቆጣሪ ንባብና ከከፍያ ጋር ተያያዥ ለሆኑ ጉዳዮች እንዲሁም መረጃ ለማግኘት የስልክ ጥሪ አገልግሎት እንደሚሰጥ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ የስልክ ጥሪ አገልግሎት ጥራትን በተመለከተ በስልክ መስመር የጥበቃ ሠዓት፣የአገልግሎት መሰጫ ሠዓት፣ጥሪ የመቀበል አቅም፣ምላሽ ሳይሰጥባቸው የቀሩ ጥሪዎችን በተመለከተ ለማየት ተሞክሯል፡፡ በዚሁ መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስልክ ጥሪ ማዕከል በሶስት ሺፍት የ24 ሠዓት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ጥሪ የማስተናገድ አቅሙ በሁለት ማዕከላት በ80 ስልኮች 40 እንዲሰሩ በማድረግ በ40ዎቹ ተጠባባቂነት አገልግሎት ይሠጣል፡፡ ለአንድ ጥሪ መቀበያ አማካኝ ሠዓት አንድ ደቂቃ ከሠላሣ ሰከንድ ሲሆን ለአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሪፖርት ማድረጊያ አንድ ደቂቃ ከአስራ አምስት ሠከንድ ስታንዳርድ ተቀምጦ እየተሰራበት ይገኛል፡፡
ከባልስልጣን መ/ቤቱ በጥሪ ማዕከላቱ ምልከታ ያደረገው ቡድን ከውይይቱ እና ከማዕከሉ ግቡኝቱ እንደተረዳው፤ የጥሪ ማዕከሉ አገልግሎት የሚሰጠው ለአዲስ አበባ ብቻ መሆኑ እንደ ክፍተት የታየ ሲሆን ማዕከሉ ካሉት ጥሪ መቀበያ ስልኮች 25 ያህሉ በሰው ኃይል ዕጥረት እና በተለያዩ ምክንያቶች ክፍት መሆናቸው ለ905 ጥሪ ማዕከል ላይ ለሚፈጠሩ ጫናዎች ምክንያት መሆናቸውን ለማየት ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ የስልክ ጥሪ የሚያደርጉ ደንበኞች ቢዝነስ ፓርትነር ቁጥር ሳይዙ መደወልና በማዕከሉ ምላሽ ለማያሰጥባቸው ጉዳዮች የሚደረጉ ጥሪዎች ለጥሪ መቋረጥ እንደ ምክንያትነት የሚጠቀሱ ችግሮች መሆናቸውን ለማየት ተችሏል፡፡
ከጥሪ ማዕከሉ ኃላፊዎች እንደተረዳነው ችግሮችን ለማስቀረት የጥሪ ማዕከሉ በክልሎች የሚከፈትበት ሁኔታ እየታሰበበት መሆኑን፣ክፍት የሆኑ ወንበሮችን የሰው ኃይል ከማሟላት በተጨማሪ የተሸሻሉ ጥሪ መቀበያ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን እና ከደንበኞች ጋር በተገናኘ የደንበኛውን ሙሉ መረጃ ወደ ሲስተም በማስገባት የቢዝነስ ፓርትንር ቁጥር መጠየቁን ለማስቀረት በመሰራት ላይ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
የነዳጅ ድጎማ ማሻሻያ ለድጎማ ይወጣ የነበረን ወርሃዊ ወጪ ከ10 ቢሊየን ብር ወደ 4 ቢሊየን ዝቅ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የነዳጅ ድጎማ ማሻሻያ መንግስት ለድጎማ ያወጣው የነበረውን ወርሃዊ ወጪ ከ10 ቢሊየን ብር ወደ 4 ቢሊየን ብር ዝቅ ማድረጉን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ገለጸ፡፡
ባለፉት ሶስት ወራት በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተጣለ ተጨማሪ እሴት ታክስ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱንም ነው ባለስልጣኑ ያስታወቀው፡፡
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ እንደተናገሩት÷ ከሶስት ወራት በፊት ተግባራዊ የሆነው የታለመለት ነዳጅ ድጎማ ማሻሻያ በዘርፉ እምርታ እያመጣ ነው።
ለአብነትም መንግስት በየወሩ በነዳጅ ድጎማ ይደርስበት የነበረውን ኪሳራ ከ10 ቢሊዮን ወደ 4 ቢሊየን ብር መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል።
መንግስት እስካሁን በነዳጅ ድጎማ 179 ቢሊየን ብር ዕዳ ወይም ኪሳራ እንዳለበት ጠቅሰው÷ የድጎማው ሂደቶች እየተስተካከሉ ሲመጡ ቀስ በቀስ ዕዳውን መቀነስ ያስችለዋል ብለዋል።
መንግስት ለነዳጅ ግዥ የሚያወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ እንደ ፖሊሲ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች እንዲገቡ ማበረታቻዎች ተግባራዊ እንደሚደረግም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ቴክኖሎጂን በመጠቀም የነዳጅ ተደራሽነት ላይ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሯ ጠቅሰዋል።
በዚህም ነዳጅ በሚያመላልሱ አገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎችና ነዳጅ ማደያዎች ላይ ቴክኖሎጂዎችን በመግጠም ቁጥጥር ስራውን ለማጠናከር እየተሰራ እንደሆነ መነጋራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
መንግስት ከዓለም የነዳጅ ገበያ ዋጋ አንጻር አሁንም ድጎማ እንደሚያደርግ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ÷ ለአብነትም በዓለም አቀፍ ዋጋ ቢሆን ኖሮ አሁን ላይ ናፍታ 81 ብር፤ ቤንዝን ደግም 66 ብር በሊትር ይሸጥ ነበር ብለዋል።
ከድጎማ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ በታሪፍና መሰል ጉዳዮች ላይ አሁንም በተለይ በክልል ዋና ዋና ከተሞች የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ባለስልጣኑ ከክልሎች ጋር እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመ**************************************************************
የባለስልጣን መ/ቤቱ የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፀፀም የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች፣ በመካከለኛ አመራሩ እና ሠራተኛው ጥቅምት 29/2015 በአዳማ ከተማ በተዘጋጀ መድረክ ተገመገመ፡፡
ዕቅድ አፈፃፀሙ በበለስልጣን መ/ቤቱ ዕቅድ ዝግጅት፣ክትትልና ግምገማ ዳይረክቶሬት በኩል የቀረበ ሲሆን በሠራተኛው እና በመካከለኛው አመራሩ በአፈፃፀም ላይ የታዩ ክፍተቶች ተገምግመው በቀጣይ በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ የሚሰሩ የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር እና በዝግጅት ምዕራፍ የታዩ ክፍተቶችን በማሻሻል ለቀጣይ ሩብ አመት አፈፀፀም ምን መምሰል እንዳለበት በመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡
ከተቋሙ የዕቅድ አፈፃጸም በተጨማሪ ለመንግስት አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች የወቅቱን አገራዊ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ ለማብራራት የተዘጋጀ ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያ ባለስልጣን መ/ቤቱ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች የህዝቡን ማህበራዊ ህይወት ለማሻሻል፣ኢኮኖሚ ዕድገቱን ለመደገፍ እና ለዘላቂ ሠላም ለማስፈን በሚደረጉ ጥረቶች የተቋሙ ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በመጠየቅ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
የበይነ መረብ (eService) አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ የሚሰጡ የበይነ መረብ(online) አገልግሎቶች ላይ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ከጥቅምት 25-26 የሚቆይ ስልጠና በአዳማ ከተማ በፔራጎ ቴክኖሎጂ ካንፓኒ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚሰጡ አገልግሎቶች መካከል የኤሌክትሪክ ስራ ፈቃድ፣የኤሌክትሪክ ንግድ ብቃት ማረጋገጥ፤የኢነርጂ ኦዲት ፈቃድ ;የኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች ቅሬታ ማስተናገድ እና የመረጃ አገልግሎቶች በበይነ መረብ ማስተናገድ የተጀመረ ሲሆን በነዳጅ ዘርፍ ለተሰማሩ ካንፓኒዎች ፈቃድ መስጠት፣የነዳጅ ጭነት ማረገፍ ዳይቨርሽን ፈቃድ፣ለነዳጅ አቅራቢ ካንፓኒዎች ነዳጅ ትስስር ፈቃድ እና ሪፖርት የመላክ አገልግሎቶችን ወደ eService አገልግሎት አሰጣጥ ስርአት ውስጥ በማስገባት አገልግሎቱን ለማስጀምር የሚያስችል ዝግጅቶች በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡
የስልጠናው ዓላማም በነዳጅ ዘርፍ እና በኢነርጂ ዘርፉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በበይነ መረብ በመታገዝ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ብቁ ሆነው ሙሉ በሙሉ ወደስራ ለመግባት የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ነው፡፡
በኤሌክትሪክ ማብሰያ ዕቃዎች እና የኢነርጂ አጠቃቀም ችግሮች እና መፍትሄዎች በተመለከተ ስልጠና መሰጠቱ ተገለፀ ............................................................. በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስጣን በአዳማ ከተማ ጥቅምት 17ና 18 /2015አ. ም ለተውጣጡ ት ለአዲስ አበባ ከተማ የሴቶች ማህበር ሓላፈዎች እና ባለሙያዎች በኤሌክትሪክ ምጣዶች :ምድጃዎች:ፍሪጅና የመብራት አምፑሎች የኢነርጂ አጠቃቀም ችግሮች እና መፍትሔ ስልጠና መሰጠቱን ተገልጿል ።
የስልጠናው ዋና አላማ የነዳጅና ኢነርጂ ባስልጣን የኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ኢነርጂ አብዱራዛቅ መሐመድ እንደ ገለፁት ለአገሪቱ በከፍተኛ ፍጥነት የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት እንዲሁም በአገሪቱ ካለው የኤለክትሪክ ፍጆታ ውስጥ አንድ ሶስተኛው የሚሆነው ለቤት ውስጥ ሀይል ተጠቃሚዎች የሚውል መሆኑ ጥናቶች ያሳያሉ :ይህም ፍላጎት በየዓመቱ የዘጠኝ በመቶ ያህል እድገት እንደ ሚያሳይ ጥናቶች ያረጋግጣሉ ። ለቤት ከሚለው ሀይል ከፍተኛውን የሚወስደው የኤሌትሪክ ምጣድ :የኤሌትሪክ ምድጃዎች ከፍተኛውን የኢነርጂ አጠቃቀም ችግሮችን በትክክል በመለየት ለችግሮቹ በቂ የመፍትሄ እርምጃ ለመውሰድ ባስልጣኑ ቅድመ ሑኔታውን አጠናቆ ወደ ትግበራው መግባቱን ስልጠናው ወቅት ለተሣታፊዎቹ አብራርተዋል ።
